Saturday, October 26, 2013

መላኩ ፈንታ ሥልጣናቸውን መከታ በማድረግ የሶስት ልጆች እናትን ከትዳሯ አፋተው አግብተዋል’’ ዐቃቤ ሕግ

‘‘መላኩ ፈንታ ሥልጣናቸውን መከታ በማድረግ የሶስት ልጆች እናትን ከትዳሯ አፋተው አግብተዋል’’ ዐቃቤ ሕግ የፌዴራሉ የሥነ ምግባርና ፀረ-ሙስና ኮሚሽን ዐቃቤ ህግ ከትናንት በስቲያ ጀምሮ በገቢዎችና ጉምሩክ ባለስልጣናት እና ግብረ አበር ባለሀብቶች ላይ የመሰረተውን ክስ በፍርድ ቤት ማሰማት ጀምሯል። የኮሚሽኑ ዐቃቤ ህግ በተለይም በአንደኛው ተከሳሽ በአቶ መላኩ ፈንታ ላይ መዝገብ ቁጥር 14356 ስር ባለው 11ኛ ክስ ውስጥ ተከሳሹ በትዳር ያለችን ሴት አስኮብልለዋል የሚል ክስ መስርቶባቸዋል። ትናንት በፌዴራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት 15ኛ ወንጀል ችሎት ክሱ ሲነበብ፤ 1ኛው ተከሳሽ አቶ መላኩ ፈንታ የስራ ኃላፊነታቸውን በመጠቀም ለስራ ጉዳይ የመጣችን ሴት፤ ትዳሯን ፈታና በትዳር ውስጥ ያፈራቻቸውን ሦስት ልጆች በትና አብራቸው እንድትሆን አድርገዋል ሲል ስልጣንን ያለአግባብ የመጠቀም የሙስና ወንጀል ፈፅመዋል ሲል ከሷቸዋል።
ወ/ሮ መቅደስ ለማ የተባሉት እኚሁ ሴት የቀድሞ ባለቤታቸውን ንብረት የሆነውን ሳንክቸሪ ኢንተርናሽናል ኃ/የተወሰነ የግል ማህበር በ2001 ዓ.ም የስራ ግብር ለመክፈል ወደገቢዎችና ጉምሩክ ባለስልጣን ሲሄዱ 144 ሺህ ብር እንዲከፍሉ በመጠየቃቸውና በዚህም ምክንያት አቤቱታ ለማቅረብ ወደ ምስራቅ አዲስ አበባ ቅርንጫፍ ለአንድ አመት ከ4 ወር መጉላላታቸውን ለማስረዳትና መፍትሄ ለማግኘት ወ/ሮ መቅደስ ለማ የአቤቱታ ደብዳቤ ይዘው ወደተከሳሹ ዘንድ በቀረቡበት ወቅት የፍቅር ግንኙነት መጀመራቸውን በክስ መዝገቡ ያትታል። በዚህም መሠረት ተከሳሽ የነበረውን ስልጣን መከታ በማድረግ ባለጉዳዩዋ ቀደም ሲል ከከፈሉት ብር ውስጥ አንድ መቶ ሺህ ብር ተመላሽ እንዲሆን አድርጓል፤ በትዳር ውስጥ ያለችን ሴትም አማግጧል ሲል የሙስና ክስ መስርቷል። ዐቃቤ ህግ በዚህ ክስ ዝርዝር ውስጥ በተጨማሪነትም ተከሳሽ በጋብቻ ውስጥ ያለችን ሴት በመንግስት ተሽከርካሪና ነዳጅ ደብረ ሊባኖስ ገዳም ክብረ በዓል ላይ እንድትገኝ ከማድረጉም በላይ ቀኑ በውል ባልታወቀበት ዕለትም፤ በጋብቻ ውስጥ የነበረችው መቅደስ ለማን በግል ሾፌሩ አማካኝነት ወደ ባህርዳር ከተማ እንድትሄድ በማድረግ ሰመርላንድ ሆቴል ለአንድ ሳምንት አብረው እያደሩ እና በሾፌሩ አማካኝነት ከተማ ውስጥ ተዝናንታለች ሲል፤ የተፈፀመው ወንጀል መንግስትና ህዝብ የጣለበትን አደራ ያለአግባብ የመጠቀም ሙስና ሰርቷል ይላል። (በእነ መላኩ ፈንታ መዝገብ ሥር ያሉትን 24 ተከሳሾች የክስ ሙሉውን ጭብጥ (በእነ መላኩ ፈንታ መዝገብ ሥር ያሉትን 24 ተከሳሾች የክስ ሙሉውን ጭብጥ እነሆ) ለፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት አዲስ አበባ የፌ/ሥ/ፀ/ሙ/ኮ/መ/ቁ. የዐ/ህ/መ/ቁ. የከ/ፍ/ቤ/ወ/መ/ቁ/ 141352 ከሣሽ ………….. የፌደራል የሥነ ምግባር እና የፀረ ሙስና ኮማሽን ዐቃቤ ሕግ ተከሣሾች ……… 1ኛ/ አቶ መላኩ ፈንታ ቻይ ሥራ፡- የኢትዮጵያ ገቢዎችና ጉምሩክ ባለሥልጣን ዋ/ዳይሬክተር 2ኛ. አቶ ገ/ዋህድ ወ/ጊዮርጊስ ወ/ሚካኤል ሥራ፡- የኢትዮጵያ ገቢዎችና ጉምሩክ ባለሥልጣን የሕግ ማስከበር ዘርፍ ም/ዋ/ዳይሬክተር 3ኛ. አቶ በላቸው በየነ ገ/ጊዮርጊስ ሥራ፡- የኢትዮጵያ ገቢዎችና ጉምሩክ ባለሥልጣን የኦዲት ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር 4ኛ. አቶ ማርክነህ አለማየሁ ወዴቦ ሥራ፡- ም/ዋና ዐ/ሕግ 5ኛ. አቶ እሸቱ ግረፍ አስታክል ሥራ፡- ገ/ጉ/ባለሥልጣን አ.አ ቃሊቲ ቅርንጫፍ የሕግ ማስከበር ኃላፊ 6ኛ. አቶ አስፋው ስዩም ተፈራ ሥራ፡- ድሬዳዋ ቅ/ጽ/ቤት የጣቢያ አስተባባሪ 7ኛ. አቶ ያዴሳ ሚዴቅሳ ዲባባ ሥራ፡- የገቢዎችና ጉምሩክ ባለስልጣን አዳማ ቅ/ፅ/ቤት ሥራ አስኪያጅ 8ኛ. አቶ አስመላሽ ወ/ማርያም ገብሬ ሥራ- የጉምሩክ ሥነ ሥርዓት አፈፃፀም የሥራ ሂደት መሪ የነበረ 9ኛ. አቶ ነጋ ገ/እግዚአብሔር ደበበ ሥራ፡- ነጋዴ 10ኛ. አቶ ከተማ ከበደ አስገልጥ ሥራ፡- የግል ባለሀብት 11ኛ. አቶ ስማቸው ከበደ ካሳ ሥራ፡- ነጋዴ 12ኛ. ዶ/ር ፍቅሩ ማሩ ወርዶፋ ሥራ፡- ሐኪም 13ኛ. ኮ/ል ኃይማኖት ተስፋዬ ገ/ስላሴ ሥራ፡- የኢትዮጵያ ሴቶች ማኅበራት ፌዴሬሽን ም/ስራ አስኪያጅ 14ኛ. አቶ ዳንኤል ገ/ኪዳን (ያልተያዘ) ሥራ፡- የግብር አውሳሰንና ምርመራ ኦዲተር 15ኛ. አቶ አውግቸው ክብረት ሥራ፡- ዐቃቤ ሕግ 16ኛ. አቶ ጌቱ ገለቴ (ያልተያዘ) ሥራ፡- ነጋዴ 17ኛ. አቶ ገ/ስላሴ ገብረ ኃ/ማርያም ሥራ፡- ነጋዴ 18ኛ. ኬኬ ኃ/የተ/የግ/ማኅበር ሥራ፡- ጄ.ኤች.ሲሜክስ ኃ/የተ/የግ/ማኅበር 19ኛ. ጄ.ኤች ሲሜክስ ኃ/የተ/የግ/ማኅበር 20ኛ. ነፃ ኃ/የተ/የግ/ማኅበር 21ኛ. ጌታስ ኃ/የተ/የግ ማኅበር 22ኛ. ኮሜት ኃ/የተ/የግ/ማኅበር 23ኛ. አቶ ፍፁም ገብረመድህን አብርሃ ሥራ፡- ነጋዴ 24ኛ. አቶ ወልደስላሴ ወ/ሚካኤል ሥራ፡- የብሔራዊ መረጃና ደህንነት አገልግሎት አማካሪ 1ኛ ክስ በ1ኛ፣ 2ኛ እና 10ኛ ተከሳሾች ላይ ብቻ ወንጀሉ በ1996 ዓ.ም የወጣውን የኢ.ፌ.ዴ.ሪ. የወንጀል ሕግ አንቀፅ 32(1) (ሀ)፣ 33፣ 411(1) (ሐ) እና 2 ላይ የተመለከተውን በመተላለፋቸው፣ የወንጀሉ ዝርዝር 1ኛ እና 2ኛ ተከሣሾች እንደ ቅደም ተከተላቸው በኢትዮጵያ ገቢዎችና ጉምሩክ ባለሥልጣን ዋና ዳይሬክተር እና ምክትል ዋና ዳይሬክተርና የሕግ ማስከበር ዘርፍ ኃላፊ ሲሆኑ፤ ስልጣንና ኃላፊነታቸውን በመጠቀም የማይገባ ጥቅም ለራሳቸው ለማግኘት ለሌሎች ሰዎችም ለማስገኘት በማሰብ፣ 10ኛ ተከሳሽም በመንግስት ሰራተኞች ብቻ በሚፈፀም የሙስና ወንጀል ልዩ ተካፋይ በመሆን፣ - 1ኛና 2ኛ ተከሳሾች በ2001 ዓ.ም በተካሄደው አራጣ አበዳሪዎችን ለሕግ የማቅረብ ተግባር በተጀመረበት ወቅት ለተከሳሹ በጥቆማ መልክ ከቀረቡት ዘጠኝ አራጣ አበዳሪዎች ስም ዝርዝር መካከል 10ኛ ተከሣሽ አራጣ አበዳሪ መሆኑን የሚያስረዱ ማስረጃዎች ቀርበውለት እያለ የተከሳሹ ጉዳይ በምርመራ ተጣርቶ ለሕግ እንዲቀርብ ማድረግ ሲገባው ከዚህ በተቃራኒው ከተከሣሹ ጋር በፈጠሩት ሥውር የጥቅም ግንኙነት ሌሎች አራጣ አበዳሪዎች ምርመራ ተጣርቶባቸው ለሕግ ሲቀርቡ ያለምንም ሕጋዊ ምክንያት 10ኛ ተከሳሽ ላይ ምርመራ እንዳይጣራና ሕግ ፊት ቀርቦ እንዳይጠየቅ በማድረጋቸው፣ - 10ኛ ተከሳሽ በበኩሉ ከላይ በተጠቀሰው ጊዜ አራጣ አበዳሪነቱን የሚያስረዱ ማስረጃዎች ቀርቦበት እያለና ሌሎች አራጣ አበዳሪዎች ሕግ ፊት ቀርበው ሲከሰሱ ከ1ኛ እና 2ኛ ተከሣሾች ጋር በስውር በፈጠረው ሚስጥራዊ የጥቅም ግንኙት በአራጣ አበዳሪነቱ ምርመራ እንዳይጣራበትና ሕግ ፊት ቀርቦ እንዳይጠየቅ የ1ኛ እና 2ኛ ተከሳሾችን ሽፋን አግኝቶ ሕገወጥ ተጠቃሚ በመሆኑ፣ በአጠቃላይ ሁሉም ተከሳሾች በሙሉ ፈቃዳቸውና ዕወቀታቸው የወንጀሉ ሙሉ ተካፋይ በመሆን በተሰጣቸው የመንግሥት ኃላፊነት ሊጠብቁትና ሊከላከሉት የሚገባውን የመንግስትና የሕዝብ ጥቅም በሚጎዳ አኳኃን በዋና ወንጀል አድራጊነት በፈፀሙት የመንግስት ስራን በማያመች አኳኃን መምራት የሙስና ወንጀል ተከሰዋል። 2ኛ ክስ በ1ኛ፣ 2ኛ፣ 3ኛ እና 11ኛ ተከሳሾች ላይ ብቻ ወንጀሉ በ1996 ዓ.ም የወጣውን የኢ.ፌ.ዴ.ሪ. የወንጀል ሕግ አንቀፅ 32(1) (ሀ)፣ 33፣ 411(1) (ሐ) እና 2 ላይ የተመለከተውን በመተላለፋቸው፣ የወንጀሉ ዝርዝር 1ኛ፣ 2ኛ እና 3ኛ ተከሣሾች እንደ ቅደም ተከተላቸው በኢትዮጰያ ገቢዎችና ጉምሩክ ባለሥልጣን ዋና ዳይሬክተር፣ ምክትል ዋና ዳይሬክተርና የሕግ ማስከበር ዘርፍ ኃላፊ እና የኦዲት ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር ሲሆኑ፣ ስልጣንና ኃላፊነታቸውን በመጠቀም የማይገባ ጥቅም ለራሳቸው ለማግኘት ለሌሎች ሰዎችም ለማስገኘት በማሰብ፣ 11ኛ ተከሳሽም በመንግስት ሰራተኞች ብቻ በሚፈፀም የሙስና ወንጀል ልዩ ተካፋይ በመሆን፣ - 1ኛ ተከሣሽ በ2003 ዓ.ም ለሆቴል አገለግሎት የሚውሉ እቃዎችን ከቀረጥ ነፃ ያስገቡ ሆቴሎች ከቀረጥ ነፃ ያስገቡትን ዕቃ ከታለመለት ዓላማ ውጭ እየተገለገሉበት ስለመሆኑ መረጃ ደርሶት ጉዳዩ በባለሥልጣኑ የኢንተለጀንስ ክፍል ጥናት እንዲደረግ ተወስኖ ጥናትና የኦዲት ክትትል ከተደረገ በኋላ ጥናት ከተደረገባቸው ሆቴሎች መካከል አንዱ ጄ.ኤች ሲሜክስ ኃ/የተ/የግ/ማኅበር (ኢንተርኮንቲኔንታል ሆቴል) ሲሆን በተካሄደው ጥናትና የኦዲት ክትትል መሠረት ወንጀል መፈፀሙን የሚያረጋግጡ ማስረጃዎች ቀርቦ እያለና ሌሎች ተመሣሣይ ድርጊት የፈፀሙ ሆቴሎች ምርመራ እንዲጣራባቸው ሲደረግ የ11ኛ ተከሣሽ ሆቴል ከቀረጥ ነፃ ያስገባቸውን ዕቃዎች ለተፈለገው ዓላማ አለማዋሉን በ26/11/2002 እና በ19/16/03 ዓ.ም በተደረገው ቆጠራ በማስረጃ ተረጋግጦ እያለ ከ11ኛ ተከሣሽ ጋር በስውር በመመሣጠር የተፈፀመው ሕገወጥ ድርጊት ምርመራው እንዳይጀመርና ተከሳሹ ለሕግ እንዳይቀርብ በማድረጉ፣ - 2ኛ ተከሣሽ በበኩሉ ከላይ በተ.ቁ. 1 በተጠቀሰው ጊዜና አኳሃን የ11ኛ ተከሣሽ ሆቴል ከቀረጥ ነፃ ያስገባቸውን ዕቃዎች ለተፈለገው ዓላማ አለማዋሉን በተካሄደው ቆጠራ ተረጋግጦና ሌሎች ተመሣሣይ ድርጊት የፈፀሙ ሆቴሎች ምርመራ እንዲጣራባቸው ሲያደርግ ከ11ኛ ተከሳሽ ጋር በስውር በመመሳጠር ከላይ በተጠቀሰው ሆቴል ላይ ምርመራው እንዳይጀመርና ለሕግ እንዳይቀርብ በማድረጉ፣ - 3ኛ ተከሣሽ በበኩሉ ከላይ በተጠቀሰው ጊዜና አኳኃን የ11ኛ ተከሣሽ ሆቴል ከቀረጥ ነፃ ያስገባቸውን ዕቃዎች ለተፈለገው ዓላማ ማዋል አለማዋሉን ለማረጋገጥ ቡድን አቋቁሞ ወደ ሆቴሉ በመላክ በተደረገው ቆጠራ ብር 9‚981‚651.83 (ዘጠኝ ሚሊዮን ዘጠኝ መቶ ሰማንያ አንድ ሺህ ስድስት መቶ ሃምሳ አንድ ብር ከ83/100) ከቀረጥ ነፃ ያስገባቸውን ዕቃዎች ለተፈለገው ዓላማ አለማዋሉን በቡድኑ ተረጋግጦ እያለ ተከሣሹ አቤቱታ እንዲያቀርብና ድጋሚ ቆጠራ እንዲደረግ ከማድረጉም በላይ በድጋሚ ቆጠራውም ብር 8‚716‚012.84 (ስምንት ሚሊዮን ሰባት መቶ አስራ ስድስት ሺህ አስራ ሁለት ብር ከ84 ሳንቲም) እንዲከፍል በመወሰን ድርጅቱ ምርመራ እንዳይጣራበትና በወንጀል እንዳይከሰስ ሁኔታዎችን በማመቻቸቱ፣ - 11ኛ ተከሳሽ በበኩሉ ከላይ በተጠቀሰው ጊዜና አኳኃን ለድርጅቱ መገልገያ የሚሆኑ የሆቴል ዕቃዎች ከቀረጥ ነፃ እንዲያስገባ ተፈቅዶለት አስገብቶ ለተፈቀደለት ዓላማ ማዋል ሲገባው ከተፈቀደለት ዓላማ ውጭ መጠቀሙን በገ/ጉ/ባለሥልጣን ባለሙያዎች ተረጋግጦ እያለ በፈፀመው ድርጊት በወንጀል መጠየቅ ሲገባው ከ1ኛ-3ኛ ከተጠቀሱት ተከሣሾች ጋር በጥቅም በመመሣጠር ከ1ኛ እስከ 3ኛ የተጠቀሱት ተከሳሾችን ሽፋን አግኝቶ በወንጀል እንዳይጠየቅ በማድረግ ሕገወጥ ተጠቃሚ በመሆኑ፣ በአጠቃላይ ሁሉም ተከሳሾች በሙሉ ፈቃደቸውና ዕውቀታቸው የወንጀሉ ሙሉ ተከፋይ በመሆን በተሰጣቸው የመንግሥት ኃለፊነት ሊጠብቁትና ሊከላከሉት የሚገባውን የመንግስትና የሕዝብ ጥቅም በሚጎዳ አኳኃን በዋና ወንጀል አድራጊነት በፈፀሙት የመንግስት ስራን በማያመች አኳሃን መምራት የሙስና ወንጀል ተከሰዋል። 3ኛ ክስ በ1ኛ፣ 2ኛ፣ እና 12ኛ ተከሳሾች ላይ ብቻ ወንጀሉ በ1996 ዓ.ም የወጣውን የኢ.ፌ.ዴ.ሪ. የወንጀል ሕግ አንቀፅ 32(1) (ሀ)፣ 33፣ 411(1) (ሐ) እና 2 ላይ የተመለከተውን በመተላለፋቸው፣ የወንጀሉ ዝርዝር 1ኛ እና 2ኛ ተከሣሾች እንደ ቅደም ተከተላቸው በኢትዮጵያ ገቢዎችና ጉምሩክ ባለሥልጣን ዋና ዳይሬክተር እና ምክትል ዋና ዳይሬክተርና የሕግ ማስከበር ዘርፍ ኃላፊ ሲሆኑ፤ ስልጣንና ኃላፊነታቸውን በመጠቀም የማይገባ ጥቅም ለራሳቸው ለማግኘት ለሌሎች ሰዎችም ለማስገኘት በማሰብ፣ 12ኛ ተከሳሽም በመንግስት ሰራተኞች ብቻ በሚፈፀም የሙስና ወንጀል ልዩ ተካፋይ በመሆን፣ - 1ኛ እና 2ኛ ተከሳሾች 12ኛ ተከሳሽ ጥቅምት 20 ቀን 2003 ዓ.ም በቦሌ አውሮፕላን ማረፊያ በኩል ከስዊድን ሀገር ወደ ኢትዮጵያ ምንም ዓይነት የጉምሩክ ሥነ ሥርዓት ያልተፈፀመባቸውንና ገደብና ቁጥጥር የሚደረግባቸውን 32 ዓየነት የተለያዩ ብዛት ያላቸው የሕክምና መገልገያ መሣሪያዎችን በአራት ሻንጣ ሲያስገባ ተይዞ 5% ቀረጥና ታክስ ከፍሎ ወደ መጣበት ሀገር እንዲመልስ ተወስኖ ሕዳር 1 ቀን 2003 ዓ.ም ታግ ተለጥፎበት ቤልት ላይ ከገባ በኋላ ከሀገር እንዲወጣ የተባለውን ዕቃ ከቦሌ አውሮፕላን ማረፊያ ደብቆ መልሶ ወደ ሀገር ውስጥ ሊያስገባ ሲል ተይዞ በጉምሩክ አዋጅ ቁጥር 622/2001 አንቀጽ 9/1/ የተመለከተውን በመተላለፍ በፈፀመው የኮንትሮባንድ ወንጀል በፌዴራል መጀመሪያ ደረጃ ፍ/ቤት ተከሶ ፍ/ቤቱ የግራ ቀኙን ማስረጃ ሰምቶ ካጠናቀቀ በኋላ ለፍርድ ተቀጥሮ ባለበት ሁኔታ ከተከሳሹ ጋር በፈጠሩት ሕግ ወጥ የጥቅም ግንኙነት እንዳይቀጣ በማሰብ ለፍርድ የተቀጠረውን ክስ ያለ ሕጋዊ ምክንያት እንዲነሳ በማድረጋቸው፣ - 12ኛ ተከሣሽም በፈፀመው ወንጀል ተከሶ የነበረ ቢሆንም ከ1ኛ እና የ2ኛ ተከሳሾች ጋር በፈጠረው የጥቅም ግንኙነት የተከሳሾችን ሽፋን አግኝቶ ክሱን በማስነሳት ሕገወጥ ተጠቃሚ በመሆኑ፣ በአጠቃላይ ሁሉም ተከሣሾች በሙሉ ፈቃዳቸውና ዕውቀታቸው የወንጀሉ ሙሉ ተካፋይ በመሆን በተሰጣቸው የመንግሥት ኃላፊነት ሊጠብቁትና ሊከላከሉት የሚገባውን የመንግስትና የህዝብ ጥቅም በሚጎዳ አኳኃን በዋና ወንጀል አድራጊነት በፈፀሙት የመንግስት ስራን በማያመች አኳኃን መምራት የሙስና ወንጀል ተከሰዋል። 4ኛ ክስ በ1ኛ፣ 2ኛ፣ 8ኛ፣ 9ኛ፣ 16ኛ፣ 17ኛ እና 24ኛ ተከሳሾች ላይ ብቻ ወንጀሉ በ1996 ዓ.ም የወጣውን የኢ.ፌ.ዴ.ሪ. የወንጀል ሕግ አንቀፅ 32(1) (ሀ)፣ 33፣ 411(1) (ሐ) እና 2 ላይ የተመለከተውን በመተላለፋቸው፣ የወንጀሉ ዝርዝር 1ኛ፣ 2ኛ፣ 8ኛ እና 24ኛ ተከሣሾች እንደ ቅደም ተከተላቸው በኢትዮጵያ ገቢዎችና ጉምሩክ ባለሥልጣን ዋና ዳይሬክተር፣ ምክትል ዋና ዳይሬክተርና የሕግ ማስከበር ዘርፍ ኃላፊ፤ የጉምሩክ ሥነ ሥርዓት አፈፃፀም የሥራ ሂደት መሪ እና 24ኛ ተከሳሽ ደግሞ የብሔራዊ መረጃና ደህንነት አገልግሎት አማካሪ ሲሆኑ፣ ስልጣንና ኃለፊነታቸውን በመጠቀም የማይገባ ጥቅም ለራሳቸው ለማግኘት ለሌሎች ሰዎችም ለማስገኘት በማሰብ፣ 9ኛ፣ 16ኛ እና 17ኛ ተከሳሾችም በመንግስት ሰራተኞች ብቻ በሚፈፀም የሙስና ወንጀል ልዩ ተካፋይ በመሆን፣ ከ1999 ዓ.ም እስከ 2000 ዓ.ም ባሉት ጊዜያት በሀገሪቱ ተከስቶ የነበረውን የሲሚንቶ እጥረትና ዋጋውን ለማረጋጋት ከውጪ አገር ያለ ውጪ ምንዛሪ ክፍያ ከቀረጥ ነፃ ወደ ሀገር ውስጥ በማስገባት ለሀገራዊ የቤቶች ልማት ፕሮጀክቶች ግንባታ ላይ ለማዋል ታሰቦ የገባው ሲሚንቶ ከታለመለት ዓላማ ውጪ ለ3ኛ ወገን በመተላለፉ ቀኑና ወሩ ለጊዜው ባልታወቀበት 2002 ዓ.ም ለ2ኛ ተከሳሽ እና እሱ ለሚመራው የሕግ ማስከበር ዘርፍ ጥቆማ ተደርጎ የብር 21‚602‚608.64 /ሃያ አንድ ሚሊዮን ስድስት መቶ ሁለት ሺህ ስድስት መቶ ስምንት ብር ከ64/100/ ቀረጥና ታክስ ባለመከፈሉ በመንግስት ላይ ጉዳት መድረሱ በመረጋገጡ ውሉን የተዋዋለው አቅራቢው ድርጅት፣ ትራንዚተሮች፣ ሲሚንቶውን በትራንስፖርት አስገብተው ለ3ኛ ወገን አሳልፈው የሰጡ አጓጓዥ ድርጅቶች እና ስራ አስኪያጆቻቸው ወይም ባለንብረቶቻቸው እንዲሁም ቁጥጥርና ክትትል ያላደረጉት የጉምሩክ ሰራተኞች ጭምር ተጠያቂ መሆናቸው በኣዲት ተረጋግጦ ቀርቦ እያለ ይህንኑ መነሻ በማድረግ ምርመራ በማጣራት አጥፊዎችን ለሕግ እንዲቀርቡ ማድረግ ሲገባቸው ከዚህ በተቃራኒው በመስራት ሕገወጥ ተጠቃሚ ለመሆን በማሰብ፣ - 1ኛ ተከሳሽ የመ/ቤቱ የበላይ ኃላፊ እንደመሆኑ የመ/ቤቱ ሰራተኛ የሆነው 8ኛ ተከሳሽ በደንብ ቁጥር 155/2000 መሰረት በፈፀመው ድርጊት በወንጀል እና በዲሲፒሊን እንዲጠየቅ ማስደረግ ሲገባው በፈፀመው ድርጊት እንዳይጠየቅ ከማድረጉም በተጨማሪ በዐቃቤ ሕግ በኩል ክሱ ሲቀርብበትም ተከሳሹን ለሕግ ማቅረብ ሲገባው ስራውን እንዲለቅ ማመልከቻ እንዱያቀርብ ሁኔታዎችን በማመቻቸቱና ሊጠየቁ በሚገባቸውም ሲሚንቶውን ባስገቡትና ባጓጓዙት በሁሉም የትራንስፖርት ድርጅቶች ላይ ክስ እንዲቀርብ ባለማስደረጉ፤ - 2ኛው ተከሳሽ በበላይነት በሚመራው የስራ ዘርፍ ምርመራው ሲጣራና ክሱ ሲቀርብ የባለስልጣኑ መ/ቤት ሰራተኛ የሆነው 8ኛ ተከሳሽ ቃሉን እንዳይሰጥ በማስደረግ፣ ደመወዝ እየተከፈለው ስራ ላይ ያለ ሰራተኛ መሆኑን እያወቀ ያለአግባብ በጋዜጣ ሲጠራም በዝምታ በማለፍ በመጨረሻም ከ1ኛው ተከሳሽ ጋር ተመካክሮ ተከሳሹ ስራውን እንዲለቅ በማስደረጉ እንዲሁም ሊከሰሱ ከሚገባቸው የትራንስፖርት ድርጅቶችና ባለንብረቶች ጋር ባለው ስውር የጥቅም ግንኙነት ምክንያት የራሱና የሌሎችን ጥቅም በሕገወጥ መንገድ ለማራመድ በማሰብ ጉዳዩን እንዲያጣራ ምንም ኃለፊነት ካልተሰጠው የደህንነት መ/ቤት ከፍተኛ አመራር ከሆነው 24ኛ ተከሳሽ ጋር በመሆን ጉዳዩን የሚያውቁ ሰዎችን እያስቀረበ ከመረመረ በኋላ ወንጀል የተፈፀመበት ሲሚንቶ የሌላ ሰው ነው ብላችሁ መስክሩ በማለት የጉዳዩን አቅጣጫ እሱ በሚፈልገው መንገድ እንዲሄድ ከመገፋፋቱም በላይ ኤ ኤንድ ጂ ድርጅት፣ ኃይሌ አሰፋ እና ሸሚዛል በተባሉት 3 ድርጅቶች ላይ ብቻ ምርመራው ተጣርቶ ክሱ እንዲቀርብ ሲያስደርግ ከእሱ ከ24ኛ ተከሳሽ ጋር የጥቅም ግንኙነት ባላቸው 1ኛ. ነፃ ትራንስፖርት ድርጅት እና የድርጅቱ ባለቤት የሆነው 9ኛ ተከሳሽ፣ 2ኛ. ጌታስ የተባለው ድርጅት እና የድርጅቱ ባለቤት የሆነው 16ኛ ተከሳሽ እና 3ኛ. ኮሜት ትራንስፖርት ድርጅት እና የድርጅቱ ባለቤት የሆነው 17ኛ ተከሳሽ ላይ ተነጥሎ ምርመራ እንዳየጣራባቸው በማስደረጉ፤- 24ኛ ተከሳሽም በብሔራዊ መረጃና ደህንነት አገልግሎት መ/ቤት ውስጥ ከፍተኛ መዋቅር ላይ ተመድቦ ሲሰራ ይህን ስልጣንና ኃላፊነቱን አለአግባብ መከታ በማድረግ ከቀረጥ ነፃ የገበያ ሲሚንቶ ማጭበርበር ጋር በተያያዘ ለገቢዎችና ጉምረክ ባለስልጣን የቀረበውን ጥቆማና ምርመራ እንዲከታተል ከመ/ቤቱ ባልተወከለበት ሁኔታ የራሱና የሌሎችን ጥቅም በሕገወጥ መንገድ ለማራመድ በማሰብ በተለያዩ ቅናት 2ኛ ተከሣሽቢሮ ድረስ በመሄድ ጉዳዩን የሚያውቁ ሰዎችን እያስቀረበ ከመረመረ በኋላ ወንጀል የተፈፀመበት ሲሚንቶ የሌላ ሰው ነው ብላችሁ መስክሩ በማለት የጉዳዩን አቅጣጫ እሱ በሚፈልገው መንገድ እንዲሄድ ሙከራ ከማድረጉም በላይ ኤ ኤንድ ጂ ድርጅት፣ ኃይሌ አሰፋ እና ሸሚዛል በተባሉት 3 ድርጅቶች ላይ ብቻ ምርመራው ተጣርቶ ክሱ እንዲቀርብ ሲያስደርግ ከእሱና ከ2ኛ ተከሳሽ ጋር የጥቅም ግንኙነት ባላቸው 1ኛ. ነፃ ትራንስፖርት ድርጅት እና የድርጅቱ ባለቤት የሆነው 9ኛ ተከሳሽ፣ 2ኛ. ጌታስ የተባለው ድርጅት እና የድርጅቱ ባለቤት የሆነው 1ኛ ተከሳሽ እና 3ኛ. ኮሜት ትራንስፖርት ድርጅት እና የድርጅቱ ባለቤት የሆነው 17ኛ ተከሳሽ ላይ ተነጥሎ ምርመራ እንዳይጣራባቸው በማስደረጉ፤ - 8ኛ ተከሳሽ በዚህ ጉዳይ ተከሶ ፍ/ቤት እንዲቀርብ የታዘዘ ቢሆንም ከ1ኛ እና 2ኛ ተከሳሾች ጋር ባለው የጥቅም ትስስር እና የነሱን ሽፋን ተጠቅሞ ፍ/ቤት ቀርቦ እንዳይጠየቅ በማስደረጉ፣ - 9ኛ፣ 16ኛ እና 17ኛ ተከሳሾችም ከቀረጥ ነፃ የገባ ሲሚንቶ አጓጉዘው ከታለመለት ዓላማ ውጪ ለ3ኛ ወገን ለመሸጣቸው ተረጋግጦ እያለ ከ2ኛ ተከሳሽ ጋር ባላቸው የጥቅም ትስስር ምክንያት በምርመራው እንደይካተቱ የ2ኛ ተከሳሽን ሽፋን አግኝተው በሕግ እንዳይጠየቁ በማስደረጋቸው፣ ሁሉም ተከሳሾች ሊጠብቁትና ሊከላከሉት የሚገባውን የመንግስትና የህዝብ ጥቅም በሚጎዳ አኳሃን በዋና ወንጀል አድራጊነት ተካፋይ በመሆን በፈፀሙት የመንግስት ስራን በማያመች አኳሃን መምራት የሙስና ወንጀል ተከሰዋል። 5ኛ ክስ በ1ኛ፣ እና 2ኛ ተከሳሾች ላይ ብቻ ወንጀሉ በ1996 ዓ.ም የወጣውን የኢ.ፌ.ዴ.ሪ. የወንጀል ሕግ አንቀፅ 32(1) (ሀ)፣ 33፣ 411(1) (ሐ) እና 2 ላይ የተመለከተውን በመተላለፋቸው፣ የወንጀሉ ዝርዝር ተከሣሾች እንደ ቅደም ተከተላቸው በኢትዮጵያ ገቢዎችና ጉምሩክ ባለሥልጣን ዋና ዳይሬክተር እና ምክትል ዋና ዳይሬክተርና የሕግ ማስከበር ዘርፍ ኃላፊ ሲሆኑ፤ ስልጣንና ኃላፊነታቸውን በመጠቀም የማይገባ ጥቅም ለራሳቸው ለማግኘት ለሌሎች ሰዎችም ለማስገኘት በማሰብ፣ - 1ኛ እና 2ኛ ተከሳሾች ኢኖቫ ፓኬጂንግ ኃ/የተ/የግ/ማኅበር እ.ኤ.አ በ2009 ለመንግስት መከፈል የነበረበትን ገቢ ግብር ብር 2‚088‚328.72 (ሁለት ሚሊየን ሰማንያ ስምንት ሺህ ሦስት መቶ ሃያ ስምንት ብር ከሰባ ሁለት ሳንቲም) ግብርን አሳውቆ ባለመክፈሉ እና ዓመታዊ ትርፉ 11‚448‚939.30 (አሥራ አንድ ሚሊዮን አራት መቶ አርባ ስምንት ሺህ ዘጠኝ መቶ ሠላሳ ዘጠኝ ብር ከሰላሳ ሳንቲም) ሆኖ እያለ በበጀት ዓመቱ ያሳወቀው ግብር ብር 9‚569‚671.05 (ዘጠኝ ሚሊዮን አምስት መቶ ስልሣ ዘጠኝ ሺህ ስድስት መቶ ሰባ አንድ ብር ከዜሮ አምስት ሣንቲም) ነው ብሎ አሳሳች ማስረጃ በማቅረቡ በገቢ ግብር አዋጅ ቁጥር 286/94 አንቀጽ 96፣ 102፣ 97/1/ እና 3(ለ) የተመለከተውን ተላልፎ ሕግን በመጣስ ግብር አለመክፈልና አሳሳች መረጃ ማቅረብ ተደራራቢ ወንጀል ፈፅሟል ተብሎ በድርጅቱና በድርጅቱ ስራ አስኪያጅ ላይ በፌ/የመ/ደ/ፍ/ቤት ክስ ተመስርቶ እያለ ድርጅቱና የድርጅቱ ስራ አስኪያጅን ከወንጀል ተጠያቂነት ለማዳን በማሰብ 2ኛ ተከሳሽ ክሱ እንዲነሳ ለ1ኛ ተከሳሽ በ7/2/2005 ዓ.ም በተፃፈ ደብዳቤ የውሳኔ ሀሳብ አቅርቦ 1ኛ ተከሳሽ አፅድቆ ያለምንም ሕጋዊ ምክንያት ክሱን እንዲነሳ በማድረጋቸው፣ ሁለቱም ተከሣሶች በሙሉ ፈቃደቸውና ዕውቀታቸው የወንጀሉ ሙሉ ተካፋይ በመሆን በተሰጣቸው የመንግሥት ኃላፊነት ሊጠብቁትና ሊከላከሉት የሚገባውን የመንግሰትና የሕዝብ ጥቅም በሚጎዳ አኳሃን በዋና ወንጀል አድራጊነት በፈፀሙት የመንግስት ስራን በማያመች አኳሃን መምራት የሙስና ወንጀል ተከሰዋል። 6ኛ ክስ በ2ኛ ተከሳሾች ላይ ብቻ ወንጀሉ በ1996 ዓ.ም የወጣውን የኢ.ፌ.ዴ.ሪ. የወንጀል ሕግ አንቀፅ 32(1) (ሀ)፣ 33፣ 411(1) (ሐ) እና 2 ላይ የተመለከተውን በመተላለፋቸው፣ የወንጀሉ ዝርዝር ተከሳሹ በኢትዮጵያ ገቢዎችና ጉምሩክ ባለሥልጣን ምክትል ዋና ዳይሬክተርና የሕግ ማስከበር ዘርፍ ኃላፊ ሲሆን፤ ስልጣንና ኃለፊነቱን በመጠቀም የማይገባ ጥቅም ለራሱ ለማግኘት ለሌሎች ሰዎችም ለማስገኘት በማሰብ፣ - 2ኛ ተከሣሽ በ26/07/2001 ዓ.ም ጐላጐል ትሬዲንግ ኃ/የተ/የግ/ማኅበር የተባለ ድርጅት ያለቫት ደረሰኝ ግብይት እንደሚፈፅም ለገቢዎችና ጉምሩክ ባለስልጣን ጥቆማ ቀርቦ እውነተኛነቱን ለማረጋገጥ የባለሥልጣኑ ሠራተኞች ተልከው እንደጥቆማው አቀራረብ እንደሚፈፅም በወቅቱ በተላኩት ሠራተኞች ከተረጋገጠና ተጠርጣሪዎችም ከተለዩና ምርመራ መዝገቡ ተደራጅቶ እንደሚያስከስስ ከተረጋገጠ በኋላ ተከሣሹ የባለሥልጣኑ የሥራ ኃላፊዎች በተገኙበት የድርጅቱ ባለቤት አቤቱታ ስላቀረበ ጉዳዩ በድጋሚ መታየት አለበት በሚል ሽፋን ምርመራው እንደገና እንዲጣራ በማድረግ ቀደም ሲል በጉዳዩ ዙርያ ከተሰጠው የምስክርነት ቃል በተለየ ጉዳዩን ሊያዳክም የሚችል አዲስ ተጨማሪ ቃል እንዲቀርብ በማድረግ መዝገቡ ውጤት እንዳይኖረው ካመቻቸ በኋላ ምርመራ መዝገቡ እንዲዘጋ በማስደረጉ፣ በዋና ወንጀል አድራጊነት ተካፋይ በመሆን በፈፀመው የመንግስት ሥራን በማያመች አኳሃን መምራት የሙስና ወንጀል ተከሷል። 7ኛ ክስ በ2ኛ፣ እና 7ኛ ተከሳሾች ላይ ብቻ ወንጀሉ በ1996 ዓ.ም የወጣውን የኢ.ፌ.ዴ.ሪ. የወንጀል ሕግ አንቀፅ 32(1) (ሀ)፣ 33፣ 411(1) (ሐ) እና 2 ላይ የተመለከተውን በመተላለፋቸው፣ የወንጀሉ ዝርዝር ተከሣሾች እንደ ቅደም ተከተላቸው በኢትዮጵያ ገቢዎችና ጉምሩክ ባለሥልጣን ምክትል ዋና ዳይሬክተርና የሕግ ማስከበር ዘርፍ ኃላፊ እና የአዳማ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ሥራ አስኪያጅ ሲሆኑ፤ ስልጣንና ኃለፊነታቸውን በመጠቀም የማይገባ ጥቅም ለራሳቸው ለማግኘት ለሌሎች ሰዎችም ለማስገኘት በማሰብ፤ - ገላን ታነሪ ኃ/የተ/የግ ማኅበር የተባለው ድርጅት በዲክላራሲዮን ቁጥር E-3248/1 ወደ ውጭ ለመላክ ዲክሌር ያደረገው የቆዳ ብዛት 33‚600.00 (ሰላሳ ሦስት ሺህ ስድስት መቶ) ሆኖ በአዳማ ገቢዎችና ጉምሩክ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት በ11/03/04 ፍተሻ በሚደረግበት ጊዜ ብዛቱ 42‚360 (አርባ ሁለት ሺህ ሦስት መቶ ስልሳ) ሆኖ በመገኘቱ ምክንያት በልዩነት ለተገኘውና ግምቱ ብር 423‚189.94 (አራት መቶ ሃያ ሦስት ሺህ አንድ መቶ ሰማንያ ዘጠኝ ከ94/100) ለሆነው 8‚760 (ስምንት ሺህ ሰባት መቶ ስልሳ) ቀዳ በድርጅቱ እና በድርጅቱ ሥራ አስኪያጅ አቶ አህመድ ኑር ሐሰን ላይ የወንጀል ምርመራ ተጣርቶ የቅርንጫፍ ጽ/ቤቱ ዐቃቤ ሕግ በቁጥር 8-54593/04 በ26/08/2004 የተዘጋጀ ክስ አቅርቦባቸው እያለ፤ 7ኛ ተከሳሽ በቅርንጫፍ ጽ/ቤቱ በነበረው ኃላፊነት ባለሀብቱ ወደ ውጪ ለመላክ ባቀረበው ቆዳ ላይ ፍተሻ በሚደረግበት ወቅት ቆዳ በትርፍነት የተገኘበትና ምርመራም የተጣራበት መሆኑን እያወቀ ባለሀብቱንና ድርጅቱን ከተጠያቂነት ለማዳን አስቀድሞ በቁ.8.0/0/1048 በ12/06/04 ለድርጅቱ በፃፈው ደብዳቤ ጉዳዩን ለዐቃቤ ሕግ እንደማይልክ ከመግለፁም በተጨማሪ በባለሀብቱ ላይ የቀረበው ክስ እንዲነሳ የሚጠይቅ የውሳኔ ሀሳብ በ15/09/04 በተፃፈ ቃለ ጉባኤ ለ2ኛ ተከሳሽ በማቅረቡ፣ 2ኛ ተከሳሽ በበኩሉ ባለሀብቱ የማታለል ድርጊት በመፈፀም ቆዳ በትርፍነት ለመላክ ሲሞክር መያዙን እያወቀ በባለሀብቱ ላይ የተመሰረተው ክስ የሚነሳበት ሕጋዊ ምክንያት በሌለበት ሁኔታ ከባለሀብቱ ጋር በጥቅም በመመሳጠር በባለሀብቱ ላይ የቀረበው ክስ እንዲቋረጥ በ24/09/04 ትዕዛዝ በመስጠት ክሱ እንዲነሳ በማድረጉ፣ ሁለቱም ተከሳሾች ባለሀብቱ በሕግ እንዳይጠየቅና በትርፍነት የተገኘው ቆዳ ላይም እርምጃ እንዳይወሰድ በማድረጋቸው፣ በተሰጣቸው የመንግሠት ኃላፊነት ሊጠብቁትና ሊከላከሉት የሚገባውን የመንግስትና የሕዝብ ጥቅም በሚጎዳ አኳሃን በዋና ወንጀል አድራጊነት በፈፀሙት የመንግስት ስራን በማያመች አኳሃን መምራት የሙስና ወንጀል ተከሰዋል። 8ኛ ክስ በ2ኛ ተከሳሾች ላይ ብቻ ወንጀሉ በ1996 ዓ.ም የወጣውን የኢ.ፌ.ዴ.ሪ. የወንጀል ሕግ አንቀፅ 32(1) (ሀ)፣ 33፣ 411(1) (ሐ) እና 2 ላይ የተመለከተውን በመተላለፋቸው፣ የወንጀሉ ዝርዝር ተከሳሹ በኢትዮጵያ ገቢዎችና ጉምሩክ ባለሥልጣን ምክትል ዋና ዳይሬክተርና የሕግ ማስከበር ዘርፍ ኃላፊ ሲሆን፤ ስልጣንና ኃላፊነቱን በመጠቀም የማይገባ ጥቅም ለራሱ ለማግኘት ለሌሎች ሰዎችም ለማስገኘት በማሰብ፣ - 2ኛ ተከሣሽ አቢ ብርሃኑ የተባለ ግለሰብ ተገቢው ቀረጥና ታክስ ያልተከፈለባቸውን የሰሌዳ ቁ.ኮድ 3-48863 አ.አ. እና ተላላፊ ሰሌዳ ቁ.545 አ.አ. የሆኑ ሁለት ተሽከርካሪዎች ይዞ በ30/01/2001 ዓ.ም በመገኘቱ ምክንያት ከሌላ ግብረአበሩ ጋር ምርመራ ተጣርቶበት መዝገቡ ለሚመለከተው ዐቃቤ ሕግ ከተላለፈ በኋላ ተከሳሹ ሥልጣኑን በመጠቀም በመዝገቡ ውስጥ 1ኛ ተጠርጣሪ ከሆነው አቢ ብርሃኑ ከተባለው ተጠርጣሪ አባት አቶ ብርሃኑ ብሩ ጋር ባለው የጥቅም ትስስር ጉዳዩ ወደ ፍ/ቤት እንዳይሄድና መኪናውም እንዲለቀቅ ለማድረግ ከተያዙት ሁለት መኪኖች ውስጥ ኮድ 3-48863 አ.አ የሆነው መኪና በአዋጅ ቁ. 60/89 አንቀፅ 74 መሠረት መወረስ እየተገባው ቀረጥና ታክሱ ተከፍሎ እንዲለቀቅ በማድረግ በዚህም መነሻነት የወንጀል መዝገቡ እንዲዘጋ በማድረጉና ለዚህም ውለታው በአሁኑ አጠራር ለገጣፎ ለገዳዲ በቀድሞ ስሙ ወልገወ ቀበሌ ገበሬ ማኅበር ሊቀመንበር በነበረው አቶ ብርሃኑ ብሩ አማካኝነት በአሁኑ ሰዓት ሊገኝ ያልቻለ ሕገ ወጥ የቀበሌ ነዋሪነት መታወቂያ በመስጠትና በዚህም መታወቂያ መነሻነት በለገጣፎ ለገዳዲ ከተማ 500 ካ.ሜ ቦታ በሕገወጥ መንገድ በመውሰዱ፣ በዋና ወንጀል አድራጊነት በፈፀመው የመንግስት ሥራን በማያመች አኳሃን መምራት የሙስና ወንጀል ተከሷል። 9ኛ ክስ በ2ኛ፣ 4ኛ፣ 5ኛ እና 6ኛ ተከሳሾች ላይ ብቻ ወንጀሉ በ1996 ዓ.ም የወጣውን የኢ.ፌ.ዴ.ሪ. የወንጀል ሕግ አንቀፅ 32(1) (ሀ)፣ 33፣ 411(1) (ሐ) እና 2 ላይ የተመለከተውን በመተላለፋቸው፣ የወንጀሉ ዝርዝር ተከሣሶች እንደ ቅደም ተከተላቸው በኢትዮጵያ ገቢዎችና ጉምሩክ ባለሥልጣን ምክትል ዋና ዳይሬክተርና የሕግ ማስከበር ዘርፍ ኃላፊ፣ ምክትል ዋና ዐቃቤ ሕግ፣ በዐቃቤ ቃሊቲ ቅ/ፅ/ቤት የሕግ ማስከበር ኃላፊ እና የድሬ ዳዋ ቅ/ፅ/ቤት የጣቢያ አስተባባሪ ሲሆኑ፤ ስልጣንና ኃለፊነታቸውን በመጠቀም የማይገባ ጥቅም ለራሳቸው ለማግኘት ለሌሎች ሰዎችም ለማስገኘት በማሰብ፣ 6ኛ ተከሳሽ በ8/8/2002 ዓ.ም በባለሥልጣኑ አዋሽ መቅረጫ ጣቢያ ማንነቷ ለጊዜው ካልታወቀች ግለሰብ ላይ በፍተሻ ከተያዙ ኮንትሮባንድ ካሜራዎች ውስጥ ሦሰት ሶኒ ጂጅታል ካሜራዎችን ወስዶ ለግል ጥቅሙ ማዋሉ ታውቆ ምርመራ መጣራት ሲጀመርበት፡- - 5ኛ ተከሣሽ የባለስልጣኑ ቅርንጫፍ ጽ/ቤቱ ዐቃቤ ሕግ የሆኑትን አቶ ምንይችል ተኮላ ጋር ስልክ ደውሎ “6ኛ ተከሳሽ ለምን ታሰረ? እንዲፈታ!” ብሎ በቃል ትዕዛዝ ከማስተላለፉም በላይ በአካል ከሥፍራው ድረስ በመሄድ ምርመራው እንዳይጣራ ለፍ/ቤት በቃል አመልክቶ እንዲፈታ በማስደረጉ፣ - 4ኛ ተከሣሽ ምርመራ እንዲጣራ ትዕዛዝ ሰጥተው ለነበሩት ዐቃቤ ሕግ አቶ አምደሚካኤል ጌታቸው የስልክ ትዕዛዝ በመስጠት በ6ኛ ተከሣሽ ላይ ምርመራ እንዳይጀመር በማድረጉ፣- 2ኛ ተከሳሽ 6ኛ ተከሣሽ በተጠረጠረበት ብልሹ አሰራርና የሙስና ወንጀል በባለሥልጣኑ ደንብ ቁጥር 155/2000 አንቀጽ 37/1/ መሠረት የዲሲፒሊን እርምጃ እንድወሰድና ለሕግም እንዲቀርብ ማስደረግ ሲገባው በስራው ላይ እንዲቆይና በሕግም እንዳይጠየቅ በማድረጉ፤ - 6ኛ ተከሳሽ በዚህ ጉዳይ ታስሮ ምርመራው የተጀመረበት ቢሆንም ከ2ኛ፣ 4ኛ እና 5ኛ ተከሳሾች ጋር ባለው የጥቅም ትስስር ምክንያት የነሱን ሽፋን ተጠቅሞ ምርመራው እንዲቋረጥለት በማስደረግ ሕገወጥ ተጠቃሚ በመሆኑ፣ በአጠቃላይ ሁሉም ተከሣሾች በሙሉ ፈቃዳቸውና ዕውቀታቸው የወንጀሉ ሙሉ ተካፋይ በመሆን በተሰጣቸው የመንግሥት ኃላፊነት ሊጠብቁትና ሊከላከሉት የሚገባውን የመንግስትና የህዝብ ጥቅም በሚጎዳ አኳሃን በዋና ወንጀል አድራጊነት ተካፋይ በመሆን በፈፀሙት የመንግስት ስራን በማያመች አኳሃን መምራት የሙስና ወንጀል ተከሰዋል። 10ኛ ክስ በ6ኛ ተከሳሾች ላይ ብቻ ወንጀሉ በ1996 ዓ.ም የወጣውን የኢ.ፌ.ዴ.ሪ. የወንጀል ሕግ አንቀፅ 413/1/ሀ/ ላይ የተመለከተውን በመተላለፋቸው፣ የወንጀሉ ዝርዝር ተከሣሹ በኢት/ገ/ጉ/ባለሥልጣን የአዋሽ መቅረጫ ጣቢያ አስተባባሪ ሆኖ ሲሰራ የማይገባ ቁሳዊ ጥቅም ለራሱ ለማግኘትና ለሌሎች ሰዎችም ለማስገኘት አስቦ በ8/8/2002 ዓ.ም ስሟ ለጊዜው ያልታወቀች ኮንትሮባንዲስት ከጅጅጋ ወደ አዲስ አበባ በሚጓዝ ተሽከርካሪ ተሳፍራ ስትመጣ በኢትዮጵያ ገቢዎችና ጉምሩክ ባለሥልጣን አዋሽ መቅረጫ ጣቢያ ላይ በተደረገባት ፍተሻ ሦስት ሶኒ ዲጅታል ካሜራ ተይዞባት በደረሰኝ ቁጥር 849781 ተመዝግቦ የነበረውን ደረሰኝ እንዲሰረዝ (void እንዲሆን) በማድረግና በማስደረግ ወስዶ ለግል ጥቅሙ በማዋሉ በፈፀመው በሥራ ተግባር ላይ የሚፈፀም የመውሰድና የመሰወር የሙስና ወንጀል ተከሷል። 11ኛ ክስ በ6ኛ ተከሳሾች ላይ ብቻ ወንጀሉ' በ1996 ዓ.ም የወጣውን የኢ.ፌ.ዴ.ሪ. የወንጀል ሕግ አንቀፅ 408(1) ላይ የተመለከተውን በመተላለፋቸው፣ የወንጀሉ ዝርዝር ተከሳሹ በኢትዮጵያ ገቢዎችና ጉምሩክ ባለሥልጣን የድሬዳዋ ቅ/ጽ/ቤት የላጋር መቅረጫ ጣቢያ አስተባባሪ ሆኖ ሲሰራ በኃላፊነቱ እና በሥራ ግዴታው ማድረግ የማይገባውን በማድረግ ሕገወጥ ጥቅም ለማግኘት አስቦ፤ - ቀኑ በውለ ተለይቶ ባልታወቀበት ጥር ወር 2005 ዓ.ም ከምሽቱ 12፡00 ሰዓት በሚሆንበት ጊዜ ድሬዳዋ ከተማ ቀበሌ 03 ፖሊስ መምሪያ አካባቢ ወደ ኮንደሚኒየም በሚወስደው መንገድ ላይ ኤምዲ (MD Transit) የተባለ ድርጅት አስተላላፊ ሥራ አስኪያጅ ከሆኑት አቶ ታደሰ ገ/ዮሐንስ ላይ ከጅቡቲ ተጓጉዞ ድሬዳዋ ጉምሩክ የገባ የመኪና መለዋወጫ ዕቃዎች በሠነድ ከተዘረዘሩት በላይ (ትርፍ) በመገኘቱ ዕቃው በመያዙ ዕቃውን ለመልቀቅ ብር 10‚000 (አሥር ሺ ብር) ተቀብሎ በመውሰዱ፤ - ቀኖቹ በውል ተለይተው ባለታወቁበት በሚያዝያ ወር 2005 ዓ.ም በተለያዩ ሁለት ቀናት ከምሽቱ 12፡00 ሰዓት ሲሆን፤ በድሬዳዋ ከተማ 03 ቀበሌ ማርያም ሰፈር ዲፖ አካባቢ የንግድ ረዳት ሆነው ይሰሩ ከነበሩት አቶ ቴዎድሮስ ጌታቸው ከጅቡቲ ተጓጉዘው ድሬዳዋ ጉምሩክ የገቡ አምፖሎች ተፈትሸው ከተጠናቀቁ በኋላ ተከሳሹ ገንዘብ ካልሰጠኸኝ እቃዎቹ አይወጡም ብሎ በመደራደር ለመጀመሪያዎቹ ብር 15‚000 (አስራ አምስት ሺህ)፣ ለሁለተኛዎቹ ብር 20‚000 (ሃያ ሺህ) በድምሩ ብር 35‚000 (ሰላሳ አምስት ሺህ ብር) ተቀብሎ በመውሰዱ፤ በፈፀመው ጉቦ መቀበል የሙስና ወንጀል ተከሷል። 12ኛ ክስ በ2ኛ፣ 4ኛ እና 9ኛ ተከሳሾች ላይ ብቻ'' ወንጀሉ በ1996 ዓ.ም የወጣውን የኢ.ፌ.ዴ.ሪ. የወንጀል ሕግ አንቀፅ 32(1)(ሀ)(ለ)፣ 33፣ እና 408(1) እና (2) ላይ የተመለከተውን በመተላለፋቸው፣ የወንጀሉ ዝርዝር 2ኛ እና 4ኛ ተከሳሾች እንደቅደም ተከተላቸው በኢትዮጰያ ገቢዎችና ጉምሩክ ባለስልጣን ምክትል ዋና ዳይሬክተርና የሕግ ማስከበር ዘርፍ ኃላፊ እና ምክትል ዋና ዐቃቤ ሕግ ሆነው ሲሰሩ፣ በስራ ኃላፊነታቸው ማድረግ የማይገባቸውን በማድረግ ሕገወጥ ጥቅም ለማግኘት በማሰብ፣ 9ኛ ተከሳሽ በበኩሉ የመንግስት ሰራተኞች ብቻ በሚፈፀም የሙስና ወንጀል ልዩ አካፋይ በመሆን፤ - 2ኛ ተከሣሽ ብሥራት ኃ/የተ/የግ/ማኅበር የተባለ ድርጅት ያለ ቫት ደረሰኝ ግብይት ሲፈፅም ተከሣሹ ለሚሰራበት መ/ቤት ጥቆማ ቀርቦ እንደ ጥቆማው አቀራረብ ለማረጋገጥ የድርጅቱ ሠራተኞች መጋቢት 29 ቀን 2001 ዓ.ም ወደ ድርጅቱ በመሄድ ኦፕሬሽን ሲካሄድ ያለደረሰኝ ግብይት እያከናወነ መሆኑ በመረጋገጡ በድርጅቱ፤ በድርጅቱ ባለቤትና ሌሎች ሁለት የድርጅቱ ሠራተኞች ላይ ምርመራ ተጣርቶ ክስ ቀርቦባቸው በክርክር ላይ እያለ ተከሣሹ ለብሥራት ኃ/የተ/የግ/ማኅበር ባለቤት አቶ ባህሩ አብርሃ በቀጥታ መስመር ስልካቸው ላይ በመደወል “አንተ ከማን ትበልጣለህ ወደ መደበኛ ፍ/ቤት ክስህን አቅርበን ከፍተኛውን ቅጣት አንደምናስቀጣህ እወቅ” በማለት ግለሰቡን በማስፈራራትና በማስጨነቅ በተከሳሹ የቅርብ አገናኝ በነበረው 9ኛ ተከሳሽ አማካኝነት ቀጠሮ በማስያዝ ከላይ የተጠቀሰውን ባለሀብት ቢሮው በተደጋጋሚ እንዲገኝ በማድረግ ከላይ በተጠቀሰው የማስፈራሪያ ቃል በማስፈራራት “ሌሎች ልጆች ከእኔ ጋር ስላሉ በደንብ ተዘጋጅተህ ና” በማለት የራሱን ስልክ ቁጥር በመስጠት የስልክ ግንኙነት በማድረግ ቀኑና ወሩን በትክክል በማይታወቅበት 2004 ዓ.ም መጀመሪያ አካባቢ ዮርዳኖስ ሆቴል አካባቢ ከምሽቱ 1፡45 ሰዓት በመቅጠር ብር 250‚000 (ሁለት መቶ ሃምሳ ሺህ ብር) ከባለሀብቱ ከተቀበለ በኋላ ባሀብቱ አድርጐት የነበረውን ብራስሌት እጁ ላይ ከተመለከተ በኋላ “የእሱ ዓይነት ግዛልኝ” በማለት ግለሰቡ በብር 30‚000 (ሠላሳ ሺህ ብር) የተገዛ ብራስሌት በማግስቱ ኢንተርኮንቴኔታል ሆቴል አካባቢ ድረስ ይዞ በመሄድ ከምሽቱ 1፡30 ሰዓት አካባቢ ተከሳሹ በእራሱ መኪና ውስጥ ሆኖ ተቀብሎ ጉዳዩ እንዲጨርስለት ለ4ኛ ተከሣሽ ነግሮ ጉዳዩ እንዲያልቅ በማድረጉ፤ - 4ኛ ተከሣሽ በበኩሉ ቀኑና ወሩን በውል በማይታወቅበት በ2004 ዓ.ም መጀመሪያ አካባቢ ፒያሣ ግራር ሆቴል እየተባለ ከሚጠራ ሆቴል ውስጥ በግምት ከምሽቱ 1፡00 ሰዓት አካባቢ ከላይ ከተጠቀሰው ድርጅት ባለቤት (አቶ ባህሩ አብርሃ) ብር 50‚000 (ሃምሳ ሺህ ብር)፤ ከላይ በተጠቀሰው ቀኑና ወሩ በውል በማይታወቅበት ጊዜ ባለሀብቱን እቤቱ ድረስ በመጥራት ብር 30‚000 (ሠላሳ ሺህ ብር) እና ብር 20‚000 (ሃያ ሺህ ብር) በአጠቃላይ ብር 100‚000 (መቶ ሺህ ብር) በመቀበሉ እና ከባለሀብቱ ከላይ የተጠቀሰው የገንዘብ መጠን ተቀብሎ በባለሀብቱ ላይ የተመሠረተውን ክስ በፍ/ቤት በነፃ ከተሰናበተ በኋላ ይግባኝ እንይጠየቅ በማድረጉ፤ - 9ኛ ተከሣሽ በበኩሉ ቀኑና ወሩ በማይታወቅ በ2004 ዓ.ም ባህሩ አብርሃ የተባሉ የብሥራት ኃ/የተ/ማኅበር ባለቤት በገቢዎችና ጉምሩክ ባለሥልጣን የተመሰረተባቸውን ክስ እንዲዘጋ ከ2ኛ ተከሣሽ ጋር በማገናኘት ብር 250‚000 (ሁለት መቶ ሃምሳ ሺህ ብር) እና ብር 30‚000 (ሠላሳ ሺህ ብር) የሚያወጣ ብራስሌት 2ኛ ተከሣሽ በሕገ ወጥ መንገድ እንዲያገኝ በማድረጉ፤ በአጠቃላይ ተከሣሾች በመላ ሀሳባቸውና አድራጐታቸው በወንጀሉ ድርጊትና በሚሰጠው ውጤት ሙሉ ተከፋይ በመሆን በዋና ወንጀል አድራጊነት በፈፀሙት ጉቦ መቀበል የሙስና ወንጀል ተከሰዋል። 13ኛ ክስ በ2ኛ፣ እና 13ኛ ተከሳሾች ላይ ብቻ ወንጀሉ በ1996 ዓ.ም የወጣውን የኢ.ፌ.ዴ.ሪ. የወንጀል ሕግ አንቀፅ 32(1)(ሀ)፣ 419(1) (ሀ) እና ለ ላይ የተመለከተውን በመተላለፋቸው፣ የወንጀሉ ዝርዝር 2ኛ ተከሳሽ በተለያዩ የመንግስት መስሪያ ቤቶች ከ1978 ዓ.ም ጀምሮ እጁ እስከተያዘበት 2005 ዓ.ም ተቀጥሮና ተሹሞ ሲሰራ ከብር 247 (ሁለት መቶ አርባ ሰባት) እስከ ብር 5‚700 (አምስት ሺህ ሰባት መቶ) ያልተጣራ ወርሃዊ ደመወዝ ይከፈለው እንደነበረ እና 13ኛ ተከሣሽ ደግሞ በአገር መከላከያ ሚኒስቴር ከ01/11/1989 ዓ.ም እስከ 30/01/2000 ዓ.ም ተቀጥራ ስትሰራ ከብር 790 (ሰባት መቶ ዘጠና ብር) እስከ ብር 2‚145 (ሁለት ሺህ አንድ መቶ አርባ አምስት) ያልተጣራ ወርሃዊ ደመወዝ ይከፈላት የነበረ ሲሆን ተከሳሾቹ ያገኙት ከነበረው ደመወዝና ገቢ ጋር የማይመጣጠን፤ 1ኛ. በወጋገን ባንክ ካዛንቺስ አካባቢ በሂሣብ ቁጥር 302993 ብር 96‚477.79 (ዘጠና ስድስት ሺ አራት መቶ ሰባ ሰባት ከሰባ ዘጠኝ ሣንቲም) በ13ኛ ተከሳሽ ስም 2ኛ. በእናት ባንክ እቴጌ ጣይቱ አብይ ቅርንጫፍ በሂሳብ ቁጥር R/S746 ብር 4‚000 (አራት ሺህ) በ13ኛ ተከሳሽ ስም፤ 3ኛ. በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ፊንፊኔ ቅርንጫፍ በሂሣብ ቁጥር 1000001730766 ብር 1‚427.59 (አንድ ሺ አራት መቶ ሃያ ሰባት ከሃምሳ ዘጠኝ ሳንቲም) በ13ኛ ተከሳሽ ስም፤ 4ኛ. በኢትዮጰያ ልማት ባንክ በሂሣብ ቁጥር 1258hA, 40612HC, 35933HD, 41304HE, 2636HG, ብር 3‚925 (ሦስት ሺህ ዘጠኝ መቶ ሃያ አምስት) በ13ኛ ተከሳሽ ስም፤ 5ኛ. የካ ክ/ከተማ ቀበሌ 11/12 የቤ.ቁ. 634 የካርታ ቁጥር 29870 የቦታው ስፋት 4‚000 ካ.ሜ የሆነ ቦታ ተከሣሽን ጨምሮ 7 ሰዎች በብር 4‚200‚000 (አራት ሚሊዮን ሁለት መቶ ሺህ ብር) የተገዛ ቦታ (የተከሳሽ ድርሻ ብር 600‚000 (ስድስት መቶ ሺህ ብር)፤ 6ኛ. የሠሌዳ ቁጥር 3-02725 ትግ የሆነ አውቶቡስ ተሽከርካሪ (ለጊዜው ግምቱ ያልታወቀ) በ13ኛ ተከሳሽ ስም፤ 7ኛ. የሠሌዳ ቁጥር 3-49614 አ.አ የሆነ የንግድ መኪና (ለጊዜው ግምቱ ያልታወቀ) በ13ኛ ተከሳሽ ስም፤ 8ኛ. የካረታ ቁጥር 2713/22/93 መቀሌ ከተማ ቀበሌ 11 የሚገኝ መኖሪያ ቤት በ13ኛ ተከሳሽ ስም፤ 9ኛ. በ2ኛ ተከሳሽ ስም ዳሸን ባንክ መቀሌ ቅርንጫፍ በሂሳብ ቁጥር 5013022467001 ብር 42244.62፣ 10ኛ. በ2ኛ ተከሳሽ ስም አንበሳ ባንክ የካ ቅርንጫፍ በሂሳብ ቁጥር 00300000799-97 ብር 387.65 11ኛ. በ2ኛ ተከሳሽ ስም ወጋገን ባንክ መስቀል ቅርንጫፍ በሂሳብ ቁጥር 23444/501/03024 ብር 102‚553.50 (አንድ መቶ ሁለት ሺ አምስት መቶ ሃምሳ ሦስት ከ50/100) 12ኛ. በፀረ ብርሃን ገ/ዋህድ ስም (ልጅ) ካሳንቺስ ቅርንጫፈ በሂሳብ ቁጥር 262179 ብር 18‚142.04፣ 13ኛ. በፀረ ብርሃን ገ/ዋህድ ስም (ልጅ) ካሳንቺስ ቅርንጫፍ በሂሳብ ቁጥር 262180 ብር 1‚015.07፣ 14ኛ. በፀረ ብርሃን ገ/ዋህድ ስም (ልጅ) በኢትዮጰያ ንግድ ባንክ ሀዋሳ ቅርንጫፈ በሂሳብ ቁጥር 1000013401587 ብር 1‚753.77፣ 15ኛ. በፀረ ብርሃን ገ/ዋህድ ስም (ልጅ) በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ፊንፊኔ ቅርንጫፍ በሂሳብ ቁጥር 0173007267000 ብር 203424.99 (ሁለት መቶ ሦስት ሺ አራት መቶ ሃያ አራት ከ99/100)፤ 16ኛ. በ2ኛ ተከሳሽ ስም በአንበሳ ባንክ የብር 34‚275.25 (ሰላሳ አራት ሺ ሁለት መቶ ሰባ አምስት ከ25/100) አክስዮን፤ 17ኛ. በሳሙኤል ገ/ዋህድስም (ልጅ) የብር 10‚000 (አሰር ሺ) አክስዮን፤ 18ኛ. ከተከሳሾች መኖሪያ ቤት የተገኘ፡- 18.1. የኢትዮጵያ ብር 200‚000 (ሁለት መቶ ሺ) 18.2. EURO 19435 (አስራ ዘጠኝ ሺ አራት መቶ ሰላሳ አምስት) 18.3. USD 26300(ሃያ ስድስት ሺ ሶስት መቶ) 18.4. POUND 560 (አምስት መቶ ስድሳ) 18.5. TAILAND 210 (ሁለት መቶ አስር) 19ኛ/ በካርታ ቁጥር L/X/L/D/3139100 ግምቱ ብር 596868፣24 የሆነ 500 ካ.ሜ 20ኛ/ 6 የተለያዩ ላፕቶፖች፤ በአጠቃላይ ተከሳሾች የኑሮ ደረጃቸው አሁን ባለበትም ሆነ አስቀድሞ በነበሩት የመንግሥት ሥራ ከሚያገኙት ህጋዊ ገቢ ጋር የማይመጣጠን ብር 1,451,941.609 (አንድ ሚሊዮን አራት መቶ ሃምሳ አንድ ሺ ዘጠኝ መቶ አርባ አንድ ከ60/00)፣ ከላይ ከተራ ቁጥር 18.2 – 18.5 ድረስ የተጠቀሱትን የውጭ አገር ገንዘቦችና እና እንዲሁም የተለያዩ ንብረቶች ይዘው በመገኘታቸው በፈፀሙት ምንጩ ያልታወቀ ንብረትና ገንዘብ ይዞ መገኘት የሙስና ወንጀል ተከሰዋል። 14ኛ ክስ በ2ኛ እና 13ኛ ተከሳሾች ላይ ብቻ ወንጀሉ በ1996 ዓ.ም የወጣውን የኢ.ፌ.ዴ.ሪ የወንጀል ህግ አንቀፅ 32(1)(ሀ)፣ 684(1) እና (2) ላይ የተመለከተውን በመተላለፋቸው፣ የወንጀሉ ዝርዝር ተከሳሾች ከላይ በ13ኛው ክስ በተገለፀው ጊዜና አኳኋን በፈፀሙት የሙስና ወንጀል ያገኙትን ገንዘብና ንብረት ህገወጥ አመጣጡን በመሰወር ህጋዊ ለማድረግ በማሰብ መሬት እና መኪና በመግዛት፣ በተለያዩ ባንኮች በእራሳቸውና በልጆቻቸው ስም እንዲሁም መኖሪያ ቤታቸው ውስጥ ገንዘቦችን በማስቀመጥ በፈፀሙት በወንጀል ድርጊት የተገኘን ገንዘብና ንብረት ህጋዊ አስመስሎ ማቅረብና በወንጀሉ መርዳት የሙስና ወንጀል ተከሰዋል። 15ኛ ክስ በ13ኛ ተከሳሽ ላይ ብቻ ወንጀሉ በ1996 ዓ.ም የወጣውን የኢ.ፌ.ዴ.ሪ የወንጀል ህግ አንቀፅ 40፣419 እና 684 ላይ የተመለከቱትን ድንጋጌዎች በመተላለፏ፣ የወንጀሉ ዝርዝር ተከሳሿ ባለቤቷ የሆነው 2ኛ ተከሳሽ ግንቦት 2 ቀን 2005 ዓ.ም በሙስና ወንጀል ተጠርጥሮ በቁጥጥር ሥር ከዋለ በኋላ ተጠርጣሪው የተጠረጠረበትን የወንጀል ፍሬ መሆናቸውን እያወቀች ባለቤቷ በፈፀመው የወንጀል ድርጊት ከመከሰስና ከመቀጣት እንዲያመልጥ ለመርዳት፡- 1. በአቶ ገ/ዋህድ ወ/ጊዮርጊስ ወ/ሚካኤል ስም ተመዘገበ የባንክ ደብተር ቁጥር 0123586 የሆነ ብር 10000 (አስር ሺ) ተቀማጭ ያለው፤ 2. ካርታ ቁጥር L/X/L/D/3139/00/06/01 ከለገጣፎ ለገዳዲ አስተዳደር ለገ/ዋህድ ወ/ጊዮርጊስ የተሰጠ፤ 3. በአቶ ገ/ዋህድ ወ/ጊዮርጊስ እና በወ/ሮ ሀይማኖት ተስፋዬ ስም ለኦሮሚያ ኢንተርናሽናል ባንክ ብር 820,000 (ስምንት መቶ ሃያ ሺ ብር) ብድር ለመጠየቅ የተሞላ ቅፅ፤ 4. በአቶ ገ/ዋህድ ወ/ጊዮርጊስ እና በኮ/ል ሃይማኖት ተስፋዬ ስም ለኦሮሚያ ኢንተርናሽናል ባንክ ብር 1,000,000 (አንድ ሚሊዮን ብር) የባንክ ሼር ለመግዛት የጠየቁበት ሰነድና የተለያዩ የቤት ፕላኖችን ከላይ በተጠቀሰው ቀንና ቦታ እህቷ ለሆነችው ወ/ሮ ንግስቲ ተስፋ ገ/ስላስ እና አቶ ሀብቶም ገ/መድህን ገ/የስ ለተባሉ ግለሰቦች አሳልፋ በመስጠትዋ በፈፀመችው ወንጀል ከተፈፀመ በኋላ ወንጀል አድራጊውን መርዳት ወንጀል ተከሳለች። 16ኛ ክስ በ2ኛ ተከሳሽ ላይ ብቻ ወንጀሉ በ1996 ዓ.ም የወጣውን ኢ.ፌ.ዴ.ሪ. የወንጀል ህግ አንቀፅ 808(ሀ) ላይ የተደነገገውን በመተላለፉ፣ የወንጀሉ ዝርዝር ተከሳሹ የጦር መሳሪያ አያያዝና አጠቃቀም ደንብ ተከትሎ ፈቃድ ከሚሰጥ አካል አስፈቅዶ መያዝና መጠቀም ሲገባው ከሚመለከተው ፈቃድ ሰጪ አካል ሳያስፈቅድ የመኖሪያ ቤቱ በ02/09/05 ዓ.ም በፍ/ቤቱ ትዕዛዝ ብርበራ በተካሄደበት ወቅት፡- 1. የውግ ቁጥር 1529 የሆነ ባለ አንድ እግር ታጣፊ ክላሽ፣ 2. የውግ ቁጥር 0624 የሆነ ባለ አንድ እግር ታጣፊ ክላሽ፣ 3. የውግ ቁጥር ሠበ0402 የሆነ ማክሮቭ ሽጉጥ 4. የውግ ቁጥር የሌለው ማካሮቭ ሽጉጥ፣ 5. የውግ ቁጥር የሌለው ኮልት ሽጉጥ፣ 6. የውግ ቁጥር 47391 ኮልት ሽጉጥ፣ 7. የውግ ቁጥር NK252926 ማካሮቭ ሽጉጥ፣ 8. የውግ ቁጥር የሌለው ማካሮቭ ሽጉጥ 9. የውግ ቁጥር 2235 ስታር ሽጉጥ እና 10. የተለያዩ ጥይቶችን ይዞ በመገኘቱ በፈፀመው እንዲይዝ ያልተፈቀደለትና ፈቃድ የሌለው የጦር መሳሪያ ይዞ መገኘት ወንጀል ተከሷል። 17ኛ ክስ በ8ኛ ተከሳሽ ላይ ብቻ ወንጀሉ በ1996 ዓ.ም የወጣውን የኢ.ፌ.ዴ.ሪ. የወንጀል ህግ አንቀፅ 419(1)(ለ) ላይ የተደነገገውን በመተላለፉ፣ የወንጀሉ ዝርዝር ተከሳሹ በገቢዎችና ጉምሩክ ባለስልጣን የመንግስት ሰራተኛ ሆኖ በሰራበት ከ22/11/87 ዓ.ም እስከ 30/7/2004 ዓ.ም ድረስ ባሉት ጊዜያት ተቀጥሮ ሲሰራ በወር ይከፈለው የነበረው ያልተጣራ ደሞዝ ከብር 445 (አራትመቶ አርባ አምስት) እስከ ብር 8,651 (ስምንት ሺ ስድስትመቶ ሃምሳ አንድ ሺህ) ሲሆን በመንግስት ስራ ላይ እያለ ያገኝ ከነበረው ከህጋዊ ገቢው ጋር የማይመጣጠን፡- 1ኛ/ ግንቦት 2 ቀን 2005 ዓ.ም በመኖሪያ ቤቱ ብርበራ ተደርጎ የተገኘ ብር 1,947,676.10 /አንድ ሚሊዮን ዘጠኝ መቶ አርባ ሰባት ሺህ ስድስት መቶ ሰባ ስድስት ብር ከአስር ሳንቲም/፣ 2ኛ/ በተለያዩ ባንኮች እና የአክሲዮን ማህበራት በተከሳሽ ስም የተቀመጠ በድምሩ ብር 2,090,880.03 /ሁለት ሚሊዮን ዘጠኛ ሺ ስምንተ መቶ ሰማንያ ብር ከአስር ሳንቲም/ 3ኛ/ በተከሳሽ ስም ቦንድ የተገዛበት ብር 20,000 /ሃያ ሺህ ብር/ 4ኛ/ በአዲስ አበባ ልደታ ክ/ከተማ ፣ ወረዳ 24፣ ቀበሌ 02/03 በተከሳሽ ደሞዝ በምትተዳደረው ባለቤቱ ወ/ሮ ሀዲስ ሙሉ ስም ተመዘግቦ የሚገኝ 74.56 ካ/ሜ ስፋት ላይ የተሰራና ግምቱ ብር 200,000 /ሁለት መቶ ሺህ ብር/ የሆነ ባለ ሁለት መኝታ ኮንደምኒየም ቤት፣ 5ኛ/ በተከሳሽ ደሞዝ በምትተዳደረው ባለቤቱ ወ/ሮ ሀዲስ ሙሉ ስም በተለያዩ ባንኮች የተቀመጠ በድምሩ ብር 185,641.19 (አንድ መቶ ሰማንያ አምስት ሺህ ስድስት መቶ አርባ አንድ ብር ከአስራ ዘጠኝ ሳንቲም/ 6ኛ/ በተከሳሽ ደሞዝ በምትተዳደረው ባለቤቱ ወ/ሮ ሀዲስ ሙሉ ስም አክሲዮን የተገዛበት ብር 5,000፣ አምስት ሺህብር/፣ 7ኛ/ በተከሳሽ ደሞዝ በምትተዳደረው ባለቤቱ ወ/ሮ ሀዲስ ሙሉ ስም ቦንድ የተገዛበት ብር 10,000 /አስ

No comments:

Post a Comment