Thursday, August 22, 2013

August 22 ,,የቁጫ የአገር ሽማግሌዎች በጠቅላይ ሚ/ሩ ጽህፈት ቤት ተገኙ

የቁጫ የአገር ሽማግሌዎች በጠቅላይ ሚ/ሩ ጽህፈት ቤት ተገኙ
ነሃሴ ፲፮(አስራ ስድስት)ቀን ፳፻፭ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- 60 የሚጠጉ የወረዳዋ ሽማግሌዎች በዛሬው እለት ለ7ኛ ጊዜ በጠ/ሚ ሀይለማርያም ደሳለኝ ጽሀፈት ቤት ቢገኙም ጠ/ሚኒስትሩን ሊያገኙዋቸው እንዳልቻሉና በተወካያቸው በአቶ ወርቁ በኩል መንግስት ጉዳዩን ለፌዴሬሽን ምክር ቤት ያሳውቃል የሚል መልስ እንደተሰጣቸው ለኢሳት ገልጸዋል። በመንግስት መልስ ደስተኞች ያለሆኑት የአገር ሽማግሌዎች፣ እንደገና ተመልሰው ወደ ክልሉ ዋና ከተማ አዋሳ ማቅናታቸው ታውቋል። ሽማግሌዎቹ ለጠ/ሚንስትር ሀይለማርያም ተወካይ ፣ ወደ ቦታችን ስንመለስ እንደማንታሰር ዋስትና ይሰጠን በማለት ቢጠይቁም፣ ተወካዩ የሚያስሩዋችሁ ከሆነ በቀጥታ ደውሉልኝ ብለው ስልካቸውን እንደሰጡዋቸው ገልጸዋል። የአገር ሽማግሌዎች ወደ ጠቅላይ ሚኒሰትሩ ጽ/ት ቤት ለመሄድ ያስገደዳቸው በወረዳው የሚታሰረው ሰው ቁጥር እየጨመረ በመምጣቱና ይህን ተከትሎም ግጭት ሊነሳ ይችላል የሚል ስጋት በመኖሩ አስቀድሞ ለማሳወቅ ነው ብለዋል። በአካባቢው እየደረሰ ያለው የመብት ጥሰት ፣ በአገሪቱ መንግስት አለ ወይ የሚያስብል መሆኑን ከሽማግሌዎቹ አንዱ ተናግረዋል። እስካሁን ድረስ ቁጥሩ በትክክል ባይታወቅም ከ90 እስከ 100 የሚደርሱ ሰዎች መታሰራቸውን ሽምግሌዎቹ ይናገራሉ። መረጃውን ከቀበሌ ቀበሌ በማመላለስ ግጭት እንዲፈጠር ያደርጋሉ የተባሉ 160 ባጃጅ የሚባሉ ተሽከርካሪዎች አሁንም ፖሊስ ጣቢያ ቆመዋል። ከ30 በላይ ሰራተኞችም ተባረዋል። የቁጫ ወረዳ ነዋሪዎች በቋንቋችን እንጠቀም፣ ሌሎች መብቶቻችን ይከበሩልን የሚሉ ጥያቄዎችን ማ

No comments:

Post a Comment