Monday, January 12, 2015

ታሪካዊው ጣይቱ ሆተል ተቃጠለ:

- በውስጥ እና በውጭ የተከሰተበትን የፖለቲካ ውጥረት አቅጣጫ ማስቀየሪያ ነው::
- ጣይቱ ሆቴል ስዬ አብርሃ ለቅርብ ዘመዳቸው ለሆኑት አቶ ፍፁም ዘአብ ሽጠዋል።
በኢትዮጵያ የመጀመሪያ ዘመናዊ ሆቴል የሆነውና ለሀገሪቱ እና ለሕዝቡ እንደ ታላቅ ቅርስ የሚታየው ጣይቱ ሆቴል ተቃጠለ። በቦታው የነበሩ የዓይን ምስክሮች እንዳሉት ሆቴሉ መሉ በሙሉ ሊባል በሚችል ሁኔታ በእሳት ጋይቷል።
በሃገሪቱ ውስጥ የተከሰተው የፖለቲካ አጣብቂኝ ውስጥ የገባው ወያኔ በምርጫው ጉዳይ እና በተለያዩ የምእራባውያን ጫና የተወጠሩት በህዝብ ጥያቄ የተጨነቁት የወያኔ ባለስልጣናት የህዝቡን የአስተሳሰብ አቅጣጫ ለማስቀየር እና ሃሳብ ለመስረቅ ለማስደንገጥ እና አዲስ መወያያ ጉዳይ ለመፍጠር ያደረገው ተንኮል ነው ሲሉ አስተያየት ሰጪዎች ይናገራሉ::
ከ 75% በላይ በእሳት የጋየው ጣይቱ ሆቴል እሳቱ የጀመረው ከማለዳው 2 ሰአት ቢሆንም እሳት አደጋ መኪኖች የደረሱት ግን 3.30 ሰአት ነው። ሆቴሉ አቶ ስዬ አብርሃ የፕራይቬታይዜሽን ሀላፊ በነበሩበት ወቅት ጣይቱ ሆቴልን እና ጉለሌ ሳሙና ፋብሪካን ለቅርብ ዘመዳቸው ለሆኑት አቶ ፍፁም ዘአብ ሽጠዋል።
በ 1993 ሕወሃት ለሁለት ተሰንጥቆ አቶ ስዬ የሙስና ክስ ሲመሰረትባቸው የጣይቱ ሆቴል ጉዳይ በክሱ ላይ ተመልክቷል። የሆቴሉ ባለቤትም አቶ ፍፁም ለበርካታ አመታት በእስር መቆየታቸው ይታወሳል።
አቶ ፍፁም ዘአብ በሂደት ላይ ባለው በእነ አቶ መላኩ ፈንታ የሙስና መዝገብ ታስረው የነበረው ሲሆን አቃቢ ህግ በቂ ክስ አላቀረበባቸውም በማለት በነፃ ተሰናብተዋል።
ፒያሳ የተነሳውን እሳት ለማጥፋት ባካባቢው የደረሱ የእሳት አደጋ ሰራተኞች ቅድምያ ገንዘብ በመጠየቃቸውና በሚከፈላቸው ገንዘብ መጠን ዙሪያ በፍጥነት ስምምነት ላይ መድረስ ባለመቻላቸው እሳቱ ጌዜ አግኝቶ ሊስፋፋ ችሏል።
አንድ የአዲስ አበባ ነዋሪ እንዲህ በማለት ምሬታቸውን ገልጸዋል፣
“ፒያሳ ጣይቱ አከባቢ እያተቃጠለ ያለበት ሁኔታ ነው ያለው:: የእሳት አደጋ መኪና በቦታው ቢቆምም ውሃ የሚረጩት ከህዝቡ ጋር ሳንቲም እየተደራደሩ ባለበት ሁኔታ ንብረት እየተንቦለቦለ ነው:: ካጠፉት ብኋላ ገንዘብ ቢጠይቁ ምን ችግር አለው?”
ሌላኛው ወጣት ደግሞ እንዲህ ብሏል፣
“ልብ የሚሰብር ዜና - ጣይቱ ሆቴል እየተቃጠለ ነው። በአካባቢው ያለነው ወጣቶች ቀርበን እንዳናጠፋ ፓሊስ እያገደ ነው።”
አሁንም ሌላኛው ታዛቢ ሁኔታውን ሲገልጹ፣
"...እሳቱ ከተቀጣጠለ 5 ደቂቃ ብሗላ ወደ እሳት ኣደጋ ማጥፍያ ብርጌድ የተደወለ ቢሆንም በቦታው የተግኙት ግን ከኣንድ ሰዓት ንሗላ መሆኑ ታውቋል።" ብለዋል።
ሌላኛዋ የአዲስ አበባ ነዋሪ ሁኔታው እጅግ አስቆጥቷቸዋል እንዲህ ይላሉ፣
"ምንም አይነት ማስተባቢያ አያስፈልግም ከታሪክ ጋር ፀብ ያለው ወያኔ ታሪካዊውን ጣይቱ ሆቴልን አንድዶታል! በቅርቡ እዚሁ ሆቴል አቅራቢያ ለልማት ይነሱ የተባሉ ቤቶት በእሳት አጋይቶ ሲያነሳቸው አይተናል አሁንም የ 5 ደቂቃ ርቀት እንኩዋን የሌለው እሳት አደጋ እሳቱ እንደተነሳ ሲደወልለት እሳቱ ሙሉ ለሙሉ በሚባል ሁኔታ ይህን ታሪካዊ ሆቴል ካወደመው በዋላ በቦታው ተገኝተዋል ታዲያ ይሄ የማን ስራ ነው? ነው ወይስ ወያኔ ለታሪክ እሚራራ ቡቡ ልብ አለው እያላችሁን ነው?
ከታሪክ እና ከህዝብ ጋር የተጣላ ገዢ ለእያንዳንዷ ጥፋት ተጠያቂ ነው ጣቶች ሁሉ ወደሱ ይቀሰራሉ!!"
የአዲስ አበባ እና የሌሎችም ትልልቅ ከተሞች ነዋሪዎች በታሪካዊ የገበያ ስፍራዎችና በሌሎችም ታሪካዊ ቅርስነት ባላቸው ቤቶች እና ንብረት ላይ ለሚደርሱት የእሳት ቃጠሎዎች የመንግስት እጅ ሊኖርበት እንደሚችል ጥርጣሪያቸውን በተደጋጋሚ ይገልጻሉ።


No comments:

Post a Comment