Thursday, September 25, 2014

የ‹‹ፍትህ አካላት›› ስብሰባ በአቶ በረከት ማስጠንቀቂያ ተጠናቀቀ


  • 703
     
    Share
ነገረ ኢትዮጵያ 
• ‹‹ የተባላችሁትን መስራት አለባችሁ፣ ግዴታችሁም ነው›› አቶ በረከት
• ‹‹በቀጭን ትዕዛዝ ነው የምንሰራው፣ የተጻፈ ህግ አይሰራም›› ዳኞች

አቶ በረከት
አቶ በረከት
ከሁለት ሳምንት በፊት በአቶ በረከት ስምኦን የተከፈተውና 15 ቀን የፈጀው ባህርዳር ላይ የተደረገው የ‹‹ፍትህ አካላት›› ስብሰባ ትናንት መስከረም 14/2007 ዓ.ም በአቶ በረከት ስምኦን ማስጠንቀቂያ መጠናቀቁን የነገረ ኢትዮጵያ ምንጮች ገለጹ፡፡
ስብሰባውን የዘጉት አቶ በረከት ስምኦን ‹‹ፖሊስ፣ አቀቤ ህግና ዳኛ ከአስፈጻሚው (ከካቢኔው) ጋር ተስማምቶና እጅና ጓንት ሆኖ መስራ አለበት፡፡ ይህ ነው ልማታዊ የፍትህ ስርዓት፡፡›› ማለታቸውን ምንጮች ገልጸዋል፡፡
በተቃራኒው ተሰብሳቢዎቹ ‹‹ከአስፈጻሚው አካል ጋር እጅና ጓንት ሆናችሁ ስሩ ማለት የፖለቲካ ጣልቃ ገብነት እንዲኖር መፍቀድ ነው፣ ሊሰበስበን ይገባ የነበረው የካቢኔ አካል ሳይሆን የራሳችን ተቋም የሆነው ከፍተኛ ፍርድ ቤት ነው፣ ስልጠናው በራሱ የዳኝነት ስርዓቱን፣ ተቋሙንና ግለሰባዊ መብታችንን የጣሰ ነው፡፡›› ሲሉ ቅሬታቸውን እንደገለጹ ታውቋል፡፡ በአንጻሩ አቶ በረከት ‹‹አሜሪካን ጨምሮ በየትኛውም አገር የፍትህ ስርዓት አስፈጻሚ አካሉ ጣልቃ ይገባል፣ ይህ የምታነሱት ሀሳብ አደናቃፊ ሀሳብ ነው፣ የተባላችሁትን መስራት አለባችሁ፣ ግዴታችሁም ነው›› ማለታቸውን ምንጮቹ ገልጸዋል፡፡
በስብሰባው ላይ የተገኙት ዳኞችም ‹‹በቀጭን ትዕዛዝ ነው የምንሰራው፣ አድር የተባለውን ማድረግ ነው፣ የተጻፈው ህግ አይሰራም›› በሚል የወረደላቸውን ትዕዛዝ እንደሚያስፈጽሙ ጠቁመዋል፡፡ በስብሰባው የተገኙት ሰብሳቢ ዳኛ (የተቋም ባለቤት)ና የስራ ሂደት አስተባባሪ በስብሰባው ላልተገኙት ባልደረቦቻቸው ከእነ አቶ በረከት በወረደላቸውን ትዕዛዝ መሰረት ‹‹አቅጣጫ ይሰጣሉ››ም ተብሏል፡፡
-- Ze-Habesha 

No comments:

Post a Comment