Sunday, September 15, 2013

<የእባብ ልጅ እፉኝት !! ስለ አቶ ሽመልስ ከማል

<የእባብ ልጅ እፉኝት !! ስለ አቶ ሽመልስ ከማል (አቶ ሽመልስ ኃይለየሱስ) ጥቂት መረጃዎች ሃጂ ከማል ሐጂ በብሄር ቀቤና ሲሆኑ ሚስታቸው (የአቶ ሽመልስ ከማል እናት) ወሮ አበባ ሁሴን ደግሞ በአባት የጅማ ኦሮሞ፣ በእናት ወርጂ ናቸው። ሃጂ ከማል ሃጂ ኢትዮጵያ ሃጃጆችን መርተው በሄዱበት ወቅት ከንጉስ ፋይሰል ጋር ፎቶ ተነስተዋል። ገና ከጅምሩ የኃይለ ስላሴ ቤተመንግስት ድረስ ይገቡ ነበር። የሙስሊሙን እንቅስቃሴ ለማፈን መሳሪያ ሆነው ሰርተዋል። በመጨረሻ ንጉሱ ክርስትና ያስነሷቸው ሲሆን ቤተሰባቸውን ሁሉም ክርስትና አስነስተዋል። ወሮ አበባ ሁሴን ለሃጂ ከማል ሃጂ አራት ወንድና አራት ሴት ልጆችን
ወልደዋል። ሃጂ ከማል ክርስትና ከተነሱ በኋላ ኃይለየሱስ ተሰኝተዋል። አንዳንዶች ‹‹ቀድሞውኑ በሙስሊም ስም (ሽፋን) ኖሩ እንጂ ሙስሊም አልነበሩም፤ ኢስላምን የሚያጥላላና የሙስሊሙን የመብት ጥያቄ የማፈን ስራ ሲሰሩ ራሳቸውን ሃጂ ከማል ሃጂ ብለው ይጠራሉ እንጂ መች ሙስሊም ነበሩ?›› ይሏቸዋል። የግለሰቡ መኖሪያ ቤት ጥቁር አንበሳ ጋር (ሜትሮሎጂ) እና የስልጤ መስጅድ መካከል ነበር። ግለሰቡ ሙስሊሙን ለማጠቃት ለአፄ ኃይለስላሴ ወሳኝ ስራ ስለሰሩ በ1956 የሰላም ማህበር ሲዘጋ በአውራጃ ገዥነትና የንብረት ክፍል ኃላፊነት ቦታዎች ላይ ተሹመው ነበር።ምንሊክ ሳልሳዊ ስለ አቶ ሽመልስ ከማል ጥቂት መረጃዎች ‹‹አቶ ሽመልስ ከማል ሪፖርተር ጋዜጣ ላይ ተቀጥረው ከመስራታቸውም ባሻገር በጊዜው መንግስትን ይተች የነበረውን ‘’ኒሻን’’ የተባለ የራሳቸውን ጋዜጣ እስከማቋቋም የደረሱ ሲሆን፤ አቶ ሪድዋን ሁሴንም እንዲሁ ተቀዋሚ ፓርቲ መስርተው የፓርቲ ሊቀመንበር ከመሆናቸውም ባሻገር በ1992 ዓ.ም ፓርቲያቸውን ወክለው ለምርጫ በመቅረብ የኢህአዴግ ተወዳዳሪን በማሸነፍ ፓርላማ እስከመግባት እንደደረሱ ይታወሳል። እነዚህ ግለሰቦች ገዢው ፓርቲ ካመቻቸላቸው የጥቅመኝነት ስልጣን የሚያመጣላቸውን ጥቅም ተከትሎ ፍላጎታቸውን ማርካት ሲጀምሩ መሰረታዊ ከሆነው ለሰው ልጆች የመቆርቆር ሃሳባቸው ጋር እረፍት የሚነሳ የህሌና ጫና ውስጥ መግባታቸውን አይቀሬ ያደርገዋል።›› (ሙሉነህ አያሌውና ኃ/መስቀል በሸዋም የለም፣ የመለስ ውርሶች ታህሳስ 2005 ገፅ 210) • የአቶ ሽመልስ አባት ሃጂ ከማል ሃጂ ሁለት መፅሃፍ የፃፉ ሲሆን የመጀመሪያው ‹‹የመካና መዲና ሚስጢር›› ሲሰኝ መፅሃፉ ከአዲስ አበባ ተነስተው ለሃጅ በሚል መካ የተጓዙበትን ሂደት ይተርካል። መጽሀፉ በተዘዋዋሪና በቀጥታ ኢስላምን ያጥላላል። ‹‹ለምን ድሬ ሼህ ሁሴን እያለ ሃጅ እንሄዳለን? በደንብ ብንይዘው አናጅናን (ሼህ ሁሴን) ለቱሪዝምና ለሃጅ ምትክ አድርገን እንጠቀማለን›› የሚል መልእክት ያስተላልፋል፡፡ ከዚህም አልፎ ‹‹ነብዩ (ሰዐወ) ድሬ ሼህ ሁሴንን ሳይዘይር ሃጅ የሄደ ሃጁ ተቀባይነት የለውም ብለዋል›› እስከማለት የደረሰ ቅጥፈት አካቷል፡፡ ‹‹ሙስሊም ኢትዮጵያውያን ስለምን የዓረብኛ ስም ያወጣሉ? ለምን የአማርኛ መጠሪያ ስም አያወጡም?›› እስከማለት ይደርሳል፡፡ ኢስላም ሴቶችን እንደሚበድልና ሌሎች ተመሳሳይ ነጥቦችንም ይዳስሳል። ሌላኛው መፅሃፍ ‹‹የህሊና ግዳጅ›› የሚሰኝ ሲሆን ዓላማ አድርጎ የተፃፈው ‹‹የአፄ ኃይለስላሴ መንግስት ሙስሊሞችን ይበድላል›› ለሚሉ ሙስሊሞች ምላሽ እንዲሆን ነው። ጸሐፊው በመፅሃፋቸው ‹‹የአፄ ኃይለ ስላሴ መንግስት ሙስሊሙን ይበድላል ብለው ሃጅ ላይ ወረቀት የበተኑና በውጭ ሚዲያዎች የፃፉትን የተሳሳተና ሃሰተኛ ድርጊት እያየሁ አላህ የውመል ቂያማ እንዳይጠይቀኝ ነው ይህን የፃፍኩት›› ይሉናል። ‹‹ሰሃቦችን በስደት ሲመጡባት ያስተናገደች ሃበሻ እንዴት ሙስሊሞችን እየበደለች ነው ተብሎ ይፃፋል?›› ሲሉም ይሞግታሉ። ሁለቱም መፅሃፍቶች ያኔ በንጉሱ ዘመን ህዝበ ሙስሊሙን ያስቆጡ ነበሩ። • ግለሰቡ ከ1953-1956 ‹‹የሰላም ማህበር›› የተባለው የሙስሊሞች ማህበር መሪ ነበሩ። ድርጅቱን ሙስሊም አባቶች የእስላም ማህበር ብለው ሲያቋቁሙ አፄ ኃይለ ስላሴ ስያሜውን ‹‹የሰላም ማህበር›› በሚል እንዲቀየር አስገደዱ። በድርጅቱ ውስጥ አመዴ ለማ (ፊታውራሪ) እና ሃጂ በሽር ዳውድን ጨምሮ በርካታ አባቶች ነበሩ። ስለ ግለሰቡ (ሐጂ ከማል) መሰሪነት ፊታውራሪ አመዴ ለማና ሃጂ በሽር ዳውድ ግለ ታሪካቸውን በፃፉበት መፅሃፍቶቻቸው ጠቅሰዋል። ልጃቸውንና የኢህአዴግ ባለስልጣንን አቶ ሽመልስ ከማልን በመፍራት ስማቸውን ሳይጠቅሱ ድርጊቱን ብቻ የጠቀሱ ቢሆንም ሃጂ በሽር ዳውድ ግን በረቂቁ ላይ ጠቅሰውት በታተመው ላይ ስማቸው ወጥቷል። ‹‹የግለሰቡ ስም ረቂቁን ባረመው ዶ/ር ኢድሪስ ሙሀመድ ተቀንሶ ይሆን?›› የሚለው ጥያቄ እንዳለ ሆኖ ስማቸው ቢወጣም ድርጊታቸው ግን በመጽሀፉ ውስጥ ተጠቅሷል።ምንሊክ ሳልሳዊ • ሃጂ ከማል ሐጂ በብሄር ቀቤና ሲሆኑ ሚስታቸው (የአቶ ሽመልስ ከማል እናት) ወሮ አበባ ሁሴን ደግሞ በአባት የጅማ ኦሮሞ፣ በእናት ወርጂ ናቸው። ሃጂ ከማል ሃጂ ኢትዮጵያ ሃጃጆችን መርተው በሄዱበት ወቅት ከንጉስ ፋይሰል ጋር ፎቶ ተነስተዋል። • ገና ከጅምሩ የኃይለ ስላሴ ቤተመንግስት ድረስ ይገቡ ነበር። የሙስሊሙን እንቅስቃሴ ለማፈን መሳሪያ ሆነው ሰርተዋል። በመጨረሻ ንጉሱ ክርስትና ያስነሷቸው ሲሆን ቤተሰባቸውን ሁሉም ክርስትና አስነስተዋል። ወሮ አበባ ሁሴን ለሃጂ ከማል ሃጂ አራት ወንድና አራት ሴት ልጆችን ወልደዋል። ሃጂ ከማል ክርስትና ከተነሱ በኋላ ኃይለየሱስ ተሰኝተዋል። አንዳንዶች ‹‹ቀድሞውኑ በሙስሊም ስም (ሽፋን) ኖሩ እንጂ ሙስሊም አልነበሩም፤ ኢስላምን የሚያጥላላና የሙስሊሙን የመብት ጥያቄ የማፈን ስራ ሲሰሩ ራሳቸውን ሃጂ ከማል ሃጂ ብለው ይጠራሉ እንጂ መች ሙስሊም ነበሩ?›› ይሏቸዋል። • የግለሰቡ መኖሪያ ቤት ጥቁር አንበሳ ጋር (ሜትሮሎጂ) እና የስልጤ መስጅድ መካከል ነበር። ግለሰቡ ሙስሊሙን ለማጠቃት ለአፄ ኃይለስላሴ ወሳኝ ስራ ስለሰሩ በ1956 የሰላም ማህበር ሲዘጋ በአውራጃ ገዥነትና የንብረት ክፍል ኃላፊነት ቦታዎች ላይ ተሹመው ነበር። • በደርግ ጊዜ ጡረታ ወጥተው ታመው ወደ ቤት ገቡ። ለሁለት ወራት ያክል በአልጋ ላይ ተኝተው አንዲት ቃል ሳይወጣቸው በመጨረሻ ሞቱ። ሙስሊሞች ‹‹ዱዓችን ሰራ›› ብለው አላህን አመሰገኑ። በተክለ ሀይማኖት ቤተክርስቲያንም ተቀበሩ። • ግለሰቡ ከመሞታቸው አስቀድሞ ገና ታመው በተኙበት ነበር ባለቤታቸው ወ/ሮ አበባ ሳዑዲ ዓረቢያ ይኖሩ ከነበሩና አቶ ከድር ማሜ ከተሰኙ የባሌ ሰው ጋር ቅርርብ የጀመሩት። ቅርርባቸው በመጀመሪያ ግለሰቡ ለእረፍት ሲመጡ የእሳቸውን ዕቃ በማሻሻጥ ላይ ነበር የተመሰረተው። በኋላ ላይም ግለሰቡ ወ/ሮ አበባን ጨምሮ ቤተሰቡ ወደ ኢስላም እንዲመለስ አደረጉ። ከአቶ ሽመልስ በስተቀርም ሁሉም ሰለሙ። ወ/ሮ አበባም ፀጉር መግለጥና ሱሪ መልበስ ትተው ሂጃብ መልበስ ጀመሩ። በኋላ ላይም ከአቶ ከድር ማሜ ጋር ተጋቡ፡፡ • ግለሰቡ ወ/ሮ አበባን ይዘው ወደ ሳዑዲ ገቡ። በዚያም ወ/ሮ አበባ እየሰሩ ልጆቻቸውን ማሳደግ ጀመሩ፡፡ የበኩር ልጅ የነበሩት አቶ ሽመልስ ግን ሊሰልሙ ፈቃደኛ አልነበሩም። እናታቸው ወ/ሮ አበባ ‹‹ሽመልስ ግትር ነው›› ይሉ ነበር። • በህግ የተመረቁት አቶ ሽመልስ በከፍተኛ ፍ/ቤት ይሰሩ ነበር። ከዚያም ሪፖርተር ጋዜጣ፣ ቀጥሎም ኒሻን ጋዜጣ ላይ ይሰሩ ነበር። በዚህ ጊዜ ነበር ኢህአዴግ አስሮ የገረፋቸው። ከእስር ሲለቀቁ አቶ ሽመልስ ኢህአዴግን ተቀላቀሉ። በዚህን ጊዜ ነው ‹‹ሰለሙ›› የተባለው፤ ቤተሰቦቻቸው ግን አሁንም ድረስ ‹‹የሱ እስልምና ያን ያህል ነው›› ይላሉ (እናቱን ጨምሮ)። የአቶ ሽመልስ ወንድም መሰለ ኃይለየሱስ ሲሰልሙ አብደላ ሃጂ ከማል ተብለው ነበር፡፡ ሌላኛዋ መስከረም የምትባለው ደግሞ እንግሊዝ ኗሪ ናት፤ ሌላኛው ወንድማቸው የአየር መንገድ ቴክኒሻን የነበሩ ሲሆን እንግሊዝ ገብተዋል፤ ሌላኛው ደግሞ ኤሌክትሪሻን ሲሆኑ የሚኖሩት በአሜሪካ ነው፡፡ ወ/ሮ አበባም ልጆቻቸው ጋር አሜሪካና እንግሊዝ ይመላለሱ ነበር፡፡ የአቶ ሽመልስ ሌላኛዋ ሴት እህት ደግሞ በገነት ሆቴል ውስጥ፣ ኋላ ላይ ደግሞ መሿለኪያ አካባቢ ጅምር ቤት ነበራት፤ ባሏ ጀርመን ሃገር ስለሚኖር ጀርመን ትመላለሳለች። • ከቤተሰቡ ኢስላምን አጥብቀው የያዙት ኢንጅነር አብደላ ከማል (ቀድሞ መሰለ ኃይለየሱስ ይባሉ የነበሩት) ናቸው፡፡ ሃይማኖተኛ መሆናቸውን ብዙዎች ይመሰሩላቸዋል። • አቶ ሽመልስ ‹‹ሰለመ›› ከተባሉ በኋላ ከአህባሽ አደሬ ጓደኞቻቸው ጋር ይቅማሉ፤ ያጨሳሉ፤ ከነሱ ስርም አይጠፉም፤ በዚህ ጊዜ ነበር ወደ አህባሽ እምነት የገቡት። • በ1992 ምርጫ ‹‹ለሙስሊሙ እሰራለሁ›› በሚል የአካባቢው ሙስሊሞች በመስጅድ ጀምዓ ፖስተር አሳትመውላቸው፣ በራሪ ወረቀት በትነውላቸው እንዲመረጡ ቀስቅሰዋል። ከተመረጡ በኋላ ግን ለግል ጥቅማቸውና ለፓርቲው መስራታቸውን ቀጥለዋል። • በ1996 ሸህ አብደላ አል-ሃረሪ ወደ ኢትዮጵያ በመጡበት ጊዜ አቶ ሽመልስ ከማል ግለሰቡን ቦሌ ጃፓን ኤምባሲ አቅራቢያ ባለ ቪላ ቤት ሄደው ከጎበኙት ባለስልጣናት አንዱ ነበሩ። ከዚህ ጊዜ ጀምሮ ነበር ፓርቲው ውስጥ ያሉትን ሙስሊሞች እኔ ብርቱና ታዋቂ ሸህ (ሸህ አብደላ አል-ሃረሪን) ይዣለሁ፤ እናንተም እርሳቸውን በሸህነት ያዙ፤ ያለ ሸህ እንዴት ይዘለቃል?›› በማለት ለማሳመን መጣር ጀመሩ፡፡ በኋላ ላይም በመኖሪያ ቤታቸውና በቢሮ የሸህ አብደላ አል-ሃረሪን ፎቶግራፍ በፍሬም በማድረግ ለጥፈዋል። • አቶ ሽመልስ ከማል ከአህባሾች ጋር እንቅስቃሴያቸውን የቀጠሉ ሲሆን በተለያዩ አጋጣሚዎች መንግስት እያደረገ ባለው አህባሽን የማስፋፋት ስራ ላይ ተጠይቀው (በግል) ‹‹ልክና ተገቢ ነው፤ የሼኻችንን ስም የሚያጠፉት ውሃብዮች ናቸው፤ የሚጠቀስባቸው ሁሉ ሃሰት ነው›› በማለት ተከላክለዋል። • አቶ ሽመልስ ከማል ከዚህ ቀደም ከጋብቻ ውጭ አንድ ልጅ የወለዱ ሲሆን ያሳድጉ የነበሩትም እናታቸው ነበሩ። በአሁኑ ሰዓት አቶ ሽመልስ ልክ እንደ አባታቸው ከመንግስት ጋር ሆነው ፀረ-ሙስሊም ንግግርና ድርጊት እየፈፀሙ ይገኛል። • የአባትየው ሃጂ ከማል ሃጂ መፅሃፍቶች ሁለቱም አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ኬኔዲ ላይብረሪ ውስጥ ይገኛሉ። ‹‹የመካና መዲና ጉዞ ሚስጥር›› ከሚለው መጽሀፋቸው ኮት ተደርጎ ‹‹የኃይለ ስላሴ ዕቅድ በመጅሊስ ተሳካ›› በሚል ርዕስ ሚሌኒየም ላይ ተፅፎ ነበር። ከዚያ አርቲክል ሃሳቦችንና ጥቅሶችን ማግኘት ይቻላል። በመፅሃፍቶቹ ላይ የግለሰቡ ፎቶግራፍ ከነቤተሰባቸው (በ1960ዎቹ የተነሱት) አለበት። ካዕባ ፊት ለፊት የተነሱት ፎቶግራፍም አለበት። በመልክ አባትና ልጃቸው አቶ ሽመልስ ኮፒ ናቸው፤ በመልክም ሆነ በግብር! • የፊታውራሪ አመዴ ለማና የሃጂ በሽር ዳውድ መፅሃፍም እንዲሁ በገበያ ላይ አለ። • በ1990ዎቹ ሂክማ ጋዜጣ ላይ ‹‹ሃጂ ከማል ሃጂ ዛሬም ይኖሩ ይሆን?›› በሚል ርዕስ ስለ ግለሰቡ ድርጊትና ታሪክ ተፅፎ ነበር። • የአፄ ኃይለስላሴ ደህንነት ለንጉሱ በፃፈው ሪፖርት ላይ ስለሃጂ ከማል ሃጂ ተጠቅሷል። ‹‹ሙስሊሙን እንዴት እንምታው?›› የሚል ነበር የሪፖርቱ ዓላማ። ሪፖርቱ ብሄራዊ ቤተ መፅሃፍትና ቤተ መዛግብት (ከኢቲቪ ጀርባ) ውስጥ በልዩ ጥበቃ ክፍል ውስጥ ይገኛል።ምንሊክ ሳልሳዊ

No comments:

Post a Comment