Friday, September 26, 2014

የመቐለ ታሳሪዎች ስም ዝርዝር….!

http://satenaw.com/

  • 739
     
    Share
የፍትህ ያለ?
justiceባለፈው ሓሙስ 08 / 01 / 2007 ዓ ም በሓወልቲ ክፍለ ከተማ በየነባር ይዞታ ማፅደቅና ያለ ማፅደቅ ምክንያት በተፈጠረ ኣለ መግባባት 20 ሰዎች ተደብድበው መታሰራቸው ገልጬ ነበረ።
እንዲታሰሩ ያዘዘውም የክፍለ ከተማዋ ኣስተዳዳሪ ኣቶ በርሀ ፀጋይ መሆኑን ጠቅሼ ነበር።
በወቅቱ ከታሰውሩ ኑዋሪዎች
፩) ለኣከ ገብረሂወት
፩) ሃለቃ ሙሉ ገብረሰላሴ
፫) ኣቶ በርሀ ፋንቱ የ80 ዓመት ኣዛውንት
፬) ቐሺ ፍቕረ ሓዱሽ
፭) ሃለቃ ጠዓመ በርሀ
፮) ገብረ ታደሰ
፯) ወይዘሮ ለተኪሮስ ወልዱ
፰) መልኣኩ ፀጋይ
፱) ገብረሂወት ኣፅበሃ
፲) መሓሪ ተጠምቀ
፲፩) ወይዘሮ ፅርሃ ካሕሳይ
፲፪) ወይዘሮ ተክለኪሮፕስ ገብረሚካኤል
፲፫) ወይዘሮ መድሂን ሲሆኑ የማሳሰርያ ምክንያት የነባር ይዞታ የማፅደቅ መብት እያላቸው ኣስተዳዳሪዎች ሲከለክሉዋቸው የይገባናል ጥያቄ በማቅረባቸው ነው። ለዚህ ተቃውሟቸው በስብሰባው በመግለፃቸውና ኣብየቱታ ወደላይ ኣካላት( እስከ ፌደራል ደረጃ እናቀርባለን ) በማለታቸው ነው።
ሃለቃ ሙሉ ገብረስላሴ የተባለው የቀጠና 8 ሊቀ መንበር የህዝቡ የይገባኛል ጥያቄ ደግፈሃል ብለው በስብሰባው ኣውርደው እንዲያውም ኣንተ ነህ ያነሳሳሃቸው ተብሎ ታስረዋል።
የሞሞና ቀበሌ ኣስተዳዳሪ ኣቶ ግደይ ረዳም የህዝቡ ጥያቄ ደግፈሃል ተብሎ ከሃላፊነቱ በማውረድ ለብቻው በፖሊስ እንዲታሰር ኣድርገዋል።
ይህ የዓፈና ተግባር የህወሓት ካድሬዎች ከህዝቡ መሬቱ እየነጠቁ በሊዝ ስም የሚቸበችቡበት የተለመደ ሱስ ሲሆን ተቃውሞኣቸው ለገለፁ ተበዳዮች በጎ ምላሽ ከመስጠት ይልቅ ዱላና እስርቤት ቀንታቸዋል።
ህዝቡ በህወሓት መንግስት ተማረዋል። ኣንገት ላንገት ተናንቆ እየተፋለማቸው ይገኛል።
ድል ልጭቁን ህዝባችን….!

No comments:

Post a Comment