Tuesday, January 21, 2014

እጁን በብረት ቀጥቅጠው የሰበሩት ኢትዮጵያዊ ስደተኛ

በግሩም ተ/ሀይማኖት ሰነዓ ቁጭ ብዬ የሰዎችን ስቃይ ከመስማት በዘለለ ምንም ልፈይድ አለመቻሌ ሁሌም ይሰማኛል፡፡ አሁን አሁን ደግሞ በየጊዜው ከጅቡቲ፣ ከሶማሊያ በባህር ተሻግረው ወደ የመን የሚገቡትን በብዙ ሺህ የሚቆጠሩ ኢትዮጵያዊያን ስደተኞች እንደ በፊቱ ባይበዛም ይመጣሉ፡፡ በፊት ይዘው ሳዩዋቸው የነበሩት አፋኞችም፡፡ ስራቸውን በተጠናከረ መልኩ ተያይዘውታል፡፡ አፍነው እያሰቃዩ ገንዘብ አስልኩ ማለቱን ቀጥለዋል፡፡ እዚህ ቪዲዮ ላይ የሚታየውም እዛ ጉዳት የደረሰበት ሰው ነው፡፡ ብህሩን ከተሸገሩ በኋላ ወደ ሳዑዲ ጉዞው የማይሆን ሲሆን ወደ ሰነዓ ይገባሉ፡፡ ታዲያ የየመን መንግስት እስረኛ ስለበዛበት በቦታ እና አቅም ማነስ ምክንያት ቶሎ አይቀበሏቸውም፡፡ በዚህ ጊዜእስር ቤቱ ጊቢ በር ላይ ይተኛሉ፡፡ ብርዱ፣ ርገቡ፣ መጸዳጃ ቦታ ማጣቱና ልብስ የሌላቸው መሆኑ አንገብገቢ ችግር ሆነ፡፡ የቻልኩትን ያህል ለማድረግ ጥረት ሳደርግ ከጎኔ የተሰለፉ ጥቂት ሰዎች ነበሩ፡፡ አሁን ደግሞ የልጅነት ጓደኛዬ ካሳሁን የሺጥላ የቻለውን ያህል ለመርዳት ከጎኔ ሆኗል፡፡ የኩዌቱ ውዳጄ ነዛር ዳጊም እኔስ ወገኔን በሚል በጎኔ መሰለፉ ቢያስደሰተኝም ሁሌም በስደተኞች ጉዳይ ከኩዌት ድምጹን የሚያሰማ ወዳጄ ነው፡፡ ካሳሁን የሺጥላንም ሆነ ንዛር ዳጊን ከልብ የማመሰግነው በርሃብ ተጠርዘው በብርድ ተቆልተው መንገድ ዳር ወድቀው ባሉ ስደተኛ ወንድምና እህቶቼ ስም ነው፡፡ ይሄንኑ ተልዕኮዬን ለመፈጸም ሰነዓ ኢሚግሬሽን እስር ቤት በረ ላይ ያሉትን ለማጠየቅ በሄድኩበት ጊዜ አንድ ሰው አገኘሁ፡፡ ከዚህ በፊት ተደጋጋሚ እንደዘገብኩት የመን ውስጥ ባሉ ስደተኞችን አፍነው በማሰቃየት ገንዘብ ከቤተሰብ፣ ወዳጅ ዘመድ እንዲያስልኩ የሚያደርጉት ሰዎች እእ ላይ ወደቀ፡፡ ስልክ ቀጥር አምጣና ደውለን እንዲልኩ እናድርግ ብለው ሲየሰቃዩት በብረት ትከሻው ላይ ምን ያህል ጉዳት እነንዳደረሱበት እያሳየኝ ነው፡፡ የሚያሳዝነው ግን ይህን ያደረrገው ኢትዮጵያዊ የአፋኞቹ ተቀጣሪ እንደሆነ ነው የሚናገረው፡: ሺዲዮውን ይመልከቱ

No comments:

Post a Comment