Wednesday, January 15, 2014

ኢትዮጵያ በአለም የምግብ እጥረትና ባልተመጣጠነ ምግብ የመጨረሻውን ደረጃ ያዘች


በአለም ላይ የተመጣጠነ ምግብ በማቅረብ፣ በምግብ ዋጋና በጥራት ሆላንድ አንደኛ ሆና ስትመረጥ ፈረንሳይና ስዊዝርላንድ ይከተላሉ። አሜሪካ 21ኛ ደረጃ ስትይዝ ከአንድ እስከ 10 ያሉትን ደረጃዎች የአውሮፓ አገራት ይዘውታል።

የኦክስፋም ጥናት ላለፉት 23 አመታት ኢትዮጵያን በምግብ እራሱዋን እናስችላለን፣ ግብርናው በከፍተኛ ደረጃ እያደገ ነው በማለት ለሚናገረው ለኢትዮጵያ መንግስት ትልቅ መርዶ ነው በማለት አንድ ኢኮኖሚስት ተናግረዋል ። 
ከአፍሪካ አገራት በምግብ አቅርቦትና ጥራት ከኢትዮጵያ በባሰ ሁኔታ ውስጥ መገኘቷ፣ እስከ ዛሬ ድረስ ለግብርናው ዘርፍ የዋለውን ኢንቨስትመንት ጥያቄ ውስጥ የሚከት ብቻ ሳይሆን የገዢውን ፓርቲ ግብርና መር ፖሊሲ ውድቀትን የሚያመላክት መሆኑን አስተያየት ሰጪው ይናገራሉ

የኦክስፋምን ጥናት መነሻ በማድረግ ረዩተርስ እንደዘገበው በምግብ አቅርቦት፣ በምግብ ጥራትና በምግብ ዋጋ ኢትዮጵያ ከ125 አገራት ከቻድ በመቀጠል የመጨረሻውን ደረጃ ይዛለች።



 ኢሳት ዜና :

No comments:

Post a Comment