Friday, January 10, 2014

(ሰበር ዜና) እነ ሌንጮ ለታ ኢትዮጵያ ሊገቡ ነው

Zehabesha Amharic

(በአንድ ወቅት በዘ-ሐበሻ ድረገጽ ወጥቶ የነበረው ሌንጮን እና ፕሮፌስር ይስሃቅን በሚኒያፖሊስ በድርድር ስብሰባ በኋላ የተነሱትን ፎቶ የሚያሳይ ምስል)
(በአንድ ወቅት በዘ-ሐበሻ ድረገጽ ወጥቶ የነበረው ሌንጮን እና ፕሮፌስር ይስሃቅን በሚኒያፖሊስ በድርድር ስብሰባ በኋላ የተነሱትን ፎቶ የሚያሳይ ምስል)

(ዘ-ሐበሻ) “ከእንግዲህ የቀድሞው መንገድ አይሰራም” በሚል የኦሮሞ ዴሞክራሲያዊ ግንባርን የመሰረቱት የቀድሞ የኦነግ አመራሮች እነኦቦ ሌንጮ ለታ ኢትዮጵያ ሊገቡ መሆኑ ተሰማ፡፡
የዘ-ሐበሻ የሚኒያፖሊስ ምንጮች እንዳስታወቁት ከዚህ ቀደም ኦሮሚያ ክልልን ለማስገንጠል ይንቀሳቀሱ ከነበሩ ሃይሎች ጋር የነበሩት እነ ኦቦ ሌንጮ ለታ የኦሮሞ ዲሞክራሲያዊ ግንባርን በሚኒሶታ ከመሰረቱ በኋላ በሃገር ቤት ገብተው ለመታገል መወሰናቸውን አስታውቀዋል።
ከጥቂት አመታት ወዲህ ፕሮፌሰር ኤፍሬም ኢስሃቅ እነ ሌንጮ ለታን ለማስማማት ወደሚኒያፖሊስ ከ2008 ጀምሮ በተደጋጋሚ ሲመላለሱ እንደነበር የዘ-ሐበሻ ምንጮች በፎቶ ግራፍ ጭምር የተደገፈ መረጃ ያቀረቡ ሲሆን “ከ እንግዲህ የቀድሞው መንገድ አይሰራም” የሚል አቋም የያዘው ይኸው የሌንጮ ለታ ግሩፕ የፕሮፌሰር ኤፍሬም ይስሃቅን ምልጃ ተቀብሎ ወደ ኢትዮጵያ በመግባት በቀጣዩ ምርጫ ለመወዳደር እንደሚዘጋጅ የዘ-ሐበሻ ምንጮች ገልጸዋል።
የሌንጮ ለታ የኦሮሞ ዴሞክራሲያዊ ግንባር ወደ ኢትዮጵያ በቅርብ ቀን እንደሚገባ ያስታወቁት እነዚሁ ምንጮች፤ በተለይ በአሁኑ ወቅት በርካታ የኦሮሞ ምሁራን፣ የሰብ አዊ መብት ተከራካሪዎች የመብት ጥያቄ አንስተው በአሸባሪነት በታሰሩበት ወቅት በዴሞክራሲያዊ መንገድ ኢሕ አዴግን እንታገላለን ብለው መወሰናቸው በሚኒሶታ የሚገኙ በርካታ ኦሮሞ ኢትዮጵያውያንን እያነጋገረ እንደሚገኝ በተደጋጋሚ መዘገቡ ይታወሳል።
ለትውስታ እነዚህን ታሪካዊ ፎቶዎች እንጋብዝዎ
olf 2
olf 3
olf 4
olf 5
olf 6
Olf
Ze-Habesha 

No comments:

Post a Comment