Monday, November 10, 2014

የመኢአድ ጠቅላላ ጉባኤው ተጠናቀቀ – እነ አቶ አባበው ለቀው ወጡ


64205_589493681108302_1870617069_n
ነሐሴ ወር 2006 ዓ.ም መኢአድ እና አንድነት ዉህደት ይፈጽማሉ ተብሎ ተጠብቆ እንደነበረና የሕወሃት ምርጫ ቦርድ ለመኢአድ አመራር እውቅና አልሰጥም በሚል ዉህደቱን ማጨናገፉ ይታወቃል። ከሁለት አመታት በላይ በአቶ አበባው መሐሪ ከሚመራው መኢአድ ጋር ደብዳቤዎች ሲጻጻፍ የነበረው ምርጫ ቦርድ ፣ አንድም ጊዜ በአመራሩ ላይ ጥያቄ አንስቶ ሳያውቅ፣ ዉህደት ሊደረግ ሲል፣ ሸንካላ ምክንያት በመፍጠር ሆን ብሎ ዉህደቱን ማጨናገፉ፣ ምርጫ ቦርዱ በሕወሃት አመራር ታዞ ያደረገዉ እና ምንም አይነት ገለልተኝነት እንደሌለው ያሳየበት እንደሆነ ብዙዎች ያናግራሉ።
የምርጫ ቦርድን ሕገ ወጥ ጥይቄ ለማሟላት መኢአድ ቅዳሜ ጥቅምት 29 እና እሁድ ጥቅምት 30 ጠቅላላ ጉባኤ ጠርቶ የነበረ ሲሆን፣ ጠቅላላ ጉባኤው ባለመስማማት እንደተጠናቀቀ ለማወቅ ችለናል።
አርብ ጥቅምት 28 ቀን፣ የመኢአድ ላእላይ ምክር ቤት ተሰብስቦ የመኢአድ አመራር የነበሩና በተለያዩ ችግር የተገለሉ ፣ አቶ ማሙሸት አማረን ያካተተ ፣ 14 ሰዎችን ጉዳይ፣ ጠቅላላ ጉባኤው በነገታው ዉሳኔ እንዲያሳልፍ ስምምነት የተደረሰ ሲሆን፣ ምንም እንኳን ከአንድንት ጋር ሊደረግ የነበረዉን ዉህደቱ ምርጫ ቦርድ ቢያጨናግፈውም፣ የምርጫ ዘመቻውን ከአንድነት ጋር በተቀናጀ መልኩ ለማድረግ በጠቅላላ ጉባኤው ዉሳኔ ለማስወሰን ታስቦም እንደነበረ ለማወቅ ችለናል።
ቅዳሜ ጥቅምት 29 ቀን ጠቅላላ ጉባኤው በአቶ ሃይሉ ሻዉል መሪነት የተከፈተ ሲሆን፣ ከ335 በላይ የጠቅላላ ጉባኤ አባላት ተገኝተዉም ነበር። እነ አቶ ማሙሸት በርካታ ሰዎች በስብሰባው እንዲገኙ ማድረጋቸዉንም ለማረጋገጥ ችለናል።
በስብሰባው ወቅት በአቶ ኃይሉ ሻዉልና በአቶ አበባው መሐሪ መካከል ጠንካራ ልዩነቶችና አለመስማማቶች የነበሩ ሲሆን ስብሰባው በጥሩ ሁኔታ እንዳልተጠናቀቀም ለማውቅ ችለናል። አቶ አበባው፣ ከሁለቱ በስተቀር የሥራ አስፈጻሚ አባላት በሙሉ ለደህንነታቸው ፈርተናል በሚል ስብሰባዉ ጥለው እንደወጡ መረጃዎች ይጠቁማሉ። ከስብሰባው ከወጡት መካከል የመኢአድ የሕዝብ ግንኙነት ክፍል ሃላፊው አቶ ተስፋሁን አለምነህም ይገኙበታል።
ስብሰባው እሁድ ጥቅምት 30 በቀሩት በአብዛኛው እነ አቶ ማሙሸት የሰበሰቧቸው ተወካዮች ባሉበት አቶ ማሙሸት አማረን የመኢአድ ፕሬዘዳንት አድርገው መርጠዋል።
ጠቅላላ ጉባኤው ቅዳሜ ጥቅምት 29 ቀን የተደረገ እለት የምርጫ ቦርድ ተወካይ እንዳልነበረም የደረሰን ዘገባ ሲያመለክት፣ የምርጫ ቦርድ ተወካይ በሌለበት፣ አብዛኛው የጠቅላላ ጉባኤ ተወካዮች አልተገኙም በተባለበት የተደረገ ምርጫ ምን ያህል ሕጋዊ ሊሆን እንደሚችል ግልጽ የሆነ ነገር እንደሌለ ከመኢአድ አባላት የሚደርሱ ዘገባዎች ይገልጻሉ።
ከአራት አመታት በላይ ያልታዩት ኢንጂነር ኃይሉ ሻዉል፣ በዚህ መልኩ ስብሰባው በሰላም እንዲጠናቀቅ አለማድረጋቸው እንዳልተደሰቱ የሚገልጹት አንድ ያነጋገርናቸው የመኢአድ አባል ለመኢአድ አሁን ያለበት ደረጃ በዋናነት ተጠያቂው አቶ ኃይሉ ሻወል እንደሆኑ ይናገራሉ።
በመኢአድ እና በአንድነት መካከል ሊደረግ ታስቦ የነበረ አብሮ የመስራት ዉሳኔ በነበረው አለመስማምምት አልመሳካቱ ጥሩ እንዳልነበረ የተናገሩት እኝሁ የመኢ፤አድ አባል፣ “አብዛኛው የመኢአድ አባል ከአንድነቶች ጋር እየታሰረ፣ እየተደበደበ፣ እየተገደለ ነው። በተግባር የመኢአድ እና የአንድነት አባላት አንድ ናቸው” ሲሉ በአመራሮች ዘንድ አለመስማማቶች ቢፈጠሩም በሜዳ በየዞኑና በየወረዳው ያለው የመኢአድ ታግይ እንኳን እርስ በርሱ እንደ አንድነቶ ካሉ ሌሎች የትግል አጋሮቹ ጋር አንድ ሆነ እየሰራ እንደሆነም ይገልጻሉ።
በጉዳዩ ላይ ያነጋገርናቸው ከበርካታ ተወካዮች ጋር ስብሰባዉን ለቀው የወጡት አንድ የመኢአድ ከፍተኛ አመራርር አባል፣ በማንም ድርጅት አለመስማማቶች እንደሚፈጠሩ ገልጸው፣ ብሶት ለመናገር ወደ ኢቲቪ እንደማይሮጡ ገልጸዋል።
በአቶ አማረ ማሙሽት የሚመራው መኢአድ ጽ/ቤቱን ተቆጣጥሮ አዲስ ካቢኔም እንዳዋቀረ ለማወቅ ችለናል። በዚሁ መሰረት አዲስ ካቢኔ የሚከተሉት አባላትን አካቷል፡
1: አቶ ማሙሸት አማረ (ፕሬዝዳንት)
2: ዶ/ር ታዲዎስ ቦጋለ (ተቀዳሚ ምክትል ፕሬዝዳንት)
3: አቶ እንድርያስ ኤሮ (ምክትል ፕሬዝዳንት)
4: አቶ ተስፋየ መላኩ (ዋና ፅሃፊ)
5: አቶ ሰማሀኝ አብርሃም (የድርጂት ጉዳይ)
6: ኮኔሌር ትርሶት ጉልላት(የህዝብ ግንኙነት)
ገ: ወ/ሮ አለማየሁ ሞገድ (የሴቶች ጉዳይ)
8: አቶ አብርሀም ጌጡ (የውጭ ጉዳይ)
9: አቶ ሀብተማርያም ያንተ(ፋይናንስና አስተዳድር)
10: አቶ ታጠቅ አሰፋ (የወጣቶች ጉዳይ)
11:አቶ ሀይለየሱስ ሚናስ (የምርጫ ጉዳይ)
13:አቶ ተስፋሁን አለምነህ (ትምህርትና ስልጠና አላፊ)
14 : መ/አ አየለ አለ(የህግና ዲስፕሊን አላፊ)
15: አቶ ወርቁ ከበደ (የምሃል ቀጠና ሃላፊ)
16: አቶ አዳነ ጥላሁን(የሰሜን ቀጠና ሃላፊ)
17: አቶ ብሩ ደሲሳ( የምራብ ቀጠና ሃላፊ)
18: አቶ ገለቱ ደጀርሳ (የደቡብ ቀጠና ሃላፊ)
19: አቶ ተፈራ መንግስቴ (የምስራቅ ቀጠና ሃላፊ)
ግርማ በለጠ

No comments:

Post a Comment