Friday, September 20, 2013

የኢትዮጵያ አየር መንገድ አውሮፕላን በሞተሩ ላይ ባጋጠመው እክል ማልታ ላይ ለማረፍ ተገደደ


አዲስ አበባ ፣ መስከረም 10 ፣ 2006 (ኤፍ.ቢ.ሲ) ንብረትነቱ የኢትዮጵያ አየር መንገድ የሆነ ቦይንግ 757-200 አውሮፕላን ባጋጠመው ችግር ማልታ ላይ አረፈ። ትናንት በአውሮፕላኑ የቀኝ ሞተር ላይ በደረሰበት ድንገተኛ ችግር ለማረፍ ተገዷል። ከሮም ወደ አዲስ አበባ ይበር የነበረው አውሮፕላን 135 ሰዎችን አሳፍሮ ነበር። አውሮፕላኑ በማልታ አየር ማረፊያ ለሞተሩ ጥገና ከተደረገለት በኋላ ወደ አዲስ አበባ በሯል። ከአየር መንገሩ እስከ አሁን የተሰጠ ምግለጫ የሌለ ሲሆን መረጃውን እንዳገኘን የምናቀርብ ይሆናል። ምንጭ - www.timesofmalta.com

No comments:

Post a Comment