Saturday, September 21, 2013

ኦሮማይ፣ ትግሉ በሚቻለውና በማንኛውም መንገድ!

ከቴዎድሮስ ሓይሌ (tadyha@gmail.com) ሠሞኑን የግንቦት ሰባት ዋና ፀሐፊ የሆኑት አቶ አንዳርጋቸው ጽጌ ስለ ኤርትራ ቆይታቸውና ስለድርጅታቸው ቀጣይ የትግል እንቅስቃሴ ሠፊ ገለጻና ማብራሪያ በኢሣት ቴሌቪዠን ከሠጡ ወዲህ የዘረኛው የትግሬ ነጻ አውጪ ግንባር ደጋፊ የሆኑት መርገማዊ ልሳኖች( አይጋ ፎረም ፤ ትግራይ ኦላይንና አውራንባ ታይምስ) እና አንዳንድ ተንበርካኪ የመንደር ሬድዮኖች ሰፊ የውግዘትና የህዝብን መንፈስ ያሸብርልናል
በተቃዋሚዎችም ላይ ጥርጣሬ ይዘራልናል በሚል ደካማ ግንዛቤ እያካሄዱ ካለው አሰልቺና ኋላቀር ፕሮፓጋንዳ እጅግ ተጋኖ እየቀረበ ያለው ከሻብያ ጋር አብሮ መስራት ታላቅ የሃገር ክህደት ስለመሆኑ እፍረት የለሽ ኡኡታ በማሰማት ላይ ይገኛሉ።Ato Andargachew Tsige, Ginbot 7 ይህንን ጽሑፍ እንድጽፍም ያነሳሳኝ ይህ የወያኔ በቀቀኖች ልቅ ያጣ የፀረ ሻብያ ውትወታ ወያኔ የምትባለው የጠባብ ዘረኞች ቡድን ለዚህ ዛሬ ለደረሰችበት የዘረፋና የልዕልና ደረጃ የበቃችው ከቶ በማን ትከሻ ሆነና ነው ። ዛሬ ሌሎች ኢትዮጽያውያን ወደ ኤርትራ ስለሄዱ ይህ ሁሉ ውንጀላ ደጋፊ ተብዬቹ የሚነዙት ወያኔ በሻብያ ሁለገብ ድጋፍ የማቴሪያል የትጥቅ የዕቅድና የሃሳብ መመሪያ ውጪ እንኳን ሚኒሊክ ቤተመንግስት ልትደርስ ቀርቶ ተከዜንም ባልተሻገረች ነበር።በአንድ ወቅት የኤርትራው መከላከያ ሚንስትር ጀነራል ስብሃት ኤፍሬም ስለ ወያኔዎቹ ያለውን እጅግ የወረደ ንቀት የገለጸበትን አባባል እንዳስታውስ አሰገደደኝ ‘’እኛ ከነጀነራል ደምሴ ቡልቱና ከነጀነራል ረጋሳ ጅማ ጋር በመዋጋታችን ኩራት‘’ የሚሰማን በመሆኑ ከነዚህ የፍየል እረኛ ወያኔዎች ጋር ፈጽሞ ለንጽጽር የማይቀርቡ እጃቸውን ይዘን ለዚህ ያደረስናቸው እኛነን ሲል ነበር ከአመታት በፊት የተናገረው። ወያኔዎች በሻብያ የበላይ ሹማምንት ብቻ ሳይሆን በተራው ተጋደልቲ ጭምር የሚናቁና እንደ ሻብያ አገልጋይ የሚታዩ ስለመሆናቸው ከሁለት አስዕርተ አመታት በኋላ እንኳ አለመለወጡን በረባው ባረባውም በባነኑ ቁጥር የሻብያ ስም እንደሚያስበረግጋቸው ዘወትር ከአፋቸው አለመጥፋቱን የምናስተውለው ሲሆን የሰሞኑ ደግሞ ተባብሶ የሚታየው ጫጫታ አንዱ የወያኔዎች የፍርሃት ማሳያ ይመስለኛል። የወያኔ መሪዎች የትግራይን ገበሬ ልጆች በግዴታ ለሻብያ አሰልፈው እያዘመቱ ፈንጅ ማምከኛና በማስደረግ የፈጸሙት የሎሌነት አሳፋሪ ገሃድ እየወጣ ባለበት በአሁኑ ወቅት አበው በቆማጣ ቤት አንድ ጣት ብርቅ ነው እንዲሉ እሱ ብቻ ሕልመኛ እሱ ብቻ ባለራዕይ የነበረውና በሞት ተለይቶ እንኳ ወሬው የገነነለት መለስ ዜናዊ እንዲህ ለራሱ የሚያሸረግድ አድርባይ የሎሌ መንጋ ትቶ እንደሄደ ትላንት እርሱም ለሻብያ ካድሬዎች ይንበረከክ እንደነበረ ታሪኩን የሚያውቁት ሲመሰክሩ ቆይተዋል በተለይም ወያኔዎች ከሻብያ ጫማ ስር ለመዋላቸው የሚቀርብባቸው ማስረጃ የኢትዮጽያን ተፈጥሯዊ የባህር በር አሣልፈው ከመስጠት አልፈው የኤርትራ ነጋዴዎች የጅማን ቡና የለገደንቢን ወርቅ ከማህል ሃገር በብር እየገዙ ለውጭ ገበያ በዶላር ያቀርቡ የነበረበትን ሁኔታ አንድ እግር ቡና የማታብቅለው ኤርትራ ከቡና ላኪ ሃገሮች ተርታ መሰለፍ እስክትደርስ ድረስ የተካሄደውን የወያኔ ተንበርካኪነት ስናስታውስ ሻብያ በአዲስ አበባው ኤንባሲ ውስጥ የጥቁር ገበያ የዶላር ምንዛሬውን ሲያደራ እዚያው ኤንባሲ ውስጥ እስር ቤት አቋቁሞ የፈለገውን ሲያደርግ የነበረበት የጌታና የሎሌ ታሪክ የተዘነጋ ይመስል ወያኔና ጭፍሮቿ ሻብያን ቀንድና ጭራ ልትቀጥልልለት የምታደርገው መፍጨርጨር ተመልካች የማይታደምበት ተራ ኮሜዲ ከመሆኑም በላይ እውነተኞቹ የትግራይ ልጆች እንደ አስራት አብረሃምና እንደ ገብረመድህን አርዐያ ያሉት ይህንን የሚታወቅ ታሪክ በተባ ብዕራቸው ትውልድ እንዲያውቀው ከትበው ያስቀመጡት በመሆኑ ዝርዝር ሃተታ አያስፈልገውም ። ዘረኝውና ዘራፊው የወያኔ ጥርቃሞ በእንዲህ ያለ የሻብያ የጭን ገረድነት የገለማ ታሪክ እያለው ዛሬ ሌሎች ኢትዮጽያውያን ከሻብያ ጋር ቢተባበሩ ከኢሳያስ ጋር ቢነጋገሩ ከቶ ሊቃወም የሚችልበት የሞራል መሠረት የሌለው መሆኑን ወናፍ ፕሮፓጋንዲስቶቹ ሊረዱ በተገባ ነበር። የኢትዮጽያ ልጆች በመረጡት አጀንዳ በመሰላቸው የትግል ስትራቴጂ ከማንኛውም ምድራዊ ሃይል ጋር የመነጋገር የመተባበር ሙሉ መብትና የተሟላ የሞራል የበላይነት ስላላቸው ላለፉት 22 አመታት የህዝባችንን ደም በመምጠጥ ላይ ያለውን ዘራፊ ሌባና ሰውበላው ወያኔን ለማስወገድ ከሻብያ ጋር አይደለም ከሴጣንም ጋር ቢዋወሉ የሚያስመሰግን እንጂ ከቶም የሚያስወቅስ አለመሆኑን ማንም ሊያሰምርበት የሚገባው አብይ ነጥብ ሃገራችንና ሕዝባችን ከወያኔ የከፋ ምድራዊ ጠላት የለውምና ነው። ኢትዮጽያዊ ሃይሎች ከማንኛውም ወገን የሚደረግላቸውን የገንዘብ የማቴሪያልና የስልጠና እገዛ ሃገርና ወገንን ለመታደግ እስካዋሉት ድረስ ከማንም ጋር ቢተባበሩ ከቶም በታሪክ ሊያስወቅሳቸው የሚያስችል ባለመሆኑ በያዙት ጎዳና በልበሙሉነትና በወኔ ሊጓዙ በመቃተት ላይ ያለው የወገናቸው የሰቆቃ ድምጽ ግድ ይላቸዋል። ነገር ግን የሃገርን ብሄራዊ ጥቅም በሚጎዳ ማናቸውም ውልና ስምምነት ውስጥ ቢገቡ ወያኔ ለሻብያ ቂጣ ጋጋሪና መንገድ መሪ በመሆን እንደፈጸመው የውርደት ታሪክ እነሱም እንዳይደግሙት ሊጠነቀቁና አካሄዳቸውን ከጊዜያዊ ፍላጎት አንጻር ሳይሆን ከዘላቂ ጥቅም አንጻር እንዲያደርጉ ይጠበቅባቸዋል። ከዚህ ባሻገር ወያኔን ለመደምሰስና ለማስወገድ የሚደረገው ትግል በተቀናጀና ሁሉን ወገን ባሳተፈ መልኩ እንዲሆን ሠፊ የፖለቲካ የዲፕሎማሲና የፕሮፓጋንዳ ስራ በስፋትና በጥራት እንዲካሄድ ከህዝቡና ከአጋር ወገኖች የሚገኝ ትግሉን በጥንካሬ ለመወጣት እንዲቻል የሚያግዝ ከፍተኛ የገንዘብ አቅም በማፈላለጉ ላይ ያለይሉኝታ ሊንቀሳቀሱ ይገባል። እዚህ ላይ ባለፈው ሰሞን እንደትልቅ የሃገር ክህደት ወያኔዎችና አንዳንድ ህዝባችን የተጫነበት ድቅድቅ የዘረኝነትና የግፍ ጭለማ ያልታያቸውና የሃገራችን እጣፋንታ ያልገባቸው በተቃውሞው ጎራ የተሰለፉ ቅንጡ ፖለቲከኞች ሲያራግቡት የሰነበቱት የማጥላላት ዘመቻ ግንቦት 7 ከሻብያ ግማሽ ሚለዮን ብር የመቀበሉ ቱማታ በእኔ እምነት የሚያስወቅስ ሳይሆን የትግሉ እድገት አንድ ደረጃ እንደደረሰ ማሰያ በመሆኑ ከወያኔ ጋር ለሚደረገው እልህ አስጨራሽ ትግል የገንዘብም ሆን የቁሳቁስ ድጋፍ ከሻብያ አይደለም ከሠይጣንም ቢገኝ አመስግኖ መቀበል የሞራል ድጋፍ ያለው አካሄድ በመሆኑ አስፈላጊ አይደለም እንጂ የተገኘው ድጋፍ በአደባባይ ቢገለጽ የሚያኮራ እንጂ የሚያሳፍር አይደለም። በተለይ በተቃውሞው ጎራ ያለው ወገን ቆም ብሎ ሊያስብ የሚገባው መሠረት በሌለው እንቶፈንቶ ለመነታረክ ግዜ ከማጥፋት ይልቅ በየራሳችን ይዝን የተነሳንውን አላማ ከግብ ለማድረስ መትጋት ላይ ትኩረት ማድረግ ቢቻል ወያኔ ይህን ያህል ችግር አትሆንብንም ነበር ። ስለሆነም ከኛ ቁጥጥር ውጪ የሆነንን የሌሎችን እንቅስቃሴ ሂደቱን ባንደግፍ እንኳ ተቋዋሚ ልንሆንበት የሚያስችላን አንዳች የፖለቲካ አመክንዮ ስለሌለን በመተባበር በጋራ መቆም ባንቸል በመከባበር በየራሳችን መንገድ መጓዙ የመከራውን መንገድ የሚያሳጥር በመሆኑ ላይ ግንዛቤ ሊኖረን ይገባል። በኤርትራ በኩል የአመጽ ትግሉን እናካሂዳለን ብለው በድፍረት የቀረቡትን ወገኖች ስለቁርጠኝነታቸው አድናቆት መቸር ሲገባ አንዳንደ የዘረኛው ቡድን ተላላኪዎችና የመንደር ራድዮ ጣቢያዎች ጉዳዩን አጣመው ስላቀረቡት ብቻ ያን ይዞ የትችትና የስድብ ዘመቻ ማካሄድ ተገቢም ካለመሆኑም በላይ በእርስ በርስ ሽኩቻ የሕዝባችን መከራ እንዲራዘም ማድረግ ስለሚሆን ሁሉም ወገን ተገቢነት ባለውና ስልጡን በሆነና መቻቻልን ባሰላሰለ መንገድ ሁሉም የትግል ሃይሎች ቢቻል ጎን ለጎን ካልሆነም በመከባበር ግባቸው ላይ ብቻ ትኩረት በማድረግ ከጎንዮሽ መጠላለፍ እንዲታቀቡ የደጋፊው ህብረተሰብ አሰላለፍ ከስሜታዊነትና ከጠባብ የቡድን አመለካከት ባሻገር ሠፊውን አላማ ላይ ያነጣጠረ ብልህ አካሄድን ማቀናጀት ሁሉም አትራፊ የሚሆንበት የፖለቲካ ሂሳብ በመሆኑ ላይ ትኩረት መስጠት ይኖርብናል። ከዚህ ባሻገር ካሮጌ ፖለቲካችን የወረስነው የስማበለው የባልቴቶች የአሉባልታ ተረት ተረት ይዞ መጓዝ የደረስንበት ዘመን የማይዋጀውና የንቃተ ህሊና ደረጃ ወደማይፈቅድበት የማሰብ አድማስ የሰፋበት ሁኔታ መከሰቱን በመረዳት በሎጅክና በትንተና ሃሳባችንን እስካላስረገጥን ድረስ አዲሱ ትውልድ የማይቀበለው ባለመሆኑ በተለይ እድሜ ጠገብ ፖለቲከኞቻችን ከዚህ አንጻር የትውልድና የአመለካከት መጠነሰፊ ሽግሽግ በግዜ ሂደት መከሰቱን አውቃችሁ በየአቅጣጫው እየተካሄደ ያለውን ትግል በጥራትና በግልጽ ለውይይት እንዲቀርብ በማድረግ በአመጽ ጎዳና እንዘምታለን የሚሉትን ሃይሎች በነጠረ ሂስና ግለሂስ ጥንካሬና ድክመታቸውን እንዲለዩ ህዝባችንም አቅጣጫውን እንዲያስተካክል የሚረዳ ተሳትፏችሁ በጥበብ የተሞላ መሆን ይኖርበታል። አለያ የኔብጤው ወኔና እውቀት አጠር ዲያስፖራ ሠልፍ እንኳ ለመውጣት በደረቅ በጋ ስካርቭ የሚደርብና አርቴፊሻል ጢም የሚቀጥል ፍርሃት ያራደው አውታታ ፤ የወያኔን አገዛዝ ለመደምሰስ ዱር እንገባለን የሚሉትን ሃይሎች መደዴ በሆነ ቋንቋ ሲዘልፍና የግለሰቦችን ስብዕና ሲዘልፍ ላስተዋል ምን ያህል ከሞራል አልባነት ከኋላቀርነት ያልተላቀቀ ምስኪን ወገን በመኖሩ እንዲህ አይነቱ የስድብ ሱሰኛ በምክር አይደለም በጸበልም የሚተወው ባለመሆኑ ለእንዲህ አይነቱ የአስተሳሰብ ድውይ ከማዘን በስተቀር ሌላ ሃይል ማበከን ተገቢ አይመስለኝም ። አዲሱ ትውልድ ይጠይቃል በበቂ መልስለት ይከተልሃል፤ ይህ ነው መሬት ላይ ያለው ሃቅ ቅንጅት ሚሊዮኖችን ያነቃነቀው ሕዝባዊ አጀንዳና የሚታይ ራዕይ ስላስቀመጠ ነበር። በቅርቡ የተመሠረተው ሠማያዊ ፓርቲ በመሪዎቹ ቁርጠኝነትና ባቀረቡት ወቅታዊ አጀንዳ አንጻር ከስምንት አመታት በኋላ ታላቅ ህዝባዊ ሠልፍ በማድረግ የፈጠሩት መነቃቃት ፓርቲው ከተመሰረተ አጭር ግዜው ቢሆንም ያለው ተደማጭነቱ ከአንጋፋዎቹ ልቆ እንዲገኝና ተስፋ እነዲጣልበት ያደረገው የድርጅቱ መርሆ በሎጅክ የተቃኘና አላማውን ግልጽ በማድረጉ ይመስለኛል። ሕዝብ የሚከተለው ትውልዱ ለትግል የሚነሳው ወቅቱ ከፈጠረው አዲስ ሁኔታ አንጻር እንጂ በታሪክ ቡልኮ ተጀቡኖ በተረትና ሃሜት በሚነዳ የፖሮፓጋንዳ ዘመቻ አይደለም፤ ያ በስማ በለው በደመነፍስ ትውልድ ከሚነዳበት የስብስቴ አመለካከት ላያዳግምና ተመልሶ ላይመጣ በማስተዋልና በስልጣኔ እየተሻረ በመሄድ ላይ በመሆኑ ብዙዎች ያወሩለትን ጥቂቶች ጀምረው ያቆሙትን የአመጽ ትግል በአዲስ መልክ እናስቀጥላለን ብለው የተነሱትን ሃይሎች የማይደግፍበት ምክንያት ቢኖረው እንኳ ከመርህ አንጻር ሊቃወም የሚችልብት ምንም በቂና ውሃ የሚቋጥር አሳማኝ ምክንያት ባለመኖሩ ሂደቱን በጥንቃቄ ይከታተላል። በዚህ የስልጣኔና የጥበብ ዘመን ላይ ቆመን ከቶስ ስል አመጽ ትግል ማንሳት ለምን አስፈለገ ጦርነት የሰውን ልጅ የሚበላ እሳት ነው። አመጽ ሃገር የሚያወድም መሠረተ ልማትን የሚንድ ኋላቀር መፍትሔ ነው፤ የሰላሙን ትግል ማበረታታት ሲገባ ለምን የአመጽ መንገድ እንደ መፍትሔ ይቀመጣል የሚሉ ወገኖች በርካቶች ናቸው። እርግጥ ነው ዲያቢሎስ ካልሆነ በቀር ጦርነትን መልካም ነው የሚል አንዳችም ጤነኛ አዕምሮ ያለው ፍጡር አለ ለማለት አይደፈርም። እንደምኞታችን ነገሮች በተቃውሞ ሠልፍና በሕዝባዊ እንቢተኝነት ቀለውልን ከላያችን የተጫነው ግፈኛ አገዛዝ አሽቀንጥረን ብንጥል መልካም ነበር። ይህ ግን ቀላል ሆኖ አልተገኘም የተከፈለውና በመከፈል ላይ ያለው መስዋዕትነት አንሶ አልነበረም አመጽ ታሳቢ የሆነው። ሃገራችንን የወረረው የወያኔ ቡድን ፖለቲካና ርዕዮተ ዓለምን መሠረት ያደረገ ሣይሆን ፤ የዘር አመለካከትን ዶግማና ቀኖናው በማድረግ ኋላቀር አካሄዱንና፤ ኢ ዲሞክራሲያዊነቱን የተቃወመውን ወገን በሙሉ የሚመለከትበት ሸውራራ አተያይ ፀረ ትግራይ በሚል በመሆኑ ከእንዲህ አይነቱ ጠባብና ድኩማን አመለካከት ባለው ሃይል ከሚመራ ቡድን ጋር የሚደረግ ስልጡን የፖለቲካ ትግል ውጤቱ ፍሬ አልባ በመሆኑ ሊገዳደረው የሚችል የሃይል እንቅስቃሴ አማራጭነቱ ሁሉን ወገን ከተረዳው የከረመ ቢሆንም አለመታደል ሆኖ የትግሉን እንቅስቃሴ ማቀናበሪያ ወሳኝ ኮሪደር በማግኘት ዙሪያ ስንቸገርና ባለውም ጠባብ አማራጭ ለመጠቀም ሳንችል የቆየንባቸው ትርምስ የተሞላ ሰፊና ወርቃማ ግዜያቶች ባክነዋል። አመጽ የጭቁኖች ድምጽ ነው ሲል የተናገረው ጠቢብ ማን ነበር ፤ አዎን አመጽ የሰውነት ክብርን ማረጋገጫ የነፃነት እስትንፋስ ማግኛ የባርነት ሰንሠለትን የሚበጥስ ጽኑ መዶሻ ነው። በሃገራችን የዛሬን አያድርገውና እንኳን ሃብትና ንብረቱ እየተቀማ ከነ ቤተሰቡ ጎዳና ሊጣል ቀርቶ ክፉ ቃል ተናግሮ ስብዕናውን የተዳፈረውን አደብ ሳያስገዛ የማይኖር ከምንም ነገር በላይ ለክብሩ ዘብ የሚቆም ማንነቱ ተዋርዶ በሞቀ ጎጆው ከመኖር ይልቅ ክብሩን ለማስመለስ ዱርቤቴ ማለትን የሚመርጥ ጀግና ሕዝብ እንደ እባብ ተሽሎክሉኮ በገባው የማንም መደዴና ቀን የሰጠው ወፍዘራሽ ዘረኛ የወያኔ መቀለጃ ሆኖ ለስደት ለሞት ለእስርና ለምድራዊ ስቃይ የተዳረገው መብቱን ለማስከበር አመጽን አማራጭ ባለማድረጉ መሆኑን እያየንው ነው። ወያኔዎች በለስ ቀንቶዐቸው ድፍን ኢትዮጽያን ሲወሩ በየሄዱበት ያገኙትን አሮጌ አካፋና ቀደዳ በርሜል ሳይቀር እየጫኑ ወደትውልድ ስፍራቸው ሲያግዙ ከነበረበት ቅራቅንቦ ሰብሳቢነት እድሜ ለታላቋ ሃገራችን ዛሬ ይህው እኒያ ከገላቸው እድፍና ከጎፈሬያቸው ተባይ ውጪ የረባ ጃኬት እንኳ ያልነበራቸው ሽፍቶች ይህው ዛሬ ድፍን ሃገር በጠኔ እየተመታ በረሃብ አለንጋ በሚለበለብበት ልጆቹን በፈረቃ የሚቀልብበት የኑሮ ምስቅልቅል ውስጥ ወድቆ ልጆቹ በየትምህርት ቤቱ ደጃፍ ረሃብ አዙሮ እየጣላቸው ባለበት ሁኔታ ላይ የወያኔው አባላት ጉቶ እየሞቁ ድብዳብ ላይ ተወልደው እዛው አጎዛ ላይ እንዳላደጉ ይህው የህዝብን ሃብት በመዝረፍ በህንጻ ላይ ህንጻ በሃብት ላይ ሃብት እያከማቹ ከራሳቸው አልፈው በድብቅ ላስቀመጧቸው እቁባቶቻቸው ወርቅና አልማዝ መኪናና ቪላ ስጦታ የሚያቀርቡበት ታጋይ ከበርቴዎችና ልማታዊ ዘራፊዎች ሕገ ወጥ ብልጽግና አካብተው ቅንጦት የሚያደርጋቸውን ባሰጣበት በዚህ ወቅት ትውልዱ ኑሮ ዳገት ሆኖበት የከፋውን ስደት ተያይዞት የሲናይ በርሃ አሸዋ ሲሳይ የቀይባህር አሳ ቀለብ እየሆነ እንደወጣ የቀረው የእምዬ ኢትዮጽያ ልጅ የሚደርስበት ሰቆቃ ዓለምን እስኪሰለች ድረስ የተለመደ የሰርክ ተግባር በመሰለበት በዚህ ዘመን ፤ በሃገር ውስጥ ያለው በገፍ በሚቀርብለት ጫት ደንዝዞ በምዕራቡ ዋልጌ ባህል ነፍዞ ከሞቱት በላይ ከቆሙት በታች በሆነ የሞራልና የተስፋ መቁረጥ ጭለማ ተውጦ የትግሬው ነጻ አውጪ አባላት ልጆች ከህዝብ በሚዘረፍ ገንዘብ በአውሮፓና በኣሜሪካ ውድ ኮሌጆች እንዲማሩ እየተደረገ ባለበት የፋሽስት አገዛዝ ውስጥ የአንድ አናሳ ብሄር ሰዎች ተጨፍልቆ እየቃተተ በስቃይ በሚኖርበት ሁኔታ ውስጥ ህዝባችን ቢያምጽ ይነሰው በእውነቱ ይህ ትውልድ እነዚህን የቀን ጅብ ወያኔዎች ለመታገል ከሰይጣንስ ጋር ቢተባበር ከቶ ወንጀሉ ምኑ ላይ ነው? ተወልደው ካደጉበት ጎጆ ቀልሰው ትዳር ይዘው ጫካ መንጥረውና ከአውሬ ታግለው ከባዱን የኑሮ ዳገት በላብ በወዛቸው አቅልለው በሰላም ሃገሬ መንደሬ ብለው የእርሻን ጥበብ የአኗኗር ዘይቤን ሃይማኖትንና ግብረገብነትን በየሄዱበት አስተምረው በቋንቋና በባህል የተለያቸውብ ወገን የራሳቸው አድርገው ተዛምደውና ተጋብተው በሰላም ለዘመናት ከኖሩበት ቅዬ ሃገራችሁ አይደለም በሚል ያፈሩትን ሃብት ነጥቆ ተማሪዎች ከትምህርታቸው በግድ እንዲፈናቀሉ በማድረግ በክፋትና ቂም በቀል አንድን ህዝብ ለማጥፋት የሚያደባውን እርጉሙን የትግሬ ነጻ አውጪ ቡድን ይህ ሕዝብ መፋለም ይነሰው በጉራፈርዳ በቤኒሻንጉል በአፋርና በጋንቤላ እንዲሁም በሌሎች ቦታዎች የተፈጸመው የዘር ማጥፋትና ሁን ብሎ በድህነት የመቅጣት ወያኔያዊ ሴራ በእውነቱ ከወንጀልም ወንጀል ከሃጢያትም ሃጢያት የሚሆነው ይህንን ሳጥናዔላዊ ቡድን አለመታገል ብቻ ነው። ነብሳቸውን ይማረውና አያቴ ‘’ ጣሊያን ምን አጠፋ በከንቱ ኩነኔ ሃገሩን አጠፉት መለስና ላይኔ’’ ብለው ነበር ያኔ ገና ወያኔ ሃገር ስትወር ፋሽስት ጣሊያን ያልፈጸመውን ግፍ ኦርቶዶክስና አማራ የሚባል ተቋምና ህዝብን ለማጥፋት እቅድ ነድፎ መርዝ አዘጋጅቶ የመጣን አርዮሳዊ ሃይል ለሺህ ዘመናት የውጪና የውስጥ ሃይሎችን በጽናት በመመከት ህልውናዋን አስጠብቃ የኖረችውን የታሪክ ማህደሯን ቅድስት ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን እንድትከፋፈል የዘረኞች ምሽግ በመሆን ሃዋርያዊ ሃላፊነቷን ዘንግታ የጥፋት አላማው ማራመጃ ለማድረግ በመለመላቸው ጥቅመኛና ዘረኛ ጻጻሳትና ፓትርያርክ ተብዬ በማዘጋጀት በቤተክርስቲያኒቱና በምዕመኑ ላይ ሲደርሰ የቆየው በደልና ግፍ በቀላሉ ተዘርዝሮ አያልቅም። ወያኔ በቤተክርሰቲያኒቱ ላይ ያለውን ጥላቻ በማስፋፋት ይደረጋል ተብሎ አይደለም ሊታሰብ እነኳ የማይሞከረውን ታላቁን የዋልድባ ገዳም ለስኳር ልማት በሚል በገዳሙና በመናኝ ባህታውያኑ ላይ የተፈጸመው ግፍ ስንቃኝ የውጭ ወራሪ ሃይል ይህን ያህል ይዳፈራልን? ታዲያስ ይህ ጉግማንጉግ ፀረ ኦርቶዶክስ የሆነ የወያኔ መንጋ ከቶስ ከሰይጣን የሚለየው በምንድን ነው? ይህንን ወንጀለኛና መንጋ ዘረኛ ይወገድ ዘንድ የዚህች ታላቅ ሃይማኖት ካህናትና ምዕመናን አድዋ ላይ ጌቶቹ ጣሊያኖችን በጸሎትና በሰይፍ እንዳሸነፈ በዚህም ሃገር በቀል የፋሽስት ሎሌን ለማስወገድ የሚደረገውን ትግል በውግዘትም በሞራልም ማገዝ ለቤተክርስቲያኗ ሰላም መረጋገጥን ለምዕመኖቿ መረጋጋትን የሚያስገኝ ትርጉም ያለው መልካም ሁኔታ ሊገኝ የሚችለው ይህ የዘረኛ መንጋ ተጠራርጎ ሲወገድ ብቻ በመሆኑ ይህንን ትግል ማገዝ የቤተክርስቲያኒቱና የምዕመናኑ መንፍሳዊ ግዴታ ጭምር ነው። የሃይማኖት ተቋማትን ማጥፋት የትግራይ ነጻ አውጪ ግንባር እኩይና ሠይጣናዊ አላማ ሌላው ያነጣጠረበት የኢትዮጽያ ሙስሊም ማህበረሰብ ከአመታት በፊት ይህው ከፋፋይ ዘረኛ የወያኔ ቡድን የሙስሊሙን ማህበረሰብ የስልጣኑ ማደላደያ በማድረግ ከጎኑ ለማሰለፍ የሞከረበት እኩይ አላማው ከቅርብ አመታት ወዲህ ከታወቀ በኋላ መላው ሙስሊም በአንድ ድምጽ ያቀረበውን የሃይማኖት ነጻነት ጥያቄ በሃይለ ለመጨፍለቅ ከምዕመኑ ጋር ያደረገው ትንቅንቅ የሙስሊም ወንድሞቻችን ዓለምን ያስደመመ እጅግ ዘመናዊና ሰላማዊ የትግል እንቅስቃሴ ቢያደርጉም ጨዋነትን ምንም ያህል መርሐቸው ቢያደርጉም የወያኔ ቡድን ሠላማዊ ቋንቋ የሚገባው ባለመሆኑ ለሠላት የወጣውን የሙስሊም ማህበረሰብ ህጻን ከአዋቂ ሣይመርጥ በተለያዩ ቦታዎች የፈጸመውን ጅምላ ፍጅት የምታስታውስ ሙስሊም ወገን ይህንን የደደቢት ጭራቅ ለማስወገድ የሚደረገው ትግል በመንፈሳዊ ቡራኬም ሆነ በቀጥተኛ ተሳትፎ ክንድህን ሠብስበህ እንዳትታገለው ከቶስ የሚያግድህ ምንድነው? እየተጨቆኑ መኖር ለሃገርህና ለእምነትህ ታግለህ በክብር ማለፍ ነው። ለማጠቃለል ኢትዮጽያ እንደሃገር ትቀጥል ዘንድ ትውልዷም ተሰዶ ከማለቁ በፊት ይህን ሃገር አፍራሽና መንጋ ቅጥረኛ ከቅድስት ሃገራችን ለማስወገድ እየተካሄደ ያለውን ማንኛውም እንቅስቃሴ ዘር ሃይማኖት ሳንለይ በጋራ ቆመን በጽናትና በብርታት የመደገፍ የማበረታታት የማገዝ ታሪካዊም ሞራላዊም ሆነ መንፈሳዊ ግዴታ አለብን። በትግል አለም መውደቅ መነሳት ያለና የነበረ በመሆኑ ትላንት በሄድንባቸው መንገዶች ውጤት ባናገኝም ስልታችንን በማስተካከል ጥበብ በተሞላበትና ቁርጠኝነት ባለው መልኩ እንጓዝ ዘንድ መሪ ሃይል ሆናችሁ የወጣችሁ ሃይሎች በየትኛውም የትግል ስልትና ያላችሁ ያለ የሌለ ሃይላችሁን በማስተባበር የወያኔን ተፍጻሜተ መንግስት ለማቅረብ የሚረዳ አመራር በመቀየስ ታግላችሁ እንድታታግሉን ግዜው ግድ ይላችኋል። ታላቁ ደራሲ ኦሮማይ በሚለው መጽሃፉ የሳላቸው የገሃዱ ታሪካችን አካል የነበረው ቀይ እንቡጥ የተባለው በለጋ ወጣቶች የተመራው የሃገር ፍቅር ሰራዊት ውጤቱ የማታ ማታ ቢበላሽም በለጋ እድሜያቸው በቆራጥነትና በጀግንነት አንድ ስትራቴጂክ ተራራ ለማስለቀቅ የከፈሉት ወደር የሌለው መስዋዕትነት ይህ ትውልድ ዞር ብሎ በማሰብ ነፃነቱን ረግጠው በሃገሩ ባይተዋር ባደረጉትና ሃገራዊ ድርሻውን ነጥቀው ባቋቋሙት የንግድ ኢንፓየር እነሱ በቁንጣን ሲወጠሩ የሃገሬ ወጣት ከረሃብ ጋር ሲታገል በየድልድይ ስር የሚያድርበት የአፓርታይድ አገዛዝ እንዲያከትም መፍትሄው ያለው በአዲሱ ትውልድ መዳፍ ውስጥ በመሆኑ ያአህዛብ አሽከርና የችጋር ጓደኛ ሆኖ ተሰቃይቶ ከመሞት ታሪክ ሰርቶ ለታሪክም ለህሊናም የሚጠቅም በጎ ተግባር ፈጽሞ ለመገኘት በሚቻለውና በማንኛውም መንገድ የሚደረገው ትግል በማገዝ ህዝባችንን ልንታደግ ሃገራችንን ልንጠብቅና ሃይማኖታችንን አስከብረን በነጻነት እንድንኖር ወያኔን ለማስወገድ የሚካሄደውን ሁለገብ ትግል በትጥቅ ይሁን በሰላም ከኤርትራ ይሁን ከሱዳን ከሱማሌ ይሁን ከጅቡቲ በሚነሳ የአመጽ ሃይል ይሁን በሕዝባዊ ንቅናቄ ሁሉን ባለን አቅምና ጉልበት ልናግዝ ታሪክ ትውልድ ሞራልና መንፈሳዊ ሕይወታችን ግድ ይለናል። በጽናትና በጋራ ቆመን ጠላቶቻችንን ለመደምሰስ እግዚያብሄር ሃይልና ብርታት ይሁነን።

No comments:

Post a Comment