Tuesday, October 29, 2013

MUST READ የኢዴፓ ገበና ሲገለጥ (ሊነበብ የሚገባው ደባ) ዶክተር በየነ እና ሻለቃ አድማሴ በአቶ መለስ ትእዛዝ የወር ደምወዝ ነበራቸው::

by Minilik Salsawi የኢዴፓ ገበና ሲገለጥ (ሊነበብ የሚገባው ደባ) የልደቱ አያሌው ኢዴፓ በየትኛው ሞራሉ ነው ተቃዋሚውንም ይሁን ገዢውን ፓርቲ የሚተቸው?? #Ethiopia #EPRDF #UDJ #EDP #BLUEPARTY ምንሊክ ሳልሳዊ የአቶ ልደቱ አያለውን መጽሃፍ የጻፈው በወያኔ ልዩ ትእዛዝ አቶ ገነነ አሰፋ ነው::
ዶክተር በየነ ጴጥሮስ እና ሻለቃ አድማሴ መላኩ በአቶ መለስ ትእዛዝ የወር ደምወዝ ነበራቸው:: ማንኛውም ኢትዮጵያዊ በኢዴፓ ህልውና አያምንም::ዘላለም ህዝቡ ኢዴፓን በበጎ መንፈስ አያየውም:: በአሁን ሰአት ለተፈጠረው ኢሕኣዴጋዊ አክራሪነት እና የፖለቲካ ጽንፈኝነት ተጠያቂው ኢዴፓ እና አመራሩ ናቸው:: ኢዴፓ ብሎ ራሱን የሚጠራው በኢሕኣዴግ የጎለበተው ድርጅት ባካሄደው ስብሰባ ተቃዋሚ ፓርቲዎችን እና ገዢውን ፓርቲ እንደተቸ እየሰማን ነው:: ኢዴፓ የ97 ምርጫ የህዝብን ድምጽ አፈር የከተተ እና ከገዢው ፓርቲ ጋር መሰሪ ተግባራትን በማከናወን የቅንጅት አመራርን ለእስር ቅንጅትን ደግሞአላማውን በማኮላሸት ድባቅ እንዲመታ ያደረገ ታማኝ ቅጥረኛ በራሱ አጠራር ተቃዋሚ ፓርቲ ነው::ኢዴፓ ለዚህ ላደረገው አፍራሽ ተልእኮ አመራሮቹን ሳይታሰሩበት የፓርላማ ወንበር እና ጉርሻ በማግኘት ተለጥጦ እስከዛሬ ድረስ በገዢው ፓርቲ አመራሮች እና ካድሬዎች የአንበሳነት ቡራኬ እየተሰጠው ይገኛል:: ኢዴፓ በተለያዩ ከገዢው ፓርቲ በተመደቡ የደህንነት ሴረኞች እና ከመንግስት ስልጣን ወደ ፓርቲ ስልጣን በተለወጡ ሰዎች እንዲሁም በተለያዩ ክልሎች በኢንቨስትመት ስራ ለይ የተሰማረን ነን የሚሉ ከባለስልታናት ጋር በሙስና የተጨማለቁ ሰዎች የሞሉበት በተቃዋሚነት ስም የሚያላዝን የገዢው ፓርቲ አጋር የፖለቲካ አራጋቢ ነው::የገዢውን ፓርቲ ሁኔታ ገመገምኩ የሚለው ኢዴፓ ገዢው ፓርቲ ከፕሮፓጋንዳ ባለፈ ለዴሞክራሲ ሥርዓት መጠናከር ምንም ዓይነት ተጨባጭ ዕርምጃ እየወሰደ እንዳልሆነና ይህም በአገሪቱ የጽንፈኝነት ፖለቲካና አክራሪነት የበለጠ እየተጠናከረ እንዲመጣ አድርጓል ማለቱ ምን ለማለት እና ማንን ለማጭበርበር ፈልጎ አሊያም በየትኛው ሞራሉ ነው ይህንን ሊል የሚችለው ... በሃገሪቱ በ1997 እና ከዛ በኋላ የተገኙ የተቃዋሚ ድሎች እንዲኮላሹ ከማድረጋቸውን በላይ የድርጅቱ አመራሮች ሕወሓት ከመደበላቸው ከአቶ ስብሃት ነጋ በሚወርድ ትእዛዝ የዲሞክራሲ ጭላንጭሉ ከናካቴው እንዲጠፋ እና አሁን ላለንበት የጭለማ አፋኝ ስርኣት እንድንዳረግ አስታውጾ አበርክቷል::በአሁን ሰአት ለተፈጠረው ኢሕኣዴጋዊ አክራሪነት እና የፖለቲካ ጽንፈኝነት ተጠያቂው ኢዴፓ እና አመራሩ ናቸው:: አቶ ልደት አያሌው ኢዴፓን ይመራ በነበረበት ጊዜ በየወሩ 5000 ብር ይከፈለው ነበር እንዲሁም ሙሼ ሰሙ ዶክተር ሶፊያ እና አቶ አብዱ .. እንዲሁ ደሞወዝ ነበራቸው:: አቶ ልደቱ የደህንነት ሚኒስትሩ የነበሩት አቶ ገብረመድህን እስከ 1993 ድረስ ደሞዙን በመቀበል የቆየ ሲሆን ከዛ በኋላ ደሞዛቸውን በበላይነት የሚያገኙት አሁን በሙስና እስር ላይ ከሆነው የደህንነቱ አማካሪ አቶ ወልደስላሴ ወልደሚካኤል ነበር::በ97 ላደረጉት ውለታ ከስድስት ሚሊዮን ብር ስጦታ አግኝተዋል:: ለኢዴፓ አመራሮች ያዘጋጁትን መጽሃፍ ; ንግግር ; ማንኛውንም አርቲክል የጻፈው የገነት ዘውዴ ውንድም አቶ ገነነ አሰፋ ነበር ለዚህም በአቶ መለስ ዜናዊ ትእዛዝ ትልቅ የገንዘብ ጉርሻ ተሰቶታል::ታሪካቸው የማያልቀው ተቃዋሚ ነን የሚሉት የፓርቲዎችን እንቅስቃሴ ውስጥ ውስጡ እንዲያሽመደምዱ በወቅቱ የፓርላማ አባል የነበሩት ሻለቃ አድማሴ መላኩ እና ዶክተር በየነ ጴጥሮስ ከአቶ መለስ ዜናዊ በተሰጠ ልዩ ምስጢራዊ ትእዛዝ በየወሩ የደህንነቱ አማካሪ የአሁኑ እስረኛ ወልደስላሴ ደምወዝ ይከፍላቸው ነበር:: ኢዴፓ አሁንም በህዝብ ፊት ቆሞ የህዝብን ማንነት ለመካድ እና ራሱን እንደ ህዝብ ፓርቲ ለማሳየት የሚቧጥጠው ነገር እንደማይሳካለት ቢያውቅም ከወያኔ በሚወርድለት ትእዛዝ በሙስና የተዘፈቁ የኮሌጅ ባለቤት የሆኑ የአማራ ክልል ግለሰብ አምጥቶ ሾሟል::የጸረ ሽብር ህጉን እንደግፋለን የሚሉት ከአማራ ክልል ባለስልጣናት ጋር በእከክልህ እከክልኝ ኢንቨስተር የሆኑት የኢዴፓ አዲስ ሊቀመንበር ሙሰኛው አቶ ጫኔ ከበደ በኢትዮጵያ በእስር ላይ የሚገኙ የፖለቲካ መሪዎች ጋዜጠኞች እና የሃይማኖት ሰዎች አሸባሪ ናቸው ብለው የሚያምኑ ሰው ናቸው:: እንደ ኢዴፓ/ኢሕኣዴግ እምነት ተቃዋሚዎች የኢዴፓን የተቃዋሚነት ሚናና ህልውና የካዱና፣ በሕዝቡ ዘንድ በበጎ መንፈስ እንዳይታይ ሆን ብለው ሴረኛ አሉባልታዊ ዘመቻ የሚያካሂዱ መሆናቸውን መገንዘቡን ገልጿል፡፡ እነዚህ ፓርቲዎች የወቅቱ ትግል ተጠናክሮ ለድል እንዳይበቃ ዋነኛ እንቅፋት መሆናቸውን ገልጾ ሕዝቡ የእነዚህን ተቃዋሚ ኃይሎች ትክክለኛ ማንነት እንዲገነዘብ ጠይቋል፡፡...ኢዴፓ ለገዢው ፓርቲ ታማኝነቱን ያሳየበት ይህ አባባል አሁንም ቢሆን ኢዴፓ ማወቅ ያለበት ነገር ቢኖር ማንኛውም ኢትዮጵያዊ በኢዴፓ ህልውና አያምንም::ህዝቡ ኢዴፓን በበጎ መንፈስ አያየውም:: ኢዴፓ 200 አመት እንደ አዲስ እየተወለደ ቢሰራ ተቀባይነት አያገኝም::በሃገር ቤት ያሉ ተቃዋሚዎች ሳይሆኑ ትግሉን አፈር እያበሉት ያሉት እንደ ኢዴፓ ያሉ ቅጥረኞች መሆናቸውን በአደባባይ ያየነው ጉዳይ ነው::ማንኛውም ተቃዋሚ ፓርቲ ከኢዴፓ ጋር በትብብር እንደማይሰራ የታወቀ ሲሆን ኢዴፓ ራሱ ራሱን መርምሮ ከቅጥረኝነት ወደ ተቃዋሚነት መሸጋገር የራሱ ድርሻ እንጂ ለሌሎች የሚሰጠው መመሪያ አይደለም:: ሌሎች ተቃዋሚ እንደሆኑ ራሳቸውን ያውቃሉ:: የስልጣን ጥመኝነት ያለበት የኢዴፓ አመራር በየትኛው ሞራሉ ህዝብ ፊት እንደሚቀርብ ባይታወቅም በፖለቲካ እፍረት የማይሰማው ቅጥረኛ ፓርቲ መሆኑን ግን በይፋ ያስመሰከረ እና የሆዳሞች እና የሙሰኞች ስብስብ እንደሆነ ማናችንም የምንመሰክረው ሃቅ ነው:

No comments:

Post a Comment