Monday, October 7, 2013

አምባሳደር ዶ/ር ሙላቱ ተሾመ ፕሬዘዳንት ሆነው ተሾሙ

ዛሬ መስከረም 27 ቀን 2006 ዓ.ም. ለ12 ዓመታት በፕሬዘዳንትነት ያገለገሉት መቶ አለቃ ግርማ ወልደጊዮርጊስ ተሰናብተው በምትካቸው አዲስ ተሾመ፡፡
በተለይ 547 አባላት ያሉት የህዝብ ተወካዮች እና 187 አባላት ያሉት የፌዴሬሽን ምክር ቤት የስራ ዘመን መጀመሩን ያበሰሩት ፕሬዘዳንት ግርማ ወ/ጊዮርጊስ የስንብት ንግግራቸውንም አድርገዋል፡፡ በምትካቸውም ለቀጣዩ 6 ዓመታት የሀገሪቱ ርዕሰ ብሔር(ፕሬዘዳንት) ሆነው ለማገልገልም በቱርክ የኢትዮጵያ አምባሳደር ዶ/ር ሙላቱ ተሸመ ዊርቱ ተሾመዋል፡፡ ይሁን እንጂ በሀገሪቱ ህገ መንግስት መሰረት አዲስ ፕሬዘዳን ከቀድሞዎቹ የተለየ ምንም ዓይነት የተለየ ስራ ማከናውን የማይችሉ ሲሆን ዋነኛ ስራቸውም በጠቅላይ ሚኒስትሩ የቀረቡትን አምባሳደሮች መሾም፣ የውጭ ሀገር አምባሳደሮች በኢትዮጵያ የሹመት ደበዳቤ መቀበል፣የእንኳን አደረሳችሁ የበዓላት መልዕክት ማስተላለፍ፣ ከተጋበዙ አዳዲስ ፕሮጀክቶች ግንባታ ሲጠናቀቅ ማስመረቅ ነው፡፡ ከተጠሱት ይልቅ ርዕሰ ብሔሩ ስልጣን አላቸው የሚባለው ለተከሰሱ ሰዎች ይቅርታ ማድረግ ብቻ ነው፡፡ ይህም ቢሆን በኢህአዴግ ፍትህ ሚኒስቴር ሹሞች እና ለይስሙላ የተቋቋመው የይቅርታ ቦርድ ሲያቀርብ ብቻ የሚከናወን ነው፡፡ ስለዚህ ከአዲሱ ፕሬዘዳንት ከቀድሞ ምንም አዲስ የተለየ ነው የሚባል መልካም ነገር የሚፈጥሩበት ዕድል ሊኖር አይችልም፡፡ ምክንያቱም የስራ ድርሻቸው በህገመንግስቱ ተገድቦ የተሰጠ ቁንፅል በመሆኑና ሁሉም ስራ በኢህአዴግ ፍላጎትና ፈቃድ በ”ጠቅላይ ሚኒስትሩ” ጠቅላይነት የሚፈፀም መሆኑ በግልፅ ተቀምጧልና፡፡

No comments:

Post a Comment