Saturday, December 28, 2013

የኦሮሞ ሙስሊሞችን የበላይነትን በኦሮሞ ክርስቲያን ና ኦሮሞ ባልሆኑ ሙስሊሞች ላይ ለመጫን የታለመ ድብቅ አጀንዳ ይፋ ሆነ


ጃዋር ማህመድ የተባለው ግለሰብ ባገኘው መድረክ ላይ ሁሉ በጣም የተሳሳቱ አዘናጊና አግላይ ንግግሮችን በማድረግ ይታወቃል :ባለፈው ወር በሙስሊም ኦሮሞች ስብሰባ ላይ በመገኘት የሰጠውም በጣም አደገኛ አስተያየት ብዙ ሰዎችን አስደንግጥዋል:: ጃዋር በንግግሩ ሙስሊሞች ያለኦሮሞ ነጻነት ሊሳካላቸው እንዳማይችልና የኦሮሞ ድል የ ሙስሊም ድል እንደሆነ ገልጽዋል::ክርስቲያን ኦሮሞዎችን እንዲሁም አማራና እንዲሁም ሌሎች ብሄሮችን ባገለለ መልኩ ጃዋር ጅቡቲ ና ሶማሊ ስላሉ ሙስሊሞች ሲናገር ተደምጥዋል:: የዘር ጉዳይና ሀይማኖት ሲደባለቁ ምን አይነት ችግር እንደሚፈጥሩ ያልተገነዘው ጃዋር በኢትዮጵያ ውስጥ ያለውን የተወሳሰብ የህዝብ ግንኙንት ባላገናዘብ መልኩ በየመድረኩ ላይ የሚሰጣቸው ይተጣመሙና በውሸት ላይ ይተመሰረቱ አስተያየቶች ብዙ ኢትዮጵያውያን እያስቆጣ ይገኛል::
‪ ጃዋር ሞሀመድ የፖለቲካ እብደት “እኔ ባለሁበት 99% ሙስሊም ነው ማንም ሰው ደፍሮ ቀና አይልም ‪#‎በሜንጫ‬ ነው አንገቱን የምንለው ” በአሜሪካ በተደረገ ስብሰባ ላይ ከተናገረው(ሜንጫ የማጭድ ቅርፅ ያለው ረዘም ያለ ባለስለት የቁጥቋጦ መቁረጫ መሳሪያ ነው)
ከሁሉ በባሰ ብዙ ኢትዮፕያውያንን ያስደነገጠው የሀጂ ነጅብ በጃዋር አስተያየት መስማማት ነው:: እንደ ሀጂ ነጅብ አስተያየት ከሆነ 50 ሚሊዮን ሙስሊም እንዳለና 80% ሚሊዮኑ ኦሮሞ እንደሆነ ተናግረዋል:: ይህም ማለት 40 ሚሊዮኑ ኦሮሞ ሙስሊም እንደሆነና ይህም ማለት መቶ በመቶ የኦሮሞ ህዝብ ሙስሊም ነው ማለት ነው:: የኦሮሞ ህዝብ ብዛት 34.4 ሚሊዮን መሆኑ መዘንጋት የለበትም::
ሀጂ ነጅብ በማስከተልም ኦሮሞች ሙስሊሙን ነጻ ማውጣት እንዳለባቸው አስምረውበታል::ይህ በውነቱ በጣም አሳዛኝና ከሙስሊም ትግል ጀርባ ያለውን ኢትዮጵያን እስላማዊ ለማድረግ የታለመውን እቅድ ያሳያል::
የሙስሊምን እንቅስቃሴ በመደገፍ ክርስቲያኖች ያረጉት አስትዋጾኦ ቀላል አይደለም ከ ጳጳስት ጀመሮ የፖለቲካ መሪዎች አክቲቭኢስቶች ጭምር ይህንን ትግል በመደገፍ የበኩላቸውን አስተዋጽኦ አድርገዋል:: ይህንን ያረጉት በኢትዮጵያዊንት መንፈስ እንጂ መስሊም ወይም ኦሮሞ ስለሆኑ አይደለም ::አቶ ነጂብ እንደ ኢትዮጵያ ሙስሊም ተወካይነታቸው ሁሉንም ሙስሊም መወከል ሲኖርባቸው ወደ ዘር በተደራጀና ሀይልን መሰረት ባደረገው የጃዋርና የአክራሪዎች ስብሰባ ላይ ተገኝቶ እናንተ ናቹ ነጻ ምታወጡን ማለት በጣም ሚያሳዝን ነገር ነው::
ጃዋር መሀመድ ሌሎች የኢትዮጵያ ሙስሊሞችን ባገለለ መልኩና የራሱን ዘር ባስቀደመ መልኩ ባድረገው ንግግርን መደገፍ የሙስሊም እንቅስቃሴ ከጀርባው የያዘው ድብቅ አጀንዳ እንዳለ ሚያመላከት ነው::
ጃዋር መሀመድ እስከቅርብ ጊዜ ድረስ ድምጻችን ይሰማ ከሚባለው የሙስሊም የዲያስፖራ እንቅስቃሴ ላይ ከፍተኛ አስተዋጾ ሲያድረግ እንደነበር ይታወቃል:: የጃዋር አጀንዳ የሆነውን የኦሮሞ ሙስሊሞች ስልጣን መያዝ ከመድረክ ጅርባ ይነጋግሩበት እንደነበር ሀጂ ነጅብ አምነዋል:: ኢትዮፕያውንን አብሮ ሚያኖረው የህግ የበላይነት, ዲሞክራሲ, ፍትህና እኩልነት መሆኑ እየታወቀና ኢትዮጵያ የብዙ ሀይማኖቶች ብሄሮች አገር እንደሆነች እየታወቀ በየመድረኩ ላይ እንደዚህ አይነት ሀላፊነት የጎደለውና ዘረኛ አስተያየት መስጠትና ያንንም መደገፍ በጣም ሚያሳዝን ነው::
የነጃዋር አላማ ይፍትህ የበላይነትን በኢትዮጵያ ምድር ለማምጣት አይደለም::አላማቸው ግልጽና ግልጽ ነው:: የኦሮሞ ሙስሊሞችን የበላይነትን በክርስቲያን ና ኦሮሞ ባልሆኑ ሙስሊሞች ላይ ለመጫን ነው::ይህንን ደግሞ በፍጹም ምንቀበለው አይሆንም::ክርስቲያኑ አንድ ነን በሚል መማማል አንድ መሆን እንደማይቻል ሊገነዘበው ይገባል::
source.boletoday.com

No comments:

Post a Comment