Tuesday, December 24, 2013

Photo: በጋዜጠኛርዕዮት አለሙ ጉዳይ… የፍርድ ብይኑ ለዳኛው በጽሁፍ እንደተሰጠው ተጋለጠ!!
December 22/2013

EMF=ርዕዮት አለሙ ጋዜጠኛ ናት። ሆኖም የኢህአዴግ ስርአት ወጣቷን ጋዜጠኛ “አሸባሪ” በማለት ክስ ከመሰረቱባት በኋላ፤ የ14 አመት እስራት ፈርደውባታል። ይህ ብይን እንደተሰጠ… የፖለቲካ ውሳኔ እንጂ የዳኞች ውሳኔ እንዳልሆነ ውስጥ ውስጡን ሲወራ ነበር። ይህ ወሬ እውነት መሆኑን የሚያረጋግጡ መረጃዎች እየተገኙ መሆናቸውን በተለይ የቤተሰብ ምንጮች ገልጸዋል።

qqየጋዜጠኛ ርዕዮት አለሙ ታናሽ እህት እንዳሳወቀችው ከሆነ፡ “በዚህ ሂደት ያገኘኋቸው ሁለት ማስረጃዎች አሉ፡፡ አንደኛው በዳኛው የተነበበው የጥፋተኝነት ውሳኔ የእጅ ጽሁፍ ሲሆን ሁለተኛው የዳኛው የእጅ ጽሁፍ ናቸው፡፡ እነዚህ ሁለት ማስረጃዎች በእርግጥም የጥፋተኝነት ውሳኔው በዳኛው እንዳልተጻፈ የሚያረጋግጡ ሆነው አግኝቻቸዋለሁ” ብላለች።

አሁን ብዙዎችን እያነጋገረ ያለው፤ “ከችሎቱ ጀርባ ያለው ድብቅ ዳኛ ማነው?” የሚለው ይሆናል። ይህ በ’ጅ ጽሁፍ ተጽፎ የተሰጠ ብይን የማን እጅ ጽሁፍ ይሆን? ጋዜጠኛ ርዕዮት አለሙ ላይ ብይን በተሰጠበት ወቅት፤ አቶ መለስ በህይወት ነበሩ… የሳቸው ይሆን? ወይንስ የሽመልስ ከማል እጅ ጽሁፍ ነው?

ህዝቡ በዚህ ጉዳይ የራሱን ትዝብት እንዲወስድ፤ በተለይም የፍርድ ውሳኔው ጸሃፊው ማን እንደነበር ለማወቅ ይህ ደብዳቤ ይፋ ይሆናል። ይህ መረጃ ለህዝብ ይፋ የሚሆነው ጋዜጠኛ ርዕዮት የታሰረችበት 30ኛ ወር በታስቦ በሚልበት፤ ታህሳስ 14 2006 ዓ.ም መሆኑ ታውቋል
በጋዜጠኛርዕዮት አለሙ ጉዳይ… የፍርድ ብይኑ ለዳኛው በጽሁፍ እንደተሰጠው ተጋለጠ!!
December 22/2013

EMF=ርዕዮት አለሙ ጋዜጠኛ ናት። ሆኖም የኢህአዴግ ስርአት ወጣቷን ጋዜጠኛ “አሸባሪ” በማለት ክስ ከመሰረቱባት በኋላ፤ የ14 አመት እስራት ፈርደውባታል። ይህ ብይን እንደተሰጠ… የፖለቲካ ውሳኔ እንጂ የዳኞች ውሳኔ እንዳልሆነ ውስጥ ውስጡን ሲወራ ነበር። ይህ ወሬ እውነት መሆኑን የሚያረጋግጡ መረጃዎች እየተገኙ መሆናቸውን በተለይ የቤተሰብ ምንጮች ገልጸዋል።

የጋዜጠኛ ርዕዮት አለሙ ታናሽ እህት እንዳሳወቀችው ከሆነ፡ “በዚህ ሂደት ያገኘኋቸው ሁለት ማስረጃዎች አሉ፡፡ አንደኛው በዳኛው የተነበበው የጥፋተኝነት ውሳኔ የእጅ ጽሁፍ ሲሆን ሁለተኛው የዳኛው የእጅ ጽሁፍ ናቸው፡፡ እነዚህ ሁለት ማስረጃዎች በእርግጥም የጥፋተኝነት ውሳኔው በዳኛው እንዳልተጻፈ የሚያረጋግጡ ሆነው አግኝቻቸዋለሁ” ብላለች።

አሁን ብዙዎችን እያነጋገረ ያለው፤ “ከችሎቱ ጀርባ ያለው ድብቅ ዳኛ ማነው?” የሚለው ይሆናል። ይህ በ’ጅ ጽሁፍ ተጽፎ የተሰጠ ብይን የማን እጅ ጽሁፍ ይሆን? ጋዜጠኛ ርዕዮት አለሙ ላይ ብይን በተሰጠበት ወቅት፤ አቶ መለስ በህይወት ነበሩ… የሳቸው ይሆን? ወይንስ የሽመልስ ከማል እጅ ጽሁፍ ነው?

ህዝቡ በዚህ ጉዳይ የራሱን ትዝብት እንዲወስድ፤ በተለይም የፍርድ ውሳኔው ጸሃፊው ማን እንደነበር ለማወቅ ይህ ደብዳቤ ይፋ ይሆናል። ይህ መረጃ ለህዝብ ይፋ የሚሆነው ጋዜጠኛ ርዕዮት የታሰረችበት 30ኛ ወር በታስቦ በሚልበት፤ ታህሳስ 14 2006 ዓ.ም መሆኑ ታውቋል

No comments:

Post a Comment