Sunday, December 8, 2013

የሀገሪቱ የፍትህ ድብብቆሽ ይህን ይመስላል! ተማሪዎች ‹‹የፍትህ ያለህ!›› እያሉ ነው! በአገሪቱ ፍትህ የለምን?


DECEMBER 8, 2013 
ከ2005 አጋማሽ በኋላ የአወልያ ግቢን መሰረት ያደረገውንና 2004 ታህሳስ ወር የተጀመረውን የህዝበ ሙስሊሙን ተቃውሞ የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች መረከብ እንዳለባቸው የሚያስረዱ ጥሪዎች ከየአቅጣጫው ይሰሙ ጀመር፡፡ ይህ አስፈሪ አቅጣጫ ልቦናው ውስጥ ከፍተኛ ፍርሀት የፈጠረበት የኢህአዴግ መንግስት የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎችን በራሳቸው ጉዳይ (በሰላትና ሂጃብ ጉዳይ) እንዲጨናነከትሎ በጥር ወር 2005 መጀመሪያ በከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ሊኖር የሚገባውን የቁ በማድረግ በህዝበ ሙስሊሙ ተቃውሞ እንዳይሳተፉ ለመግታት ማሰቡን ከአንድ ከፍተኛ የኢህአዴግ ባለስልጣን የወጣ መረጃ አመለከተ፡፡ ይህን ውሳኔ ተአለባበስ፣ አመጋገብና አምልኮ ስነ-ስርአት አስመልክቶ የትምህርት ሚኒስቴር አውጥቶት የነበረውን ኢ-ህገ መንግስታዊ ረቂቅ ደንብ የባህር ዳር ዩኒቨርሲቲ በቀጥታ ተግባራዊ አደረገ፡፡ ይህ ገና በውይይት ላይ የሚገኝ ረቂቅ ደንብ ምንም እንኳ ሁሉንም የሃይማኖት ተከታዮች የሚመለከት ቢመስልም ቅሉ ግን ያነጣጠረው ድሮም በእናት አገሩ ኢትዮጵያ ፍዳውን እያየ በኖረው ሙስሊም ተማሪ ላይ ነበር፡፡ በውስጡም ሂጃብንና ሰላትን የሚገድቡ ህገ ወጥ ኢህአዴጋዊ ሴራዎች የተጎነጎኑበት ነበር፡፡
በሂደትም 13 የባህር ዳር ዩኒቨርሲቲ ኒቃብ ለባሽ እህቶች በይፋ እንዲባረሩ ተደረገ፡፡ የባህር ዳር ዩኒቨርሲቲ ሙስሊም ጀመዓ አጠቃላይ አሚር ተባረረ፡፡ በወቅቱ የተፈጠረውን ውዝግብ ያባብሳሉ ተብለው የሚታሰቡ 12 ሙስሊም ተማሪዎች ማስጠንቀቂያ ተለጠፈላቸው፡፡ በግቢው የጀመአ ሰላት የሚሰገድባቸው ንብረቶች ተዘረፉ፡፡ ኒቃባቸውን አውልቀው እንዲማሩ፣ ወይም ዊዝድሮዋል ሞልተው ወደቤታቸው እንዲሄዱ፣ አለበለዚያ ግን እንደሚባረሩ አስከፊ ምርጫ የተሰጣቸው ሙተነቂብ እህቶች ‹‹አናወልቅም፤ እንማራለን›› በማለታቸው በዩኒቨርሲቲው ፖሊሶችና የተማሪዎቸ የመኝታ አገልግሎት ሀላፊዎች ከነሻንጣቸው እንደባእድ ከግቢው ውጭ ተወረወሩ፡፡ ተሰብስበው ሲሰግዱ የታዩ 28 ሴት ተማሪዎች ማስጠንቀቂያ ተሰጣቸው፡፡ ጭራሽ ‹‹100 ሜትር ተራርቃችሁ መስገድ አለባችሁ›› እስከመባልም ተደረሰ!
የረቂቅ ደንቡን ህገ ወጥነት ከኢትዮጵያ ህገ መንግስት ሀይማኖታዊ ድንጋጌዎች አንጻር፣ ከአለም አቀፍ ህግጋት አኳያ፣ ኢትዮጵያ ‹‹ፈለጋቸውን ተከትያለሁ›› ከምትላቸው ሴኩላር አገራት ተሞክሮ አንጻር፣ እንዲሁም ለሰላትና ሂጃብ ኢስላም ከሚሰጠው ቦታ አንጻር መንግስት ባዘጋጃቸው የተለያዩ ስብሰባዎች ላይ ያስረዳው መላው የዩኒቨርሲቲ ተማሪ (ክርስትያኖችንም ይጨምራል) በባህር ዳር ዩኒቨርሲቲ ህገወጥ እርምጃ ቁጣውን መግለጽ ጀመረ፡፡ ጾም፣ ፔቲሽን፣ የገንዘብና የሞራል ድጋፍ፣ ሌላም ሌላም ተደርጎ በዩኒቨርሲቲው ተቃውሞ ተጧጧፈ፡፡
ቁጥራቸው ከ700 እስከ 1200 የሚደርሱ የባህር ዳር ሙስሊም ተማሪዎች ‹‹ሃይማኖታችን እስትንፋሳችን በመሆኑ ካለሱ መኖር አንችልም!›› በማለት ከትምህርት ገበታቸው ተፈናቅለው ወደየቤታቸው ተመለሱ፡፡ የዚህ ሁሉ የተማረ ሀይል ትምህርት መስተጓጎል ያላሳሰበው የዩኒቨርሲቲው አስተዳደር (መንግስት) ‹‹ሰላት ኦክስጅናችን ነው ብለዋል፤ እስቲ ይሞቱ ከሆነ እናያለን!›› ብሎ ከማሾፍ አንስቶ ተመልሰው ትምህርታቸውን የማይቀጥሉ ከሆነ ለተፈጠረው ችግር ሀላፊነቱን እንደማይወስድ፣ ‹‹አንዳንድ የዩኒቨርሲቲው ተማሪዎች ዩኒቨርሲቲው ተማሪዎችን ለማስተዳደር ያወጣውን ደንብ አንቀበልም በማለት ትምህርት ማቋረጣቸው ይታወቃል›› የሚል የተጻፈበትን ዛቻ አዘል ማስታወቂያ በመለጠፍ ድሮም አላማቸው የተማረውን ሙስሊም ወጣት ከትምህርት ማደናቀፍ መሆኑን አሳበቀ፡፡
በዚህ ክስተት ማግስት ነው እንግዲህ የተማሪዎች እስር የተጀመረው፡፡ መንግስት በየዩኒቨርሲቲዎች ይህንን ተቃውሞ (የህዝበ ሙስሊሙንም የተማሪውንም) ‹‹እያቀጣጠሉብኝ ነው›› ብሎ ያሰባቸውን 17 የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎችና አንድ ሌክቸረር ከየዩኒቨርሲቲው በመልቀም የግፍ ማእከሉ በሆነው የፌደራል ፖሊስ ወንጀል ምርመራ ዘርፍ (ማእከላዊ) በየተራ አጎራቸው፡፡ በምርመራው ሂደትም ‹‹ፖሊስ›› ተማሪዎቹን ‹‹ሁሉንም የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ከትምህርት ገበታቸው በማፈናቀል የጎዳና ላይ ነውጥ ለማስነሳት ያለሙ ናቸው፤ ምናልባትም ከግብጽና ሳኡዲ መንግስት ጋር ግንኙነት ሳይኖራቸው አይቀርም፤ ግብረ አበሮቻቸው ከኢትዮጵያ የወጡ በመሆኑ መንግስት ከጎረቤት አገሮች ጋር ተነጋግሮ ለመያዝ በውይይት ላይ ነው፤ የቴክኒክ ማስረጃዎችን እያሰባሰብን ነው፤ ሂደታቸው በፍርድ ቤት እየታየላቸው ያሉትን የህዝበ ሙስሊሙ መፍትሄ አፈላላጊ ኮሚቴዎች ራእይና አላማ ለማስቀጠል ሲንቀሳቀሱና ተማሪውን ለሁከት ሲያነሳሱ የነበሩ ናቸው፤ ተማሪዎችን ለጂሀድ ጦርነት ሲያዘጋጁ ነበር…›› ወዘተ በማለት ቀኑን ሙሉ ያለከልካይ በሚፈነጭበት አራዳ ፍርድ ቤት በሽብርተኝነት ከሶ ለአራት ወራት ሲያመላልሳቸው ቆይቷል፡፡
ከአራት ወራት የምርመራ ቆይታ በኋላ አምስቱ (4 ወንድ 1 ሴት) ተለቀው 13ቱ ደግሞ (12 ወንድና 1 ሴት) በፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት 4ኛ ወንጀል ችሎት የሽብርተኝነቱን አንቀጽ በመቀየር የወንጀል ህጉን አንቀጽ 32/1/ሀ፣ 38/1 እና 257/ሀ ተላልፈዋል በማለት ከሷቸዋል፡፡ እንግዲህ ልጆቹ ሽብርተኛ ሳይሆኑ ነው ያን ያህል ካንገላቷቸው በኋላ የሽብርተኝነት ክሱን የተዉት! አዲሱ ክሳቸው በጥቅሉ ‹‹የትምህርት ሚኒስቴርን ረቂቅ ደንብ ተግባራዊነት አደናቅፈዋል፤ ራሳቸውን የህዝበ ሙስሊሙ መፍትሄ አፈላላጊ ኮሚቴ በማለት የሰየሙትን ግለሰቦች በሃይል ለማስፈታት ተንቀሳቅሰዋል›› የሚል ሆነ፡፡
በሂደት 4ኛ ወንጀል ችሎት ይህንን ጉዳይ የማየት ስልጣን የሌለው መሆኑን ገልጾ በ14ኛ ወንጀል ችሎት በአንድ ዳኛ ብቻ እንዲታይ ተደረገ፡፡ ተማሪዎቹም እንደህግ የተከሰሱበት አንቀጽ ዋስትና የማያስከለክል በመሆኑ የዋስ መብታቸው ተፈቅዶ ጉዳያቸውን በውጪ እንዲከታተሉ ፍርድ ቤቱን ጠየቁ፡፡ እጅግ የሚገርሙ ትርኪ ምርኪ ምክንያቶችን በመደርደር ፍርድ ቤቱ የዋስትና መብታቸውን ለመወሰን ብቻ 15 የሚደርሱ ቀጠሮዎችን ሰጥቷል፡፡ በምሳሌነት ብናይ፡-
*ሰኔ 10-10-2005 ‹‹የክስ መቃወሚያ እንስማ›› በሚል ለዋስትና ሌላ ቀጠሮ ተሰጠ፤
*ሰኔ 17-10-2005 ‹‹አልደረሰልንም፤ ምን የሚያጣድፍ ነገር አለ?›› ተባለ፤
*ሰኔ 19-10-2005 ‹‹አልደረሰልንም፤ ሌላ ሪፈር የምናደርገው ነገር አለ›› ተባለ፤ (የአለቆቹን እነ ዶክተር ሽፈራው ተክለማርያምን ተጽእኖ ሪፈር ለማድረግ ይሆን?)
*በሌላ ቀጠሮ ደግሞ ‹‹በቃ በሚቀጥለው ሳምንት ቁርጣችሁን እናሳውቃችኋለን›› ተብሎ ተቀጠረ፤
*ሐምሌ 05-11-2005 ‹‹ከምስክር ጋር አብረን እናየዋለን›› ተባለ፤
በዚህ መልኩ ብዙ እንዲመላለሱ ከተደረገ በኋላ ከ2005 የኢድ ተቃውሞ በኋላ በነበራቸው ቀጠሮ አቃቤ ህግ ‹‹ልጆቹ የተያዙበት እንቅስቃሴ አሁንም በሌሎች መስጂዶችና ከተሞች የቀጠለ በመሆኑ የነሱ መፈታት ተጽእኖ ሊኖረው ስለሚችል የዋስትና መብታቸው ይከልከልልኝ›› ብሎ በጠየቀው መሰረት ፍርድ ቤቱ ‹‹አቃቤ ህግ ያቀረበውን ምክንያት ፍርድ ቤቱ ተቀብሏል፤ የዋስትና መብት ከልክለናል፤ ከፈለጋችሁ ይግባኝ ማለት ትችላላችሁ›› በማለት እጅግ ህገ ወጥ ውሳኔ በመወሰን ምስክር መስማቱን ቀጠለ!
እንግዲህ በዚህ ሂደት ውስጥ እያሉ የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት የወንጀል ህጉን ‹‹የወንጀል ቅጣት አወሳሰን መመሪያ ቅጽ 2/2006›› በሚል አርእስት አሻሽሎ ጥቅምት 1 – 2006 ተግባራዊ አደረገው፡፡ በዚህ መመሪያ መሰረትም በተማሪዎቹ አንቀጽ (257/ሀ) የተከሰሰው ጥፋተኛ ሆኖ ቢገኝ ሊቀጣ የሚችለው ከ 10 ቀን እስከ 10 ወር በሚደርስ እስራት ወይም የጉልበት ስራ መሆኑን ያትታል፡፡ ተማሪዎቹ ደግሞ እስከ 10 ወር እስራት ላይ በማሳለፋቸው የዋስትና መብት መሰጠት አይበዛባቸውም ማለት ነው፡፡
በመሆኑም የዋስትና ይግባኝ ጥያቄያቸው ፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ገብቶ ለጥቅምት 25 እና 26 ቀጠሮ ተሰጠ፡፡ በቀጠሮዎቹም ‹‹ቀድሞውኑ ዋስትና በማያስከለክል አንቀጽ ተከሰው ሳለ መከልከላቸው አግባብነት አልነበረውም፤ የተሰሙት ምስክሮችም በክስ ማመልከቻው ላይ የተጠቀሰውን ጭብጥ ያስረዱ አይደሉም፤ አሁን ደግሞ ወንጀል ግለሰባዊ በመሆኑ አንድ ተከሳሽ ሊጠየቅ የሚገባው ራሱ በሰራው ስራ ብቻ መሆኑ በህግ ተቀምጦ እያለ ውጭ ላይ እየተደረጉ ባሉ እንቅስቃሴዎች ምክንያት ደንበኞቻችን ዋስትና መከልከላቸው ተገቢ አይደለም፤ አሁን ደግሞ ጠቅላይ ፍርድ ቤቱ በዚሁ አመት ባወጣው የቅጣት አወሳሰን መሰረት ጥፋተኛ ሆነው ቢገኙ እንኳ ሊቀጡ ከሚችሉት በላይ ታስረዋል፤ በዚህ ላይ የዩኒቨርሲቲ ተማሪ በመሆናቸው ጉዳያቸውን በውጭ እንዲከታተሉ የዋትና መብታቸው ይከበር›› ሲሉ የተማሪዎቹ ጠበቆች ለፍርድ ቤቱ አስረዱ፡፡ ፍርድ ቤቱም ለአርብ ጥቅምት 29-02-2006 ለውሳኔ ቀጠሮ ሰጠ፡፡
ጥቅምት 29 በጠቅላይ ፍርድ ቤት የተሰራው ድራማ ግን እጅግ የሚደንቅ ነበር፡፡ ፍርድ ቤቱ ‹‹ዛሬ ጠርተናችኋል እንዴ?›› በማለት ነበር ውሳኔውን በግልጽ ለመናገር መወዛገቡን ያሳየው፡፡ በዚያችው አጋጣሚ ከመዝገብ ቤቱ የውስጥ ሰው የተገኘው መረጃ ግን ‹‹የሥር ፍርድ ቤቱን ውሳኔ አጽንቷል›› የሚል ነበር – የከፍተኛ ፍርድ ቤቱን ውሳኔ ለማለት ነው፡፡ ተማሪዎቹ ‹‹የወሰናችሁትን ውሳኔ ከመዝገብ ቤቱ ማረጋገጥ ችለናል፤ ለምን በግልጽ አትነግሩንም?›› በማለት የዳኛውን ከንፈር አደረቁት፡፡ ዳኛው ግን ‹‹አይ… በቃ… ዛሬ ከሰአት አይተነው ውሳኔው ሰኞና ማክሰኞ በጽህፈት ቤት በኩል ይደርሳችኋል›› በማለት ውሳኔው ገለልተኛ አለመሆኑን አሳብቆ አረፈው፡፡
ጠቅላይ ፍርድ ቤቱ ራሱ ያወጣውን መመሪያ ተቃርኖ (ረስቶት ነው እንኳ አንዳይባል በዚሁ አመት ጥቅምት ላይ ያወጣው ነው) ለጭቁኖቹ የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ቦታ የሌለው መሆኑን አሳይቷል፡፡ በጣም የሚገርመው ነገር ግን በዚያው ቀን ከሰአት ውሳኔው ከመዝገብ ቤት እንዲሰወር የተደረገ ከመሆኑም በላይ የውሳኔው ግልባጭም እስካሁን ለተከሳሾች ያልደረሳቸው መሆኑ ነው፡፡
አሁን ተማሪዎቹ ያለባቸው 28 መልካቸውን እንኳ ለይተው የማያውቋቸው የሀሰት ምስክሮች ትርኪ ምርኪ ምስካሬ ቢሆንም ከ20 በላይ ምስክሮች ተሰምተዋል፡፡ የተወሰኑትን አቃቤ ህግ ‹‹የተለየ ነገር አያሰሙልኝም›› በሚል ትቷቸዋል፡፡ አንድ ምስክር ብቻ ቀርቷል፡፡ ለሱ ሲባል ነው እንግዲህ ለህዳር 17-03-2006 ማክሰኞ ከሰአት ፍርድ ቤቱ ቀጠሮ የሰጠው፡፡
የሀገሪቱ የፍትህ ድብብቆሽ ይህን ይመስላል! ተማሪዎች ‹‹የፍትህ ያለህ!›› እያሉ ነው! በአገሪቱ ፍትህ የለምን?
Photo: ፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት የ18ቱን የዩኒቨርሲቲ ሙስሊም ተማሪዎች የዋስትና መብት ክልከላ!
ከ2005 አጋማሽ በኋላ የአወልያ ግቢን መሰረት ያደረገውንና 2004 ታህሳስ ወር የተጀመረውን የህዝበ ሙስሊሙን ተቃውሞ የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች መረከብ እንዳለባቸው የሚያስረዱ ጥሪዎች ከየአቅጣጫው ይሰሙ ጀመር፡፡ ይህ አስፈሪ አቅጣጫ ልቦናው ውስጥ ከፍተኛ ፍርሀት የፈጠረበት የኢህአዴግ መንግስት የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎችን በራሳቸው ጉዳይ (በሰላትና ሂጃብ ጉዳይ) እንዲጨናነቁ በማድረግ በህዝበ ሙስሊሙ ተቃውሞ እንዳይሳተፉ ለመግታት ማሰቡን ከአንድ ከፍተኛ የኢህአዴግ ባለስልጣን የወጣ መረጃ አመለከተ፡፡ ይህን ውሳኔ ተከትሎ በጥር ወር 2005 መጀመሪያ በከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ሊኖር የሚገባውን የአለባበስ፣ አመጋገብና አምልኮ ስነ-ስርአት አስመልክቶ የትምህርት ሚኒስቴር አውጥቶት የነበረውን ኢ-ህገ መንግስታዊ ረቂቅ ደንብ የባህር ዳር ዩኒቨርሲቲ በቀጥታ ተግባራዊ አደረገ፡፡ ይህ ገና በውይይት ላይ የሚገኝ ረቂቅ ደንብ ምንም እንኳ ሁሉንም የሃይማኖት ተከታዮች የሚመለከት ቢመስልም ቅሉ ግን ያነጣጠረው ድሮም በእናት አገሩ ኢትዮጵያ ፍዳውን እያየ በኖረው ሙስሊም ተማሪ ላይ ነበር፡፡ በውስጡም ሂጃብንና ሰላትን የሚገድቡ ህገ ወጥ ኢህአዴጋዊ ሴራዎች የተጎነጎኑበት ነበር፡፡
በሂደትም 13 የባህር ዳር ዩኒቨርሲቲ ኒቃብ ለባሽ እህቶች በይፋ እንዲባረሩ ተደረገ፡፡ የባህር ዳር ዩኒቨርሲቲ ሙስሊም ጀመዓ አጠቃላይ አሚር ተባረረ፡፡ በወቅቱ የተፈጠረውን ውዝግብ ያባብሳሉ ተብለው የሚታሰቡ 12 ሙስሊም ተማሪዎች ማስጠንቀቂያ ተለጠፈላቸው፡፡ በግቢው የጀመአ ሰላት የሚሰገድባቸው ንብረቶች ተዘረፉ፡፡ ኒቃባቸውን አውልቀው እንዲማሩ፣ ወይም ዊዝድሮዋል ሞልተው ወደቤታቸው እንዲሄዱ፣ አለበለዚያ ግን እንደሚባረሩ አስከፊ ምርጫ የተሰጣቸው ሙተነቂብ እህቶች ‹‹አናወልቅም፤ እንማራለን›› በማለታቸው በዩኒቨርሲቲው ፖሊሶችና የተማሪዎቸ የመኝታ አገልግሎት ሀላፊዎች ከነሻንጣቸው እንደባእድ ከግቢው ውጭ ተወረወሩ፡፡ ተሰብስበው ሲሰግዱ የታዩ 28 ሴት ተማሪዎች ማስጠንቀቂያ ተሰጣቸው፡፡ ጭራሽ ‹‹100 ሜትር ተራርቃችሁ መስገድ አለባችሁ›› እስከመባልም ተደረሰ!
የረቂቅ ደንቡን ህገ ወጥነት ከኢትዮጵያ ህገ መንግስት ሀይማኖታዊ ድንጋጌዎች አንጻር፣ ከአለም አቀፍ ህግጋት አኳያ፣ ኢትዮጵያ ‹‹ፈለጋቸውን ተከትያለሁ›› ከምትላቸው ሴኩላር አገራት ተሞክሮ አንጻር፣ እንዲሁም ለሰላትና ሂጃብ ኢስላም ከሚሰጠው ቦታ አንጻር መንግስት ባዘጋጃቸው የተለያዩ ስብሰባዎች ላይ ያስረዳው መላው የዩኒቨርሲቲ ተማሪ (ክርስትያኖችንም ይጨምራል) በባህር ዳር ዩኒቨርሲቲ ህገወጥ እርምጃ ቁጣውን መግለጽ ጀመረ፡፡ ጾም፣ ፔቲሽን፣ የገንዘብና የሞራል ድጋፍ፣ ሌላም ሌላም ተደርጎ በዩኒቨርሲቲው ተቃውሞ ተጧጧፈ፡፡
ቁጥራቸው ከ700 እስከ 1200 የሚደርሱ የባህር ዳር ሙስሊም ተማሪዎች ‹‹ሃይማኖታችን እስትንፋሳችን በመሆኑ ካለሱ መኖር አንችልም!›› በማለት ከትምህርት ገበታቸው ተፈናቅለው ወደየቤታቸው ተመለሱ፡፡ የዚህ ሁሉ የተማረ ሀይል ትምህርት መስተጓጎል ያላሳሰበው የዩኒቨርሲቲው አስተዳደር (መንግስት) ‹‹ሰላት ኦክስጅናችን ነው ብለዋል፤ እስቲ ይሞቱ ከሆነ እናያለን!›› ብሎ ከማሾፍ አንስቶ ተመልሰው ትምህርታቸውን የማይቀጥሉ ከሆነ ለተፈጠረው ችግር ሀላፊነቱን እንደማይወስድ፣ ‹‹አንዳንድ የዩኒቨርሲቲው ተማሪዎች ዩኒቨርሲቲው ተማሪዎችን ለማስተዳደር ያወጣውን ደንብ አንቀበልም በማለት ትምህርት ማቋረጣቸው ይታወቃል›› የሚል የተጻፈበትን ዛቻ አዘል ማስታወቂያ በመለጠፍ ድሮም አላማቸው የተማረውን ሙስሊም ወጣት ከትምህርት ማደናቀፍ መሆኑን አሳበቀ፡፡
በዚህ ክስተት ማግስት ነው እንግዲህ የተማሪዎች እስር የተጀመረው፡፡ መንግስት በየዩኒቨርሲቲዎች ይህንን ተቃውሞ (የህዝበ ሙስሊሙንም የተማሪውንም) ‹‹እያቀጣጠሉብኝ ነው›› ብሎ ያሰባቸውን 17 የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎችና አንድ ሌክቸረር ከየዩኒቨርሲቲው በመልቀም የግፍ ማእከሉ በሆነው የፌደራል ፖሊስ ወንጀል ምርመራ ዘርፍ (ማእከላዊ) በየተራ አጎራቸው፡፡ በምርመራው ሂደትም ‹‹ፖሊስ›› ተማሪዎቹን ‹‹ሁሉንም የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ከትምህርት ገበታቸው በማፈናቀል የጎዳና ላይ ነውጥ ለማስነሳት ያለሙ ናቸው፤ ምናልባትም ከግብጽና ሳኡዲ መንግስት ጋር ግንኙነት ሳይኖራቸው አይቀርም፤ ግብረ አበሮቻቸው ከኢትዮጵያ የወጡ በመሆኑ መንግስት ከጎረቤት አገሮች ጋር ተነጋግሮ ለመያዝ በውይይት ላይ ነው፤ የቴክኒክ ማስረጃዎችን እያሰባሰብን ነው፤ ሂደታቸው በፍርድ ቤት እየታየላቸው ያሉትን የህዝበ ሙስሊሙ መፍትሄ አፈላላጊ ኮሚቴዎች ራእይና አላማ ለማስቀጠል ሲንቀሳቀሱና ተማሪውን ለሁከት ሲያነሳሱ የነበሩ ናቸው፤ ተማሪዎችን ለጂሀድ ጦርነት ሲያዘጋጁ ነበር…›› ወዘተ በማለት ቀኑን ሙሉ ያለከልካይ በሚፈነጭበት አራዳ ፍርድ ቤት በሽብርተኝነት ከሶ ለአራት ወራት ሲያመላልሳቸው ቆይቷል፡፡
ከአራት ወራት የምርመራ ቆይታ በኋላ አምስቱ (4 ወንድ 1 ሴት) ተለቀው 13ቱ ደግሞ (12 ወንድና 1 ሴት) በፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት 4ኛ ወንጀል ችሎት የሽብርተኝነቱን አንቀጽ በመቀየር የወንጀል ህጉን አንቀጽ 32/1/ሀ፣ 38/1 እና 257/ሀ ተላልፈዋል በማለት ከሷቸዋል፡፡ እንግዲህ ልጆቹ ሽብርተኛ ሳይሆኑ ነው ያን ያህል ካንገላቷቸው በኋላ የሽብርተኝነት ክሱን የተዉት! አዲሱ ክሳቸው በጥቅሉ ‹‹የትምህርት ሚኒስቴርን ረቂቅ ደንብ ተግባራዊነት አደናቅፈዋል፤ ራሳቸውን የህዝበ ሙስሊሙ መፍትሄ አፈላላጊ ኮሚቴ በማለት የሰየሙትን ግለሰቦች በሃይል ለማስፈታት ተንቀሳቅሰዋል›› የሚል ሆነ፡፡
በሂደት 4ኛ ወንጀል ችሎት ይህንን ጉዳይ የማየት ስልጣን የሌለው መሆኑን ገልጾ በ14ኛ ወንጀል ችሎት በአንድ ዳኛ ብቻ እንዲታይ ተደረገ፡፡ ተማሪዎቹም እንደህግ የተከሰሱበት አንቀጽ ዋስትና የማያስከለክል በመሆኑ የዋስ መብታቸው ተፈቅዶ ጉዳያቸውን በውጪ እንዲከታተሉ ፍርድ ቤቱን ጠየቁ፡፡ እጅግ የሚገርሙ ትርኪ ምርኪ ምክንያቶችን በመደርደር ፍርድ ቤቱ የዋስትና መብታቸውን ለመወሰን ብቻ 15 የሚደርሱ ቀጠሮዎችን ሰጥቷል፡፡ በምሳሌነት ብናይ፡-
*ሰኔ 10-10-2005 ‹‹የክስ መቃወሚያ እንስማ›› በሚል ለዋስትና ሌላ ቀጠሮ ተሰጠ፤
*ሰኔ 17-10-2005 ‹‹አልደረሰልንም፤ ምን የሚያጣድፍ ነገር አለ?›› ተባለ፤
*ሰኔ 19-10-2005 ‹‹አልደረሰልንም፤ ሌላ ሪፈር የምናደርገው ነገር አለ›› ተባለ፤ (የአለቆቹን እነ ዶክተር ሽፈራው ተክለማርያምን ተጽእኖ ሪፈር ለማድረግ ይሆን?)
*በሌላ ቀጠሮ ደግሞ ‹‹በቃ በሚቀጥለው ሳምንት ቁርጣችሁን እናሳውቃችኋለን›› ተብሎ ተቀጠረ፤
*ሐምሌ 05-11-2005 ‹‹ከምስክር ጋር አብረን እናየዋለን›› ተባለ፤
በዚህ መልኩ ብዙ እንዲመላለሱ ከተደረገ በኋላ ከ2005 የኢድ ተቃውሞ በኋላ በነበራቸው ቀጠሮ አቃቤ ህግ ‹‹ልጆቹ የተያዙበት እንቅስቃሴ አሁንም በሌሎች መስጂዶችና ከተሞች የቀጠለ በመሆኑ የነሱ መፈታት ተጽእኖ ሊኖረው ስለሚችል የዋስትና መብታቸው ይከልከልልኝ›› ብሎ በጠየቀው መሰረት ፍርድ ቤቱ ‹‹አቃቤ ህግ ያቀረበውን ምክንያት ፍርድ ቤቱ ተቀብሏል፤ የዋስትና መብት ከልክለናል፤ ከፈለጋችሁ ይግባኝ ማለት ትችላላችሁ›› በማለት እጅግ ህገ ወጥ ውሳኔ በመወሰን ምስክር መስማቱን ቀጠለ!
እንግዲህ በዚህ ሂደት ውስጥ እያሉ የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት የወንጀል ህጉን ‹‹የወንጀል ቅጣት አወሳሰን መመሪያ ቅጽ 2/2006›› በሚል አርእስት አሻሽሎ ጥቅምት 1 – 2006 ተግባራዊ አደረገው፡፡ በዚህ መመሪያ መሰረትም በተማሪዎቹ አንቀጽ (257/ሀ) የተከሰሰው ጥፋተኛ ሆኖ ቢገኝ ሊቀጣ የሚችለው ከ 10 ቀን እስከ 10 ወር በሚደርስ እስራት ወይም የጉልበት ስራ መሆኑን ያትታል፡፡ ተማሪዎቹ ደግሞ እስከ 10 ወር እስራት ላይ በማሳለፋቸው የዋስትና መብት መሰጠት አይበዛባቸውም ማለት ነው፡፡
በመሆኑም የዋስትና ይግባኝ ጥያቄያቸው ፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ገብቶ ለጥቅምት 25 እና 26 ቀጠሮ ተሰጠ፡፡ በቀጠሮዎቹም ‹‹ቀድሞውኑ ዋስትና በማያስከለክል አንቀጽ ተከሰው ሳለ መከልከላቸው አግባብነት አልነበረውም፤ የተሰሙት ምስክሮችም በክስ ማመልከቻው ላይ የተጠቀሰውን ጭብጥ ያስረዱ አይደሉም፤ አሁን ደግሞ ወንጀል ግለሰባዊ በመሆኑ አንድ ተከሳሽ ሊጠየቅ የሚገባው ራሱ በሰራው ስራ ብቻ መሆኑ በህግ ተቀምጦ እያለ ውጭ ላይ እየተደረጉ ባሉ እንቅስቃሴዎች ምክንያት ደንበኞቻችን ዋስትና መከልከላቸው ተገቢ አይደለም፤ አሁን ደግሞ ጠቅላይ ፍርድ ቤቱ በዚሁ አመት ባወጣው የቅጣት አወሳሰን መሰረት ጥፋተኛ ሆነው ቢገኙ እንኳ ሊቀጡ ከሚችሉት በላይ ታስረዋል፤ በዚህ ላይ የዩኒቨርሲቲ ተማሪ በመሆናቸው ጉዳያቸውን በውጭ እንዲከታተሉ የዋትና መብታቸው ይከበር›› ሲሉ የተማሪዎቹ ጠበቆች ለፍርድ ቤቱ አስረዱ፡፡ ፍርድ ቤቱም ለአርብ ጥቅምት 29-02-2006 ለውሳኔ ቀጠሮ ሰጠ፡፡
ጥቅምት 29 በጠቅላይ ፍርድ ቤት የተሰራው ድራማ ግን እጅግ የሚደንቅ ነበር፡፡ ፍርድ ቤቱ ‹‹ዛሬ ጠርተናችኋል እንዴ?›› በማለት ነበር ውሳኔውን በግልጽ ለመናገር መወዛገቡን ያሳየው፡፡ በዚያችው አጋጣሚ ከመዝገብ ቤቱ የውስጥ ሰው የተገኘው መረጃ ግን ‹‹የሥር ፍርድ ቤቱን ውሳኔ አጽንቷል›› የሚል ነበር – የከፍተኛ ፍርድ ቤቱን ውሳኔ ለማለት ነው፡፡ ተማሪዎቹ ‹‹የወሰናችሁትን ውሳኔ ከመዝገብ ቤቱ ማረጋገጥ ችለናል፤ ለምን በግልጽ አትነግሩንም?›› በማለት የዳኛውን ከንፈር አደረቁት፡፡ ዳኛው ግን ‹‹አይ… በቃ… ዛሬ ከሰአት አይተነው ውሳኔው ሰኞና ማክሰኞ በጽህፈት ቤት በኩል ይደርሳችኋል›› በማለት ውሳኔው ገለልተኛ አለመሆኑን አሳብቆ አረፈው፡፡
ጠቅላይ ፍርድ ቤቱ ራሱ ያወጣውን መመሪያ ተቃርኖ (ረስቶት ነው እንኳ አንዳይባል በዚሁ አመት ጥቅምት ላይ ያወጣው ነው) ለጭቁኖቹ የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ቦታ የሌለው መሆኑን አሳይቷል፡፡ በጣም የሚገርመው ነገር ግን በዚያው ቀን ከሰአት ውሳኔው ከመዝገብ ቤት እንዲሰወር የተደረገ ከመሆኑም በላይ የውሳኔው ግልባጭም እስካሁን ለተከሳሾች ያልደረሳቸው መሆኑ ነው፡፡
አሁን ተማሪዎቹ ያለባቸው 28 መልካቸውን እንኳ ለይተው የማያውቋቸው የሀሰት ምስክሮች ትርኪ ምርኪ ምስካሬ ቢሆንም ከ20 በላይ ምስክሮች ተሰምተዋል፡፡ የተወሰኑትን አቃቤ ህግ ‹‹የተለየ ነገር አያሰሙልኝም›› በሚል ትቷቸዋል፡፡ አንድ ምስክር ብቻ ቀርቷል፡፡ ለሱ ሲባል ነው እንግዲህ ለህዳር 17-03-2006 ማክሰኞ ከሰአት ፍርድ ቤቱ ቀጠሮ የሰጠው፡፡

No comments:

Post a Comment