Sunday, January 19, 2014

ሾልኮ የወጣ የጥምቀት የጭፍጨፋ ድግስ ሚስጥር

by justice4ethiopia
በመጀመርያ ለክርስትና እምነት ተከታዮች እንኳን ለብርሃነ ጥምቀቱ አደረሳችሁ። እንዲያው ይሁን ብዬ እንጂ ጥምቀተ ባህር እንኳን ሙስሊም ጓደኞቻችንም አብረውን ይውሉ እንደነበር አስታውሳለሁ።የጥምቀተ ባህር ፀበል ብቻ ሳይሆን የፍቅር ፀበልም የሚረጭበት  የፍቅር በታ ነው።: በተለይ  ተረ … ተረረረ…. ረረረ የምትል ማንም ከደፈረ የሚጫወታት ሃርሞኒካ ተይዛ ከሚጨፈርበት እነ አብዱና እነ ሙስጠፋስ መች ይጠፉ ነበር። ለጥምቀት ያልሆነ ቀሚስ ይበጣጠስ ብለው ሜዳውን የሚሞሉት ኮረዶች መካከልስ ተቃቅፈው ወይ እጅ ለእጅ ተያይዘው ከሚሄዱት ሃሊማና ሩቅያስ መች ይታጡ ነበር። “ተዋዶ ያለበት እስላም ክርስትያኑ…ተዘነጋሽ እንዴ ኢትዮጵያ መሆኑ”  ያለው ቴዲ ይህን በዐይኑ አይቶ እንጂ ተረት ሰምቶ አይደለም። ደግሞም ነገም ወደፊትም አብረን እንኖራለን የማያኖሩን አይኑሩ! አሜን አላችሁ?
አሁን በኢትዮጵያ ወቅታዊ ጉዳዮች ድህረ ገጽ ላይ ሰውነት የሚያንቀጠቀጥ ዘግናኝ የሆነ ጉዳይ በእንግሊዝኛ ተጽፎ አነበብኩ። በእንግሊዝኛ መጻፉ ብቻ ሳይሆን የመልዕክቱ አስቸኳይነት እጅግ አሳሰበኝ። ለነገ የሞት ድግስ መላምት ካልሆነ አለም ሊያውቀው እኛም ሕዝቡን ልናስጥነቅቅበት የሚገባ መሆን አለበት በሚል ስሜት በድጋሚ አነበብኩት። ከሆነ በሁዋላ ከማዘን የተወራውን ማሳወቅ የታሰበ ነገርም ካለ ተነቃብን እንዲሉ ካልሆነም አስፈላጊ ጥንቃቄ እንዲደረግ ስለሚረዳ መልዕክቱን ማጮህ ይሻላል ብዬ አሰብኩ።
በድህረ ገጹ ላይ የሚነበበው እነዚህ አረመኔዎች ለኢትዮጵያ ሕዝብ ሞት እንደ ጠበል ሊረጩት ተዘጋጅተዋል የሚል መልዕክት ነው። ይህም የሚሆነው ለጥምቀት ለዛሬ  መሆኑ ነው። ባለን አስተማማኝ መረጃ መሰረት ይላሉ የአፍሪካ ቀንድ ዘጋቢዎች (infohorntimes@gmail.com) በሚገባ የሰለጠኑት የትግራይ ተገንጣይ ወንበዴ ቅጥረኞች የሙስሊሞችን አለባበስ ተክነውበት በእለተ ጥምቀት አዲስ አበባን በቦምብ ሊያናውጧት መዘጋጀታቸውን ነው።
እድሜ አብዝቶ ይስጥልንና ለሀገር አሳቢና የሕዝብ አክባሪ የሆኑት አቶ ገብረመድህን አርአያ የትግራይ ተገንጣዮች አከርካሪያቸው ሊሰበር ሲቃረብ ወጣቱን በገፍ ለማፈስ በሀውዜን ላይ ልዩ ቅንብር አዘጋጅተው ወገኖቻችንን  በአውሮፕላን እንዲጨፈጨፉ በማድረግ ፊልም ሲቀርጹና ድጋፍ ሲያሰባስቡ እንደነበረ በአንደበታቸው ነግረውናል። እነዚህ ሰዎች መግደል ማስገደል ዞር በል የማለትን ያህል እንኳን አይከብዳቸውም። ከሞት ያዳኗቸውን ያስገድላሉ የደፈሯቸውን ነብሰ ጡር ወጣት ሴቶች ገድለው ጉድጓድ ይጨምራሉ። አሁን ደግሞ ሌሎች ወገኖች በመላው ኢትዮጵያ የደም ጎርፍ ሊያፈሱ ተዘጋጅተዋል ይሉናል።
“ከፍንዳታው ቀጥለው የሙስሊም ልብስ የለበሱ የግድያ ስልጡኖች በድንጋጤ የሚበታተነውን ሰው በጥይት ይቆሉታል” ብሎ ሚስጥር አሾላኪው ነግሮናል ነው የሚሉት። ቀደም ብሎ ትዕዛዝ የተሰጣቸው ቅጥረኞች ደግሞ ብቀላ በሚመስል መልኩ ከፍንዳታው በሁዋላ በአላባ ቁሊጦ ሁለት መስጊዶችን ዶግአመድ ያደርጋሉ። የዚህ ሁሉ እልቂት ድግስ ምክንያቱ መጪውን ምርጫ ፍራቻ መሆኑም ተሰምቷል። ወሎም የጥቃት ዒላማው ከተነጣጠረባቸው ስፍራዎች ወስጥ ይገኛል። በአርሲና በባሌም እንዲሁ ዘግናኝ ጭፍጨፋን ለማድረግ በመጠባበቅ ላይ የሚገኙ አረመኔዎች መኖራቸው ተጽፏል። በጅጅጋም እንዲሁ ይላል ጽሁፉ ….የሶማሌ ሙስሊሞችን አለባበስ ለብሰው ለጥምቀት እርድ የተዘጋጁ ቅጥረኞች ትዕዛዝ በመጠባበቅ ላይ ናቸው።
የዚህ ሁሉ የክፋት ጥንስስ ዓላማው የትግራይ ተገንጣይ ወንበዴዎች አገር አሸብረው እስከዘላለሙ የኢትዮጵያን ሕዝብ አንበርክከው ለመግዛት የሚያስችላቸው ንድፍ አንደሆነ ነው የሚገለጸው። በዚህም መነሻ ተቃዋሚዎችን ሁሉ አሸባሪ የሚል ስም ለጥፎ ጭፍጨፋና እስር ከዚያም አፈናውን ለመቀጠል መሆኑ ይነገራል።
ይህ የእልቂት ድግስ ሊከሽፍ ይገባዋል። ከወዲሁ ድግሱ በሰፊው ሊነገርና ተጠያቂው ማን እንደሚሆን ሊነገር ይገባል። ሕዝባችንንም መረጃውን ልናደርሰው ይገባናል። ይህንን መረጃ ከውስጥ አዋቂ ተቀብለው ሪፖርቱን አቀናብረው ያቀረቡልንን ተቀማጭነታቸው በደቡብ አፍሪካ የሆኑት አቶ ጌታሁን መኩሪያን አመሰግናለሁ።

1 comment: