Wednesday, October 30, 2013

የትግራይ ክልል የፍትህ ቢሮ ሃላፊ አቶ ተስፋአለም ይሕደጎና በስሩ የሚገኙ ህግ አስከባሪዎች በሙስና ተጨማልቀዋል የሚል ግምገማ ቀረበባቸው፣

October 30, 2013 የክልሉ የካብኔ አባላት ጥቅምት,9,2006 ዓ/ም ባካሄዱት ስብሰባ ከክልሉ የፍትህ ቢሮ ሃላፊ ጀምሮ እስከ የታችኛው አቃቢ ህግ ድረስ ፍትህን በመተላለፍ በጉቦና ጥቅማጥቅም በመስራት በሙስና በመጨማለቃቸው ምክንያት ተገልጋዩ ህዝብ ፍትህ ተነፍጎት ያለፉትን ስርዓቶች ወደ እሚናፍቅበት ደረጃ ደርሷል በማለት መገምገማቸውን ቷውቋል፣ በስብሰባው አቶ ተስፋ አለምን ጨምሮ ሁሉም የካብኔ አባላት የተገኙ ሲሆን ከስድስት በላይ አቃብያን ህግ ጉቦ ሲቀበሉ እጅ ከፈንጅ ተይዘው እያለ ለምን ወደ ካብኔ ቀርበው እንዲገመገሙ አልተደረገም የሚል ጥያቄ የቀረበ ቢሆንም እውነት ነው ተሳስተናል በሚል ተሽፋፍኖ ማለፉን ለማወቅ ተችሏል ፣ ጉቦ ሲቀበሉ እጅ ከፈንጅ ከተያዙት አቃብያን ህግ መካከል።- 1-በየነ ሓውዜናይ—ከማእከላዊ ዞን 2-ብርሃነ ገ/መድህን—ከሸራሮ ከተማ 3-ጥላሁን ገ/የሱስ—-ከሸራሮ ከተማ 4-ወ/ሮ ትእግስት እምባሁን —-ከአዲግራት ከተማ ናቸው፣ Source : ትሕዴን

No comments:

Post a Comment