Sunday, December 15, 2013

ስለ ዶክተር ኢንጂነር ቅጣው እጅጉ በጥቂቱ


የዶክተር ቅጣው እጅጉ አጭር የሕይወት ታሪክዶክተር ቅጣው እጅጉ የካቲት 16 ቀን 1940 (እ.ኢ.አ) ከአባታቸው ከአቶ እጅጉ ሃይሌ እና ከእናታቸው ከወ/ሮ አስካለ በላይነህ በከፋ
ጠቅላይ ግዛት በቦንጋ ከተማ ተወለዱ። የአንደኛና ሁለተኛ ደረጃ ትምህርታቸውን በቦንጋ፣ በዋከና በጅማ ከተማ ካጠናቀቁ በኃላበባህር ዳር በሚገኘው ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅየከፍተኛ ትምህርታቸውን አጠናቀዋል።
kitዶክተር ቅጣው ወደ ጃፓን አገር በመሄድ በኦሳካዪኒቨርስቲ በቋንቋና የጃፓን ኢኮኖሚ፣በሄሮሺማ ዩንቨርስቲ የኢንደስትሪ እናየአውቶሞቲቭ ኢንጂነሪንግ አጥንተው ትምህርታቸውን አጠናቀዋል። በኋላም አሜሪካን ሀገር ስኮላር ሺፕ አግኝተው በቢዝነስ አድሚንስትሬሽን ማስትሬታቸውን በመጨረሻም ለትምህርት ባላቸው ከፍተኛ ፍላጎት በኤሮ-ስፔስ ምህንድስና ዶክትሬታቸውን ተቀብለዋል።
ዶክተር ቅጣው በናሳ (NASA) በሲስተም መሃንዲስነትና በጠፈር ሳይንቲስትነት የሰሩ
ሲሆን ከሌሎች መሃንዲሶችና ሳይንትስቶች ጋር በመተባበር ለእኛ አለም (Planet Earth) እና
ለተቀሩት ፕላኔቶች የምርምር ሳይንስ (Planetary Science Research and Exploration) የሚረዱ የጠፈር መንኮራኩሮችና ሮኬቶች ፈጥረዋል።  ዶክተር ቅጣው በዚህ ከፈጣሪ በተቸሩት ታላቅ ችሎታና እውቅት ለዚህች ለምንኖርባት ዓለምና ሕዝብ ታላቅ አስተዋፅዎ አበርክትዋል። ከነዚህም ጥቂቱን ለመጥቀስ ለናሳ(NASA) ሁለት የኤሮ-ስፔስ መወርወሪያ ሜካኒዝም ለቦይንግ ኩባንያ ሲሙሌተር (Flight Dynamic Simulator) እና አድቫንስድ
ወይንም ኔክስት ጀነሬሽን (Advance or Next Generation) በመባል የሚታወቁትን
ግሎባል ፖዚሽን ሳተላይት ሲስተም(Global Positioning Satellite System)
ከፈለሰፉት ውስጥ አንደኛው ሰው እሳቸው ነበሩ ዶክተር ቅጣው Trans Tech International በመባል የሚታወቀውን ዓለም አቀፍ የቴክኖሎጂ ድርጅት በመመስረት የተለያዩ ሀገሮች የቴክኖሎጂ አቅማቸውን እንዲያሳድጉ በአማካሪነት አገልገለዋል።
cabበተጨማሪም ለሀገራቸው በነበራቸው ታላቅ ፍቅር ‘የኢትዮጵያ ብሔራዊ አንድነት ግንባር’ የተባለውን ድርጅት በመመስረት ገንዘባቸውንና ጉልበታቸውን ሳይቆጥቡ ለኢትዮጵያ ሰላም ፣ ብልፅግናና አንድነት ትልቅ መስዋዕትነት የከፈሉ የትግል ሰው ነበሩ። በእውነትም ኢትዮጵያ ብቻ ሳትሆን ዓለም አንድ ትልቅ ሰው አጣች ቢባል ማጋነን አይሆንም። ዶክተር ቅጣው ከባለቤታቸው ከወ/ሮ ስቴላ እጅጉ ጋር በመልካምና በደስታ ጋብቻ ተጣምረው ይኖሩ ነበር። ዶክተር ቅጣው፣ ቢንያም ያሬድ እና አቢጋኤል የተባሉ የሁለት ወንዶችና የአንድ ሴት አባት ነበሩ።
ዶክተር ቅጣው እጅጉ ወደ ኦስትን ቴክሳስ ዘመዶቻቸውን ለመጠየቅ መጥተው ድንገት
በደርሰባቸው ሕመም ምክንያት በታማኝነትና በመሰጠት ሲያገለገሉትና ዘወትር ሊያዩት
ወደሚናፍቁት ጌታቸው እየሱስ ክርስቶስ በጃንዋሪ 12 ቀን 2006 በ58 አመታቸው ተሰብስበዋል።
kitawዶክተር ቅጣው እጅጉ በመልካም ባህሪያቸው የተወደዱ፣ በትህትናቸው የተመሰገኑ፣ በስራቸው የተደነቁ፣ በራዕያቸው ብዙ ተከታዮችን ያፈሩ፣ የብዙዎቻችን ተስፋና አርዓያ እንዲሁም የሀገር ኩራት የሆኑ ታላቅ ሰው ነበሩ። ዶክተር ቅጣውባለቤታቸውንና ልጆቻቸውን አፍቃሪ፣ ዘመድ ወዳጅ አክባሪ እና ከሁሉም በላይ እግዚአብሔርን ፈሪ ነበሩ።

No comments:

Post a Comment