Saturday, October 26, 2013

ወደ ሶማሌ ክልል አቅንቶ የነበረው የወያኔ መንግስት ባለስልጣኖች ቡድን ምክትል ጠቅላይ ሚንስትሩን ጨምሮ የመኪና አደጋ ገጠመው

ለሃገር ልማት ግንባታ እና የመንገድ ዝርገታ ሂደት የተሰኘውን ጉዙ ለማየት ከአዲስ አበባ ወደ ሶማሌ ክልል ያቀናው የወያኔ መንግስት ባለስልጣናት ቡድን በጉዞው ወቅት ከፍተኛ የሆነ የመኪና አደጋ ገጥሞት እንደነበር ምንጮቻችን ጠቁመዋል ።እንደምንጮቹ ገለጻ ከሆነ ባለስልጣናቱ እና የክልል አስተዳደር በአጠቃላይ ተሰባስበው የሚሄዱበት መኪና ከሞተር ሳይክል ጋር በመጋጨት ከፍተኛ ጉዳት የደረሰባቸው መሆኑን ይገልጻል ።በሶማሌ ክልል በቀብሪደሃር የደረሰው ይህንን አደጋ አስመልክቶ ማንኛውም የመንግስትም ሆነ የግል መዲያዎች እንዳይዘግቡት ተብሎ ማስጠንቀቂያ በቅርቡ ለነበሩት ድደህንነቶችም ሆነ ሌሎች ባለስልታናት
የተገለጸ ቢሆንም ይህ ወሬ አፍትልኮ መውጣቱን ምንጫችን ይጠቅሳል ።ከ250 በላይ የሚሆኑትን ባለስልጣናት እና እንዲሁም ባለሃብቶችን የያዘውን አባሎች በብሄራዊ ቴሌቪዝን የእንኳን ደህና መጣችሁ አቀባበልበአብዲ ሞሃመድ ሁመር ጎዴ አየር መንገድ ጣቢያ ላይ የሚያደርጉትን የአቀባበል ስነ ስርአት የሚያሳይ ብቻ ምስል ማቅረባቸው የሚዘነጋ አልነበረም ሆኖም ግን ስለ ግጭቱ አንዳችም ነገር ሊጠቆም አልተቻለም ።Somali Regional Chief Abdi Mahamoud Omar receiving the delegation led by DPM Demeke Mekonnen at Gode airport የአደጋው መረጃ ተብሎ የተገለጸውም ብሄራዊ የኦጋዴን ግንባር የተሰኘው የተቃዋሚ ድርጅት በመንግስት ባለስልጣን ላይ በከፈተው የማጥቃት ዘመቻ ለማምለጥ ሲሉ ከሞተር ሳይክል ጋር በመጋጨት አደጋው ሊፈጠር እንደቻለ መረጃው አጠናክሮ ይገልጻል ።ይሄው መኪና ምክትል ጠቅላይ ሚስንትሩን አቶ ደመቀ መኮንን ይዞ የነበርው መኪና እንደነበር የማለዳ ታይምስ ምንጮች አክለው ገልጸዋል ። እንደ ዘገባው ከሆነ በወቅቱ ይህንን አይነት ጥቃት ሲፈጸምባቸው በፍጥነት ሊጠመዘዝ የሞከረው የምክትል ጠቅላይ ሚንስትሩ ተሽከርካሪ በእግረኛ መንገድ ላይ ይጓዙ የነበሩ ሁለት ሰዎችን በመምታቱ ከፍተኛ ጉዳት ያደረሰ መሆኑን እና የካሳ ክፍያ በጠቅላይ ሚንስትሩ ወደ 300፣000 የሚጠጋ ብር ሊከፍሉ እንደፈለጉ እና በልመና ላይ እንደነበሩ አሳውቆአል ።በየጊዜውም በመንግስት ላይ ያላቸውን ተቃውሞ ለማሳየት በተለያዩ መንግስታዊ ድርጅቶች ላይ ጥቃት የሚፈጽሙት የኦጋዴን የተቃውሞ ሃይል ዛሬም እንቀጥላለን ሲሉ ዛቻቸውን በመንግስት ላይ አስፍረዋል ።ለበለጠ መረጃ ይህንን ሊንክ ይጫኑ http://africaim.com/gov-source-refutes-ethiopias-deputy-pm-was-involved-in-car-accident/

No comments:

Post a Comment