Monday, February 17, 2014

እየተዋረዱ መገዛት እስከመቼ!?

በቅዱስ ዬሃንስ

አለምነው መኮነን የተባለ የብአዴን ወኪልና የባንዳ አስፈፃሚ የአለቆቹን የዘወትር አባባል በማስረገጥእመራዋለሁ የሚለውን የአማራ ህዝብ <<ሰንፋጭ የሆነ ትምክህተኝነት የተጠናወተው፤ ትምክህተኝነቱንያልተው፤ በባዶ እግሩ እየሄደ መርዝ ንግግር የሚናገር ወዘተ>> ካለ በኋላ <<የትምክህት ልጋጉን ማራገፍአለበት>>   በማለት እንደሌሎች ብሄረሰቦች ሁሉ ደከመኝ፡ ሰለቸኝ ሳይል ዋጋ የከፈለውን የአማራ ህዝብ ዋጋበማሳጣት የሌሎቹ ጠላት አድርጐ በማቅረብ፡ የዘረኞች ተባባሪነቱን አስመስክሯል። የአማራው ህዝብ የወያኔ ዘረኞች ዋነኛ ዒላማ ሆኖ የአገዛዙን የግፍ ፅዋ ያለማቋረጥ መጋት ከጀመረ ድፍን 23 አመታት ተቆጠሩ። ፋሽስቱ ወያኔ የኢትዮጵያን ህዝብ ብሔራዊ ስሜት በማምከን ፣ የዘመናት ተገዥነቱን ለማረጋገጥ በቅድሚያ የአማራን ሕዝብ ማንነት ማጥፋት ፣ የአማራን ሕዝብ ስነ ልቦናዊ ጥንካሬ መስለብ እና አንገቱን ማስደፋት አስፈላጊ መሆኑን በጽናት ያምናል። ይህ በመሆኑም ፣ በአማራ ህዝብ ላይ በወያኔ የሚፈፀመው ግፍ እና በደል ከጊዜ ወደ ጊዜ እየተባባሰ ስር እየሰደደና እየከፋ በግልፅም በስውርም በተቀነባበረ መንገድ ቀጥሏል።
ይህ የህወሀት የጸረ አማራ ፕሮፓጋንዳ ማሽን የሚመራው በዋና ዋናዎቹ የወያኔ  ሹሞች ቢሆንም ወያኔ የአማራን ህዝብ የሚገድለዉ፤ የሚያዋርደዉና የሚያሳደድዉ አማራ ነን በሚሉ ነገር ግን የአማራን ህዝብ በጅምላ በሚሰድቡና አማራዉ ሲገደል፤ ሲታሰርና ሲፈናቀል ይበልህ በሚሉ በእነ አለምነው መኮንን አይነት ወፍ ዘራሽ ካድሬዎች ነው። አንበሳ ሲያረጅ የዝንብ መጫወቻ ይሆናል እንዲሉ፡ የአማራው ህዝብ ዛሬ ቀን ጣለውና፣ በጠላቶቹ እጅ ወደቀ፣ የድፍን ስድና መረን ያደገ ዋልጌ ሁሉ የስድብና የዘለፋ አፍ ማሟሻ የመሆን ዕጣ ደረሰው። አለምነው መኮነን የተባለ የብአዴን ወኪልና የባንዳ አስፈፃሚ የአለቆቹን የዘወትር አባባል በማስረገጥ እመራዋለሁ የሚለውን የአማራ ህዝብ <<ሰንፋጭ የሆነ ትምክህተኝነት የተጠናወተው፤ ትምክህተኝነቱን ያልተው፤ በባዶ እግሩ እየሄደ መርዝ ንግግር የሚናገር ወዘተ>> ካለ በኋላ <<የትምክህት ልጋጉን ማራገፍ አለበት>> በማለት እንደሌሎች ብሄረሰቦች ሁሉ ደከመኝ፡ ሰለቸኝ ሳይል ዋጋ የከፈለውን የአማራ ህዝብ ዋጋ በማሳጣት የሌሎቹ ጠላት አድርጐ በማቅረብ፡ የዘረኞች ተባባሪነቱን አስመስክሯል።
በርግጥ ወያኔ እንደፈረስ የሚጋልበው ብአዴን በታሪኩ አንድም ለህዝቡ የቆመ መሪ ሲያፈራ አልታየም። የአማራ ህዝብ ብአዴንን የመሰለ አሳፋሪ ድርጅት በታሪኩ ገጥሞት አያውቅም። በባዕድ ወረራ ጊዜ ለጣልያን ያደሩ ባንዶች እንኳን ከዛሬዎቹ ብአዴኖች የተሻለ ክብር ነበራቸው። ከዛሬዎቹም በተሻለ በጌቶቻቸው ጣሊያኖችን ይሰሙ ነበር። ብአዴን ግን ራሱን ከባንዳነትም አውርዶ ባርነት ደረጃ ላይ የጣለ ከመሆንም አልፎ  በባርነቱ የሚደሰት ድርጅት ነው። ብአዴን የህወሓት ወያኔ ወኪል እንጅ የአማራው ህዝብ ወኪል አይደለም፡፡ ብአዴን ሁሌም የአማራውን ህዝብ እንደ ሰደበ፣ እንዳዋረደ፤ እንዳስገዛ ነው፡፡ የብአዴን ፍሬ የሆነው አለምነው የተባለው የእናት ጡት ነካሽም በድጋሚ ያረጋገጠልን ይንኑ ነው። አለምነዉ እነዚያን እጅግ አሳፋሪና ከፋፋይ ንግግሮች የተናገረዉ ፀረ አማራና ፀረ-ኢትየዮጵያ ጌቶቹን ያስደሰተ መስሎት ወይም የሥልጣን ቆይታውን ያመቻቸና በሥልጣን መሰላል ሽቅብ የተወነጨፈ መስሎት ሊሆን ይችላል፤ ሆኖም የአማራ ህዝብና ወገኑ የሆነዉ ሌላዉ የኢትዮጵያ ህዝብ ይህንን የአንድን ህዝብ ስብእናና ክብር የሚያጎድፍ  ንግግር በምንም መልኩ ችላ ብሎ ሊያልፈዉ አይገባም፡፡
እንደሚታወቀው ዘረኛው ወያኔ የጸረ አማራነት አቋሙ እጅግ የከፋ ፣ ስር የሰደደ እና በድርጅት የታቀፈ ነዉ፤ እኛም በድርጅት ታቅፈን በድርጅት ካልገጠምነዉና ካልደመሰስነዉ በቀር የወያኔ ዘረኝነት መቆሚያና ማለቂያ የለዉም። ለምሳሌ ፋሽስቱ ወያኔ በቅርቡ በቤኒሻንጉልና በቤንች ማጅ ዞን ጉራፈርዳ ወረዳ ዉስጥ አማራውን በማፈናቀል አማሮች ከአማራ ክልል ዉጭ መኖር አትችሉም ብሏል። የወያኔ ዘረኞች እነሱ በዘጠኙም ክልል እንዳሻቸዉ እየዞሩና ኃብት እያጋበሱ አማራዉን ግን እንደ ውጭ ዜጋ በማየት በገዛ አገሩ ውስጥ ከቦታ ወደ ቦታ እንዳይንቀሳቀስ በማድረግ አማራዉ ሳይወድ በግዱ የስደት ገፈት ቀማሽ እንዲሆን አድርገዉታል። ኧረ ለመሆኑ ይህ የግፍ ፅዋ ሂትለር በጀርመን በይሁዳዎች ላይ ከፈፀመው በምን ይለያል? እንደምናስታውሰው በሽግግሩ ወቅት ጠቅላይ ሚንስትር በነበረው ታምራት ላይኔና በወቅቱ ፕረዜዳንት በነበረው ሟቹ መለስ ዜናዊ በተፈራ ዋልዋ አቀናባሪነት በተሰጠ ትእዛዝ በወተር፤ አርባ ጉጉና በበደኖ ኦህዴድና ኦነግን በየፊናው አስማርተው የኋላ ድጋፍ እየሰጡ ውድ ወገኖቻችን ህይወታቸው ስታልፍ እንደ እንሰሳ ቆዳቸው መገፈፉ፤ ሳይሞቱ በገደል ሲጣሉና ሕጻን ሽማግሌ ሴት ወንድ ሳይለይ በጅምላ የማለቃቸውን ሃዘን ሳንረሳው ዛሬ ደግሞ ዳግም የጠብ አጫሪነቱን፡ በምን ታደርጉኛላችሁ እብሪት ተወጥሮ በባንዳው አለምነው መኮነን አስፈፃሚነት ለክልሉ ህዝብ ያለውን ከፍተኛ ንቀት ሬት ሬት በሚሉና አጥንትን የሚሰረስሩ ስድቦችን በመጠቀም አንካችሁ አሉ። አለምነው መኮነን የረጨውን መርዝ እስኪ አስቡት ወገን? ማንን ተማምኖ፡ የልብ ልብ ተሰምቶት ይመስላችኋል ይህ የመርገምት ልጅ ይህን ያህል ልሃጩን በጨዋው የአማራ ህዝብ ላይ የሚተፋበት? አረመኔውን የፋሽስት አገዛዝ አደለምን። ኧረ ግን አማራው እስከመቼ በዚህ የፋሽስት ስርአት እየተገደለ፡ እየተሰደደና እየተዋረደ መኖርን መረጠ? ኧረ ዝምታው ምንድነው? ግን እስከመቼስ ይሆን?
ውድ የኢትዮጵያ ህዝብ ሆይ!
ፋሽስቱ ወያኔ በአማራ ህዝብ ላይ በተከታታይ በማድረስ ላይ ያለዉ በደል፤ ግፍና ዉርደት የወያኔ ዘረኞች ሊነግሩን አንደሚፈልጉት የአማራዉ ጉዳይ ነዉ ተብሎ የሚታለፍ ጉዳይ አይደለም።ይህ ዛሬ በአማራዉ ላይ እየፈጸመው ያለው ዘርን የማዋረድና የማጥፋት ርካሽ ስራ ነገ በእያንዳንዳችን ላይ የሚደርስ መሆኑን ልንረዳ ይገባል። የወያኔ ወንጀል አሁን የተጠነሰሰ ሳይሆን ወያኔ ገና ደደቢት በረሃ ላይ ሲጠነሰስ አብሮት የተጠነሰሰ ሴራ ነዉ። ወያኔና ዘረኛ ስርአቱ እስካልተወገዱ ድረስ ይህ የተጀመረው አማራን የማዋረድ፡ የመጨፍጨፋ፣ የማፈናቀልና የማሳደድ ዘመቻ፣ ተጠናክሮ መቀጠሉ አይቀርም። ወያኔ አማራዉን ካዳከምኩ ሌላዉ አያቅተኝም በሚል ዘረኛ ስሌቱ ዛሬ አማራዉ ላይ አተኮረ እንጂ በወያኔ የተደበደ ፣ የታሰረ፣ የተሰደደ፤ የተፈናቀለ ፤እንዲራብ የተደረገ፤ የተዋረደና የተገደለ ኢትዮጵያዊ ስፍር ቁጥር የለዉም። ዛሬ  የአማራው ህዝብ ብቻ ሳይሆን ድፍን የኢትዮጵያ ህዝብ በወያኔ ጨካኝ ስርአት አማካኝነት በጨለማ ሂዎት ውስጥ እየማቀቀ ነው። ስለዚህ ችግሩ የአገርና የወገን የህልውና ጉዳይ እንጅ  የፖለቲካ ጨዋታ ባለመሆኑ የወጣት፣ አዋቂ፣ ጎልማሳ፣ ሽማግሌ፣ ጾታ ሳይለየን ወያኔን ለማስወገድ በሚደረገው ትግል ምላሽ በመስጠት አለበት ባይ ነኝ። በአማራው ህዝብ ላይ የጠቆረውን ጨለማ በብርሃን መተኪያ ጊዜው አሁን ነው። ይህ ትውልድ የታሪክ ባለእዳ አይሁን።
በወያኔ ዙሪያ ተሰብስባችሁ የሥርዓቱ ጠባቂና ተጠቃሚዎች የሆናችሁ በሙሉ ባሳለፋችሁት የግዛት ዘመናችሁ የአማራውን ዘር ብትሰድቡትም፡ ብትገድሉትም፡ ብታስሩትና ብታስርቡትም፤ ብታሰድዱትም፤ ሀብት ንብረቱን ብትዘርፉትም፤ በአገሩ በኢትዮጵያ የመኖር መብቱን ብትገፉትም ሕዝቡ መሃሪ ነውና ዛሬውኑ የሕዝቡን ትግል ብትደግፉና ብትቀላቀሉ ይሻላል።  በተለይ አማራ ሆናችሁ ብአዴን የሚባል የፋሽስቱ ወያኔን የጥፋት ክንፍ ስታገለግሉ፡ እስከ ዛሬ በሆዳችሁ ስትገዙ የኖራችሁ እንደ አለምነው መኮንን አይነት የእፉኝት ልጆች ሕዝባችሁን የማዋረድና፤ የማድማት ተልኮዋችሁን አቁማችሁ፤ ወያኔ በወገኖቻችሁ ላይ እየፈጠረ ያለው ችግር ተሰምቷችሁ፤ ህዝባችሁን ይቅርታ ጠይቃችሁ፤ አሁኑኑ ለትግሉ ምላሽ በመስጠት መከታ በመሆን አዝሎ ያሳደጋችሁን ህብረተሰብ ከባርነት ቀንበር ታላቅቁት ዘንድ ወገናዊ ጥሪየን አቀርባለሁ። ለውሳኔው አለማርፈዳችሁን በዚሁ አጋጣሚ ላረጋግጥላችሁ ጭምር እወዳለሁ።
ድል ለጭቁኑ የኢትዮጵያ ህዝብ!

No comments:

Post a Comment