Thursday, December 12, 2013

በኢትዬጲያ ሙስሊሞች ላይ መንግስት የጥፋተኘነት ውሳኔ አስተላለፈ፡፡


በዕድሜ የገፉት አባቶች በነፃ ፍርድ ቤቱ እንዲሰናበቱ መወሰኑ ተዘግቧል፡፤ 

መንግስት በኢትዬጲያ ሙስሊሞች ላይ የጥፋተኘነት ውሳኔ ማስተላለፉን ምንጮች አስታወቁ፡፡ለታህሳስ 3 በተቀጠረው የብይን ቀነ ቀጠሮ መሰረት 10 ተከሳሾችን ነፃ ናቸው ሲል ፍርድ ቤቱ ያሰናበተ ሲሆን የተቀሩት ላይ ግን በሽብር ድርጊት ፈፃሚነት ወንጀል ጥፋተኛ ናችሁ ሲል ብይን አስተላልፏል፡፡

በዚህም መሰረት ሁሉም በዕድሜ የገፉት አባቶች ዶ/ር ከማል ገለቱ፣ሼህ አብዱረህማን፣ሼህ ሃጂ ኢብራሂም፣ ሼህ ጣሂር፣.ሼህ ሱልጣን አማን፣ ኡስታዝ ጀማል ያሲን ፣ኡስታዝ ሰኡድ አሊ ፣ወንድም አሊ መኪ ፣ ወንድም ሀሰን አቢ እና ወ/ሮ ሃቢባ መሃመድ በነፃ ፍርድ ቤቱ እንዲሰናበቱ መወሰኑ ተዘግቧል፡፤ በተቀሩት ላይ ደግሞ የጥፋተኘነት ክስ በማስተላለፍ ለጥር 22 የመከላከያ ምስክራቸውን እንዲያቀርቡ ውሳኔ በማስተላለፍ ችሎቱ ተጠናቋል፡፡

No comments:

Post a Comment