Tuesday, December 24, 2013

....ተው ኀይለመለስ ተው ! እረተው አማራ መሳይ ተው ! ወዲያ ነው ድንበሩ ኋላ እንዳታሰኘን እነማን ነበሩ ! የመሐሉ ዳር ሊሆን ነው ሀገሩ! …… ተው! ተው! ተው! በለው!

በአንድ ወቅት የመለስ ውርስ እና ራዕይ! በሶሊያና ሽመልስ
“የእርሳቸው ራእይ አሳኪዎች ሊያነሱዋቸው የሚችሉዋቸው ነገሮች ከምስላቸው ጀርባ ያለው የህዳሴው ግድብ ፕሮጀክት እና የባቡር መስመር ዝርጋታው እንዲሁም የመንግስት እቅድ ሆኖ የምናውቀው(ከህልፈታቸው በኋላ ሙሉ ለሙሉ የእርሳቸው እቅድ የሆነው) የእድገት እና ትራንስፎርሜሽን እቅዱ ይመስሉኛል፡፡ከእነዚህ ላይ ከተጨመረ የሚጨመረው መካከለኛ ገቢ ካላቸው ሃገሮች ተርታ እንድንመደብ ያደረጉት ጥረት እየተባለ የሚወራው አወዛጋቢውን የኢኮኖሚ እድገት የማስቀጠል ወሬ ነው፡፡ እነዚህ የመንግስትን ፕሮጄክት እና የግለሰብን ራእይ ማቀላቀል ጉዳዩች ወደጎን ትተን ብናስበው እንኳን ማንኛውም በጠቅላይ ሚኒስትርነት ቦታ የተቀመጠ መሪ ሊያደርግ የሚገባውን የመንግስትን ስራ የመምራት የማቀድ እና የማስፈጸም ስራ እንደ ራእይ ማሰቡ አልተዋጠልኝም፡፡
አቶ መለስ ላለፉት 21 አመታት አገዛዛቸውም ቢሆን አገራችን ብለው ጠርተዋት የማያውቋትን ኢትዮጲያን በምግብ ዋስትና ራስን ስለማስቻል በተለያየ ጊዜ ከተናገሩት ውጪ (እርሱም መንግስታዊ ሃላፊነት እንጂ ራእይ ሊሆን አይችልም) ስለወደፊትዋ ኢትዮጲያ የሚታወስ ራእይ ማስቀመጣቸውን እጠራጠራለሁ፡፡”
አቶ መለስ ለ21 አመት አገር እንደመግዛታቸው የሚያስቀሩት ውርስ ያስለመዱት ስርአት የፈጠሩት አካሄድ መኖሩ አይቀሬ ነው፡፡ጥያቄው ውርሳቸውን ምንድነው ማስቀጠሉስ ለማን ይበጃል ውርሱስ ምንድነው የሚለው ነው?
-ቁጣ እና ንቀት -ውርስ 1
-በድን ፓርላማ- ውርስ 2
-የምርጫ ድራማ ውርስ 3
-የወረቀት የመድብለ ፓርቲ ስነ ስርአት-ውርስ 4
-የተሽመደመዱ የህዝብ አገልግሎት ሰጪ ተቋማት-ውርስ 5
-የተቀላቀሉ ፓርቲ እና መንግስት-ውርስ 6
-ሊሞት አንድ ሃሙስ የቀረው የግል ሚዲያ እና ለውሸት ቆርጦ የተነሳ የመንግስት ሚዲያ-ውርስ 7
-ሰብአዊ መብትን የማያወሩ የሲቪል ማህበረሰብ ተቋማት-ውርስ 8
-የፍርሃት ትውልድ-ውርስ 9
-የኑሮ ውድነት እና የከተማ ድህነት-ውርስ 10
-ሀገርን ለባዕድ ዜጋን ወደ ባዕድ ሀገር የማብረር ባሕል-ውረስ 11
-በአንድ የፓለቲካ ጥላ ሥር ተሰብስቦ በባዶ ሆድ ባዶ ሜዳ ላይ መጨፈር-ውርስ 12
-የትውልድ ውርስ ቅርስ ታሪክን ማጥፋት እርስ በእርስ በማጋጨት የሥልጣን ዘመንን ማስቀጠል ውርስ-13
-”በሰጥቶ መቀበል”መርህ ለአጎራባች ሀገራት መሬትና መብራት እየሰጡ ተቃዋሚን ማፈንና መሳሪያ መጫን ውርስ-14
-ሻቢያናህወአት ከኋላ ብሄር ብሄረሰብ ከፊት በብሀየርና ቋንቋን የተቧደነ ህዝብ በሙስና እንጥፍጣፊ መረስርስ ማላሸቅ ውርስ-15
>>>ቀን ከቀን የሚሻሻል የማይመስል ልብ የሚሰብር እና የከፋ የከተማ ድህነት የኑሮ ውድነት፣ የእለትን ጉርስን የማግኘት ትግል፣በደሃውና በሃብታሙ መካከል የሚታይ ከፍተኛ የኑሮ ልዩነትም ቢሆን የአቶ መለስ ውርስ ነው፡፡መጓጓዥ አገልግሎት ችግርን መፍታት ያቃተው አሰራር ትራንስፓርት ማግኘት እድል እንደሆነ የሚቆጠርበት ከተማ ከአቶ መለስ የተረከብናቸው ውርሶቻችን ናቸው፡፡ ራእይ እና ውርስን የማስቀጠል መሃላው ቢለይልን ብናውቀው እና ብንረዳው ቢያንስ ለሚዛናዊነት ይረዳናል፡፡”
*በጠቅላይ ሚ/ር ማዕረግ የህወአትሻቢያ ጉዳይ አስፈፃሚ የብሔር ብሔረሰቦች ሊ/መንበር አቶ ኃይለመለስ አጠናክረው የቀጠሉት የመለስ ራዕይ ‹‹ይህ አሰብን እንይዛለን እንወራለን የሚል አካሄድ ከዚያው ከዘውዳዊው ትምክህታዊ አሥተሳሰብ የሚመነጭ ነው፡፡ ሁለተኛው ደግሞ ይህ አስተሳሰብ የተጠናወታቸው ሰዎች ከዘመነ ግሎባላይዜሽን ጋር አብረው ሊሄዱ ያልቻሉ ከድንጋይ ዘመን አስተሳሰብ ያልተላቀቁ ናቸው የሚለውንም ጨምረው ነው፡፡ ….አቦይ ስብሃት ከሰሞኑ ደግሞ ይለይላችሁ ብለው በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ተገኝተው ‹‹ ኤርትራውያን ከኢትዮጵያውያን በላይ ኢትዮጵያዊ ናቸው !! ›› ከሶስት ወር በፊት በዋሽንግተን ዲሲ የኢህአዴግ ድምጽ በሆነው “ሀገር ፍቅር ሬዲዮ” ቀርበው ሲያስረዱ ” ከትጥቅ ትግል ጀምሮ አሁንም በኢህአዴግ ከፍተኛ አመራር ላይ የሚያገለግሉት ትውልደ ኤርትራውያንና ኤርትራውያን ናቸው እኔም ኤርትራዊ ነኝ ብለዋል(ምንአባክ ታመጣላህ!) ተጨምሮ ተጋኗል።
>> ለመሆኑ (ብአዴን) አማራ ነውን? ወይስ እንዲሁ ትውልደ አማራና አማራ መሳይ ኤረትራውያን ይሆኑ? ለም መሬት ከጎንደር ተቆርሶ ለሱዳን እንዲሰጥ በምክትል ጠ/ሚር ማዕረግ አመራ መሳይ አቶ ደመቀ መኮንን ሁሴን ፈርመዋል የተባለው በእርግጥም አማራ የሚባል ባለሥልጣን ነበር ለማሰኘት መሾምና ማብላት ለዘር ማጥፋቱ ራዕይ መሳካት አስተወፆ አለው። እስቲ ስለ አያሌው ጎበዜም በቅርብ ያሉ ሰዎችና የጠቅላላው የክልሉ ነዋሪዎች ይመስክሩ።”አንዳንዴ እንደ ድመት ፊትን እያጸዱ ከኋላ ያለውን ጉድ መደባበቁ ያስተዛዝበናል!። አዲሱ የአማራ ክልል ፕሬዘዳንት አቶ ገዱ አንዳርጋቸውስ የራይ አስቀጣይ ናቸው ባለራዕይ …እስከዛሮ መን ሠርተዋል?
 ደመቀ መኮንን ሁሴን ሲያስቆርስ ቢላዋ ይስሉ ነበር ?
 ወይንስ ለዕድሜ ዘራፍ ማለት አልደረሱም ነበር ?
 …አረሱት.. አረሱት ይሉናል.. ያውም የእኛን ዕጣ ! 
እነሱ ምን ያድርጉ ኤርትራዊ በዝቶ አማራ ሲታጣ ” 
እኔ ብሆን ብለው ተስለው ነበር!? 
(አቶ ጉድ አድርጋቸው አሳዩልኝ)ተው ኀይለመለስ ተው ! 
እረተው አማራ መሳይ ተው ! 
ወዲያ ነው ድንበሩ ኋላ እንዳታሰኘን እነማን ነበሩ !
የመሐሉ ዳር ሊሆን ነው ሀገሩ!
…… ተው! ተው! ተው! በለው!

No comments:

Post a Comment