Wednesday, December 4, 2013

ሁለተኛው ETV = በእስራኤል ሃገር - // - የኢትዮ-እስራኤላውያን ሮሮ




በእስራኤል ሃገር በአቶ ፋሲል ለገሰ የሚመራው IETV ወይንም ሁለተኛው ETV ሲመሰረት አላማው ኢትዮ-እስራኤሎችን በሙሉ ልቡ ህብረተሰብ ነክ ችግሮችን በማካተት ለህብረተሰቡ ይጠቅማሉ ብሎ ዓላማ ያደረጋቸውን ለምሳሌ፤- እኛ ኢትዮ-እስራኤሎችን እንዴት ከሰለጠነው ህብረተሰብ ጋር ማቀራረብ እንዳለበት እንዲሁም ባህላችንና ቋንቋችን ለ እስራኤል ህብረተሰብ በቀላሉ እንደ ድልድይ ሁኖ ለማገልገል በ እስራኤል መንግስት አመታዊ በጀት ተመድቦለት ጣቢያው አየር ላይ ከዋለ እንሆ ሦስት አመታትን አሳልፏል።

ነገር ግን ዓላማውን ስቶ ለኢትዮጵያ መንግስት ፕሮፖጋንዳነት በማዋል ጭራሽ የኢትዮጵያን አምባሳደር በየሳምንቱ እያቀረበ ስለ ኢትዮጵያ “ግምታዊ” እድገት ስለ አምስት አመቱ ትራንስፎርሜሽን ስለአባይ ግድብ እና ግንቦት 7 የአሸባሪ ቡድን እንደሆነ እነሱን ከቀረብን የኢትዮጵያ መንግስት ለፍርድ እንደሚያቀርበን ፡እንደነዚህ አይነት ገደብ የለሽ ፕሮግራሞች ይቀርቡልናል ። አቶ ፋሲል ለገሰ በመጀመሪያ ይህን አስተሳሰብዎትን መቀየር መቻል ይኖርቦታል። አንድ ህብረተሰብ ወስዶ እንደህፃን ልጅ ዋ.. ብሎ የሚያስፈራሩባት ያሻዎትን የሚያደርጉበት ኢትዮጵያ አይደለችም ። እስራኤል ዲሞክራሲያዊና ፍትሃዊ ሃገር ውስጥ ነው ያለነው፡ ምንም እንኳን የፓርቲው ደጋፊና አቀንቃኝ እንደሆኑ የታወቅ ቢሆንም ጋዜጠኛ በሚለው ሙያ ላይ ጋዜጠኛ ለመባል ከሚያስፈልጉት ነገሮች ውስጥ ትንሾችን ለማድረግ ይሞክሩ።

ስለዚህ እኔ በግሌ የምሰጥዎት አስተያየት ቢኖር ነገሩ ለኢትዮ-እስራኤላውያን በቅቷል ። ይመለሱና ህብረተሰቡን ቃል በገቡበት መሰርት ያገልግሉ አዎ ህብረተሰቡ ከኢትዮጵያ ፖለቲካ አያገባህም ከተባለ እስዎም አያገባዎትም ። ወይንም ለሁሉም የኢትዮጵያ ፖለቲካ ድርጅቶች እና ፓርቲዎች በእኩልነት አገልግሎት ይሰጥ።
 — with አገር ሰላም.

No comments:

Post a Comment