Monday, September 1, 2014

Hiber Radio: የአንድነትና መኢአድን ውህደት ያገዱት የወ/ሮ አዜብ ወንድም መሆናቸው ተገለጸ፤ ከደ/ሱዳን ወደ ኢትዮጵያ የሚገቡ ስደተኞች የጉበት በሽታ እያስተላለፉ ነው


  • 1337
     
    Shar

የህብር ሬዲዮ ነሐሴ 4 ቀን 2006 ፕሮግራም
ጋዜጠኛ ሃብታሙ አሰፋ
ጋዜጠኛ ሃብታሙ አሰፋ<< ...መኢአድና አንድነትን እንይዋሃዱ ምርጫ ቦርድ የሰጠው ሕገ ወጥ ውሳኔን በቀጥታ የወሰነው የቦርዱ ጽ/ቤት ም/ ሀላፊ የወይዘሮ አዜብ መስፍን ወንድም ነው...መኢአድ የቦርዱን ውሳኔ በመቃወም ልዩ ልዩ ጠንካራ ተቃውሞዎችን ይጠራል። ስራ ማቆም አድማ እና ሌሎችንም ያካትታል ሕዝቡ ጥሪያችንን ይጠባበቅ ...>>
አቶ ተስፋሁን ዓለምነህ የመኢአድ የሕዝብ ግንኙነት ሀላፊ ለህብር ከሰጡት ማብራሪያ የተወሰደ (ሙሉውን ያዳምጡት)
<...ፕሬዝዳንት ኦባማ ጋና ላይ ከዓመታት በፊት ለአፍሪካ ጠንካራ መሪ ሳይሆን ጠንካራ ተቋማት ያስፈልጋል ያሉበትን ዛሬ ዘንግተዋል...ኢትዮጵያውያን ጠንካራ ተቃውሞ ማቅረባችን ጠቃሚ ነበር ይህ ባይሆን አሜሪካውያን አፍሪካውያን ደገፉት ይሉን ነበር... >
አቶ ኦባንግ ሜቶ አሜሪካ የኢትዮጵያን አምባገነኖችን በመጋበዙዋ የቀረበው ጠንካራ ተቃውሞ ውጤታማ መሆኑን ለህብር በሰጡት ቃለ መጠይቅ ገለጹ (ሙሉውን ያዳምጡት)
የአሜሪካና የቻይና የኢኮኖሚና የዲፕሎማሲ ግብ ግብ የሰብዓዊ መብት ጥሰት በተንሰራፋባት አፍሪካ ሜዳ ላይ (ልዩ ዘገባ)
ኢራቅ የተወለዱት አዲሶቹ አሸባሪዎችና በክርስትና ሀይማኖት ተከታይ ላይ ጭምር የፈጸሙት ጅምላ ግድያ እና የመስፋፋታቸው ስጋት (ልዩ ጥንቅር)
የኢትዮጵያዊነት ቀን ክብረ በዓል ዝግጅት በቬጋስ(ቃለ መጠይቅ)
ሌሎችም አሉ
ዜናዎቻችን
* የአንድነትና መኢአድን ውህደት በህገወጥ ውሳኔ ያገዱት የምርጫ ቦርድ ባለስልጣን የወ/ሮ አዜብ መስፍን ወንድም መሆናቸው ተገለጸ
* መኢአድ የቦርዱን ውሳኔ ሳይቀበል የስራ ማቆም አድማን ጨምሮ ጠንካራ ተቃውሞ እጠራለሁ አለ
* የእንግሊዝ መንግስት በአቶ አንዳርጋቸው ጉዳይ የኢትዮጵያውን አገዛዝ ባለስልጣናት ጠርቶ አነጋገረ
* ኢ/ር ግዛቸው ገዢው ፓርቲ በምርጫ ቦርድ በኩል የተቃወመውን የአንድነትና መኢአድ ውህደት የሚያቋርጥ ውሳኔ በችኮላ ማስወሰናቸው ግራ መጋባት ፈጠረ
* 24 ኢትዮጵአውያን ስደተኞች ሰሞኑን ደቡብ አፍሪካ ውስጥ በህገ ወጥ መንገድ ገባችሁ ተብለው ተያዙ
* ከደ/ሱዳን ወደ ኢትዮጵያ የሚገቡ ስደተኞች የጉበት በሽታ ለኢትዮጵያውያን እያስተላለፉ መሆኑ ተገለጸ
* ኢትዮጵያዊው የድህረ ገጽ ባለቤት በሕወሓት አገዛዝ ላይ የ120 ሚሊዮን ዶላር ክስ ከፈተ
ሌሎችም ዜናዎች አሉ
-- Ze-Habesha

No comments:

Post a Comment