Thursday, January 16, 2014

ሕወሃት የትግራይን ሕዝብ እያሸበረ ነዉ ፣ ድብደባዉ፣ ለቅሶው፣ ተኩሱ ተጧጡፏል


 አፅቢ ወንበርታ በምስራቅ ትግራይ የምተገኝ ወረዳ ናት። በ2007 ሕዝብ ቆጠራ መሰረት፣ ከመቶ አሥር ሺህ በላይ ነዋሪዎች ያሏት ናት። የአጽቢ ወረርታ ወረዳ ተብላ ትታወቃለች። በወረዳዋ መሃከል የምትገኝዉ ከተማ የአጽቢ ከተማ ናት። ከመቀሌ70 ኪሎሜተር በስተሰሜን፣ ከአዲግራት 94 ኪሎሜተር በስተደቡብ፣ከዉቅሮ 20 ኪሎሜተር በስተ ምስራቅ የምትገኝ ናት።

 የዚህ ከተማ ነዋሪዎች በከፍተኛ ዉሃ እጥረት ምክንያት ከሕወሃት/ባለስልጣናት ጋር ትልቅ ዉዝግብ ላይ ናቸው። በከተማዋ የሚኖሩ ገበሬዎችን የሚወክሉ አራት አዛዉንት ታግተው የታሰሩ ሲሆን፣ ሕወሃቶች ሕዝቡን እየደበደበ፣ እያሰቃዩ፣ መሳሪያም እየተኮሱ ነዉ። ሕዝቡ ለተወሰነ ጊዜ ፖሊሶችን አግቶ ፣ የወከሉን ገበሬዎች እንዲፈቱ የሚል ጥያቄ አቅርቦ የነበ ረ ቢሆን፣ ከለለኦች ወረዳዎች አካባቢዉን የማያወቅ ታጣቂዎቹን በማስመጣት ሕዝቡን እየደበደቡት ነዉ።

በቅርቡ ከአንድነት ፓርቲ ጋር ለመዋሃድ ጥያቄ ያቀረበዉና በድርድር ላይ የሆነዉ የአረና ትግራይ አመራር አባል፣ አብርሃ ደስታ፣ በፌስ ቡክ ከመቀሌ የዘገቡትን እንደሚከተለው አቅርበናል ፤ ይከታተሉ።

ሰበር ዜና

የአፅቢ ግጭት (ክፍል አንድ)

ባሁኑ ሰዓት (ሓሙስ 08/05/06 ዓም ከቀኑ 11:30 ጀምሮ) በአፅቢ ወንበርታ ወረዳ (ጣብያ ሩባ ፈለግ ቁሸት ሕኔቶ) በህዝብና አስተዳዳሪዎች መካከል (በውኃ አጠቃቀም ምክንያት) በተፈጠረ አለመግባባት ሃይለኛ አምባጓሮ ተፈጥሯል። ፖሊሶች ተኩስ ከፍተዋል (ከ11:30 እስከ 11:40 ሰዓት ባለግዜ ለሰላሳ ሰባት (37) ግዜ ተተኩሷል)። ምልሻዎች በተጠቀቅ ይገኛሉ። የመንግስት የሚድያ ሰዎች ሂደቱ እየቀረፁት ነው። የቆሰለ ውይም የሞተ ሰው ስለሞኖሩ ወይ አለመኖሩ በግርግሩ ምክንያት ለማወቅ አልተቻለም። ተኩሱ እየቀጠ ነው። ተጨማሪ መረጃ አቀርባለሁ።

የአፅቢ ግጭት (ክፍል ሁለት)

በአፅቢ ወንበርታ ወረዳ ህዝብና አስተዳዳሪዎች መካከል ባጋጠመ ግጭት ፖሊስ ቢተኩስም ችግሩ ከፖሊስ አቅም በላይ በመሆኑ አሁን አስተዳደሩ የመከላከያ ሰራዊትን እርዳታ ጠርቷል። አሁን የመንግስት ምልሻዎች በአከባቢው እየተሰማሩ ይገኛሉ። በግጭቱ የተሳተፈው ኗሪ ህዝብ ከሺ በላይ ይሆናል። እስካሁን ድረስ የኗሪው ህዝብ ተወካዮች የነበሩ አራት ሰዎች የት እንደገቡ አይታወቅም። ፖሊሶች ህዝቡን ለመበተን ሃይል ቢጠቀሙም ህዝቡ ግን አራቱ ተወካዮቹ ካልተለቀቁ ላለመበተን አድማ መቷል። ህዝብ እየተሰባሰበ ነው። (የተኩስ ድምፅ በስልክ አስደምጠውኛል)።

የአፅቢ ግጭት (ክፍል ሦስት)

በአፅቢ ወንበርታ በተከፈተው ግጭት የመንግስት ፖሊሶች ተኩስ መክፈታቸው፣ አርሶአደሮች መደብደባቸው፣ እንዲሁም አራት የኗሪዎቹ ተወካዮች በሃይል አስረው ወዳልታወቀ አከባቢ መውሰዳቸው ታውቋል። ህዝቡም (የአከባቢው ምልሻዎች ሳይቀሩ) አስራ ሁለትፖሊሶችና አንድ የመንግስት ምልሻ ከበው አግተው ይዟቸው ቆይተዋል። አራቱ የህዝቡ ተወካዮች እስካልተለቀቁ ድረስ ፖሊሶቹ እንደማይለቀቁ የአርሶ አደሮቹ ተወካዮች አሳውቀው ነበር። አሁን በተደረገ ድርድር አራቱ ተወካዮች ይፈታሉ፣ በህዝቡ ታግተው የነበሩ  አስራ ሁለት ፖሊሶችም ይለቀቃሉ። ህዝቡ የአራቱ ሰዎች መለቀቅ እየተጠባበቀ ይገኛል። ፖሊሶቹ ተለቀዋል፤ አራቱ ገብሬዎች እስኪፈቱ ድረስ ግን እዛው ይቆያሉ። መከላከያ ሰራዊት ጥሪ ቢቀርብላቸውም እስካሁን ድረስ (እስከ ምሽቱ 1:30) ባከባቢው አልደረሱም።

የአፅቢ ግጭት (ክፍል አራት) 

ድርድሩ አልተሳካም፡ ተኩስ ተከፍቷል ህዝብ እየተደበደበ ነው

ፖሊሶች አራት የኗሪዎቹ ተወካዮች በሃይል ሲወስዱ የአፅቢ ህዝብም አስራ አራት ፖሊሶችና አንድ ምልሻ አግተው ነበር። ህዝቡ ፖሊሶቹ እንዲለቅ አስተዳደሩ ደግሞ አራቱ ተወካዮች እንዲለቅ ድርድር ተጀምሮ ነበር። በድርድሩ መሃል የወረዳው አስተዳደር አዲስ ሃይል በመጥራት (ከሌላ ወረዳና ከክልል አስተዳደር የፀጥታ ሃይሎች በመላክ) ህዝብ በተሰበሰበብት መተኮስ ጀመሩ (ከምሽቱ 2:30-2:56)።ምልሻዎቹና ወታደሮቹ የታገቱትን ፖሊሶች ለማስለቀቅ እስከ ሁለት መቶ (በኗሪዎቹ ግምት መሰረት) የሚደርስ ጥይት በመተኮስ የታገቱት ፖሊሶችን ማስለቀቅ ችለዋል። እስከ ሁለት ሺ የሚጠጋ ህዝብ ተሰብስቦ እየጨኸ ይገኛል። አሁን (ከምሽቱ ሦስት ሰዓት) ብዙ ምልሻዎች የጫኑ ብዙ መኪኖች ወደ አከባቢው እየገቡ ነው። በሌላ አቅጣጫ (በስተ ሰሜን በኩል) ደግሞ ሌሎች ብዙ መኪኖች እየገቡ ነው (ምልሻ  ወይ ፖሊስ ወይ ወታደሮች መሆናቸው ግን በትክክል አይታወቁም)። ህዝብ በዱላ መደብደብ ጀምረዋል። ህዝቡ እየጮኸና ፈጣሪው እየለመነ ነው። የህዝቡ ጩኸትና ለቅሶ በስልክ መስማት ችያለሁ። እያናግሩኝ ያሉ ሰዎችም መረጋጋት ተስኗቸዋል። አሁን ከምሽቱ 3:05 ሁነዋል። 

የ አፅቢ ግጭት (ክፍል አምስት)

ተኩሱ ቆሟል፣ ምልሻዎቹ ለሁለት ተከፍሏል፣ወታደሮች ገብተዋል

ታግተው የነበሩ የመንግስት ፖሊሶች ሌሎች ፖሊሶችና ምልሻዎች በከፈቱት ተኩስ ተለቀዋል። አሁን ህዝቡና የመንግስት ምልሻዎች 
በሜትሮች ርቀት ተለያይተው ማዶ ለማዶ ይተያያሉ። የአፅቢ ወንበርታ ተወላጆች የሆኑ የመንግስት ምልሻዎች የመንግስት አካላትን ከድተው ከህዝቡ ጎን ተሰልፈዋል (ከአንድ ምልሻ በስተቀር ሁሉም የአፅቢ ወንበርታ ምልሻዎች ከህዝቡ ጎን ይገኛሉ)። ሁለቱም ምልሻዎች (የአፅቢ ወንበርታና አስተዳደሩ ከሌላ ወረዳ ያስመጣቸው) ተፋጠዋል። አሁን 3: 15 በደራ ጣብያ ገብረኪዳን ልዩ ስሙ “አፅገበት” የሚባል ቦታ የነበሩ ወታደሮች (መከላከያ ሰራዊት) ባከባቢው ደርሰዋል። እስካሁን ምንም ዓይነት እርምጃ አልጀመሩም። ፀጥታ ሰፍነዋል።ህዝቡ ግን እንደተሰበሰበ አለ። “ተወካዮቻችን ፍቱልን” እያለ ይገኛል። አሁን ከምሽቱ 3:24 ነው። 

 የአፅቢ ግጭት (ክፍል ስድስት) 

ወታደሮቹ ህዝብ እንዲበተን ጥሪ አቀረቡ

በሰባት መኪኖች ሙሉ ተጭነው ወታደሮች ገብተው አከባቢው ተቆጣጥረውታል። “የዞን አስተዳዳሪዎች ነን” ያሉ ባለስልጣናት ህዝቡ “የአሸባሪነት ተግባር” እያከናወነ መሆኑ በርቀት ተናግረዋል። ህዝቡም “አሸባሪዎች እናንተ ናች ሁ፤ ልጆቻችን ፍቱልን” እያለ ሲጮህ ነበር። በመጨረሻም ወታደሮቹ ህዝቡ እንዲበተን ማስጠንቀቅያ ቢሰጡም አራቱ የአፅቢ ወንበርታ ልጆች ካልተፈቱ እንደማይበተን አስታውቀዋል። መከላከያውና አስተዳዳሪዎቹ ቢያስፈራሩም ህዝቡ ግን ለመበተን ፍቃደኛ አልሆነም። ዘጋቢዎቼ ወደ ቤታቸው እየተንቀሳቀሱ ነው። ነገ እንገናኝ። አሁን ከምሽቱ 3:55 ነው። ቸር ያሰማን።

No comments:

Post a Comment