Thursday, December 12, 2013

የወያኔንን ስርዓት ለማስወገድ በጋራ የሚደረገ ትግል ወሳኝ ነው !!! (ከገዛኽኝ አበበ ከኖርዌይ)

ለአንድ ሀገር የሚያስፈልገው ዋንኛው እና ቁልፉ ነገር ሰላም እና ነጻነት ነው:: ሰላም እና ነጻነት በሌለበት ሀገር የሚኖሩ ዜጓች፣   መብታቸው ይረገጣል ፣ ነጻነታቸው ይታፈናል  ዜጓች ለእስር፣ ለሞት፣ እና ለስደት ይደጋሉ:: ማንኛውም ሰው በሚኖርበት ሀገር በሚኖርበት ሰፈር ወይም አካባቢ እና በሚኖርበት ቤት ውስጥ በሰላም እና በነጻነት መኖርን ይፈልጋል::ነጻነት በምንም ዋጋ ሊተመን የማይችል ትልቅ ጸጋ ነው:: የሰው ልጆች በነጻነት በሚኖሩበት ሀገር መብታቸውን አስከብረው እና መብታቸው ተከብሮላቸው በሰላም እና በፍቅር በሀገራቸው ላይ ሲኖሩ ይታያሉ:: እንደ አለመታደል ሆኖ ሀገራችን ኢትዮጵያ በአለም ላይ ካሉት ሀገራት በግንባር ቀደምነት  የሰው ልጆች ነጻነታቸውን እና መብታቸውን የሚገፈፉበት ሀገር፣ የሀገሪቷ ዜጓች በጨቋኙ ገዥ ስርዓት ነጻነታቸውን ተገፈው ባሪያ ሆነው የሚኖሩበት ሀገር እንደሆነች በየጊዚው የሚወጡ አለም አቀፍ ሪፖርቶች ያስረዳሉ:: ወያኔ ኢህአዲግ የስልጣን ወንበሩን በሀይል ከተቆናጠጠበት ጊዜ ጀምሮ በየጊዜው በህዝባችን ላይ የሚያደርሰው ግፍ እና ጭቆና እየጨመረ መምጣቱ በአደባባይ የሚታይ እውነታ ነው:: ከዚህም የተነሳ በሀገራቸው ላይ የነጻነትን ሀየር መተንፈስ ያልቻሉ በየትኛውም ክልል ላይ የሚገኙ የሀገሪቷ ዚጓች በሀገራቸው ላይ መማር፣ መስራት፣ እና መኖርን እየቻሉ በሀገሪቷ ላይ እየተካሄደ ካለው አፋኝ እና ጨቋኙ ወያኔያዊ ስርዓገበሬው፣  ተማሪው፣  ፣ አስተማሪው ፣ ነጋዲው፣ ጋዜጠኛው ፣ ስፖርተኛው፣ ዘፋኙ፣ አርቲስቱ፣ ወዘተ…… በሁሉም እርከን ላይ የሚገኛው የህብረተሰብ ክፍል ሀገሩ ላይ በሰላም እና በነጻነት መኖርን ስላልቻለ ባገኘው አጋጣሚ ሁሉ በየጊዜው ለስደት ሲዳረግ ይታያል  :: ዋናው እና ወሳኙ ነገር ግን ከሁለት አስርት አመታት በላይ የዜጓችን መብት እያፈነ እና ነጻነታቸውን እየረገጠ ህዝባችንን ለስደት እያደረገ ያለውን ያለውን ይኼን ሰይጣናዊ እና አረመናዊን የወያኔን ስርዓት እንዴት እና ማን ያስወግደው የብዙዎቻችን ነጻነትን እና ፍትህን ናፋቂ ኢትዮጵያኖች ጥያቄ ነው ::
ት የተነሳ ሀገራቸውን እየጣሉ ይሰደዳሉ :: ማንኛውም ሰው ሀገሩን ጥሉ መሰደትን የሚፈልግ ያለ አይመስለኝም በሀገሩ ላይ በነጻነት እና በሰላም መማር መስራት እና መኖርን እስከቻለ ድረስ ::በአንድ ሀገር ላይ መልካም የሆነ መንግስታዊ አስተዳደር የማይካሂድ ከሆነ  አብዛኛውን ጊዜ ዜጓች ለስደት ይደረጋሉ በኢትዮጵያም እየሆነ ያለው ይህ ነው በአሁኑ ሰአት ለስደት የሚዳረገው የሀገራችን ዜጋ ሁሉም የማእበረሰብ ክፍል ነው::
በርግጥ በአሁኑ ሰአት ይህንን ስርዓት በመቃወም በሀገር ቤትም ከ ሀገር ቤትም ውጭ ብዙ የፖለቲካ ድርጅቶች እንደተቋቋሙ እና በተለያየ መንገድ እራሳቸውን እያደራጁ   እንዳሉ የምናየው እና የምንሰማው ነገር ሲሆን::የእነዚሀ  የፖለቲካ ድርጅቶች መብዛት የተለያዩ እንቅስቃሴዎችን ማድረግ  ሁላችንም በሀገራችን ላይ እንዲሆንልን የምንመኘውን እና የምንናፍቀውን የወያኔን መንግስት አስወግዱ ፍትህ፣ ሰላምን እና ነጻነትን  ያመጣልን ይሆን? የብዙዎቻችን ጥያቄ ይመስለኛል::
 እንደእኔ እንደእኔ በየጌዜው ቁጥራቸው እየጨመረ የሚመጣው የፖለቲካ ድርጅቶች መብዛት ለኢትዮጵያ ሕዝብ ሰላሙን እና ነጻነቱን ያመጣል የሚለው እመነቱ ባይኖረኝም ብዙም ተቀውሞ የለኝም :: ዋናው አላማ የወያኔን መንግስት ለመቃወም የተቋቋሙ የፖለቲካ ድርጅቶች ለተነሱለት ዓላማ በእውነተኛ ትግል ውስጥ  እስከሚገኙ ድረስ ምንም ጉዳት የለውም ::  ነገር ግን በአንዳንድ  የተቀዋሚ ፖለቲካ ድርጀቶች መካካል እየሆነ እና እያየነው ያለው ነገር አንባ ገነኑን የወያኔ ኢህአዲግን ስርአት ለመቃወም የተነሱ ማንኛውም የተቀዋሚ ድርጅቶች እራሳቸውን እንዲፈትሹ የሚገፋፋ ነገር ነው :: ይህን ያሉኩበትም ምክንያት አለኝ አንዳንዶች የፖለቲካ ድርጅቶች ለምን ዓላማ እንደተነሱ እንኮን የተነሱበትን ዓላማ የዘነጉት ይመስለኛል ምክንያቱም በአሁኑ ሰአት ሁሉም ሰው ሆነ ማንኛውም የተቃዋሚ ድርጅቶች ሊዋጋው እና ሊታገለው የሚገባ ትልቁ ቁጥር አንድ የኢትዮጵያ ሕዝብ ጠላት የወያኔ ኢህአዲግ መንግስት መሆን ሲገባው በአንዳንድ የተቃዋሚ ድርጅቶች እንደምናየው አንዱ የሌላውን ትግል ማንቆሸሽ እና ማጣጣል አላስፈላጊ እና ለነጻነት ለምናደርገው ትግል እንቅፋት የሚሆን ይመስለኛል::
በርግጥ በአሁኑ ሰአት ከሀገር ውጭ ሆነው እራሳቸውን መስዕዋት በማድረግ የወያኔን መንግስት እየተፋለሙ ያሉ ድርጅቶች ከሌሎች አጋሮቻቸው ጋር ጥምረትን በመፍጠር እና አብሮ በመታገል ዘረኛውን የወያኔን መንግስት በቁርጠኝነት እየተፋለሙት እና የወያኔን መንግስት እያስደነበሩት እንደለ የምንሰማው ዜና እሰየው የሚያስብል እና በርቱ የሚያሰኝ ቢሆንም ገና ግን ይቀራል ባይ ነኝ:: የጠላቴ ጠላት ወዳጂ ነው እንደሚባለው ማንም የፖለቲካ ድርጅት በማንኛውም መንገድ እና ማንኛውንም ስልት በመጠቀም ይሁን  የወያኔን እርኩስ ድርጊት ለመቃወም እስከተነሳ ድረስ ልንደገፈው እና ልናበረታታው ይገባል ባይ ነኝ :: እያንዳንዱ የፖለቲካ ድርጅት ወያኔን የሚታገልበት እና ወያኔን በመረጥኩት በዚህ መንገድ ብሂድ እና ብታገል እጥለዋለው ብሏ የሚያምንበት የእራሱ የሆነ እቅድ እና አላማ ሊኖረው ይችላል ነገር ግን ማንኛውም የተቃዋሚ የፓለቲካ ድርጅት በእኔ መንገድ እሳካልሂዱ ድርስ ብሎ ትክክል አንዳይደሉ መቁጠር  አግባብ የሆነ አይመስለኝም:: የትኛውም  የፖለቲካ ድርጅት በየትኛውም መንገድ ይሁን ይታገል እያንዳንዳችን ትኩረት ማድረግ ያለብን የጋራ ጠላታችንን የወያኔን መንግስት እና ስርዓት በጋራ ሆነን በአንድነት በመረባረብ ማስወገድ ለማያቋርጥ ሰላም እና ለዘለቂታዊ ነጻነት ወሳኝ ነው ባይ ነኝ:: በተናጥል እና እያንዳንዱ የተቃዋሚ ድርጅት ብቻውን የሚያደርገው ትግል የትም አያደርሰውም ምን አልባት ጊዚያዊ ድልን ሊያገኝ ይችል ይሆናል ግን ለአንዴ እና ለመጨረሻ ጊዜ ጨቋኙን የወያኔንን ስርአት አስወግዶ ዘለቂታ ያለው ሰላም እና ነጻነትን በሀገራችን ኢትዮጵያ ላይ ለማምጣት  በህብረት መታገል ይጠበቅብናል እያልኩኝ ይኼን አረመናዊ የወያኔን ስርዓት በጽናት እና በቁርጠኝነት እየታገላችው ያላችው የፖለቲካ ድርጅቶች የተነሳችውለት ዓላም የወያኔ ስርዓት እስኪወገድ ድረስ እጅ ለእጅ በመያያዝ በጋራ ትግላችውን አጠንክሩ ነጻነት እና ሰላም በሀገሩ ላይ የናፈቀው የኢትዮጵያ ህዝብ የወያኔ የዘር ፖለቲካ ሳይዘው አማራው ፣ጉራጌው፣ ኦሮሞው፣ ትግሪው፣ጋምቤላው ወዘተ …… መላው የኢትዮጵያ ህዝብ ከጓናችው ይቋማል ባይ ነኝ::
ኢትዮጵያ በቆራጥ ልጆቿ ትግል ነፃ ትሆናለች!

No comments:

Post a Comment