Tuesday, June 17, 2014

(ሰበር ዜና) ከ1000 በላይ የሚሆኑ ዜጎች ቤታችን ፈረሰ በሚል ኢሰመኩ ደጃፍ ተቃውሞ ወጡ


  • 1504
     
    Share
(ዘ-ሐበሻ) በአሁኑ ሰዓት በአዲስ አበባ የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብት ኮሚሽን መስሪያ ቤት ደጃፍ ከ1000 በላይ የሚሆኑ ዜጎች ቤታችን ፈረሰ፣ የምንሄደበት አጣን በሚል ለተቃውሞ መውጣታቸውን የዘ-ሐበሻ ዘጋቢዎች በፎቶ ግራፍ አስደግፈው ዘገቡ።
ከ1000 በላይ የሚሆኑት እነዚሁ ተሰላፊዎች መንግስት አንድ መፍትሄ እንዲሰጣቸው ለመጠየቅ በኢሰመኮ ደጃፍ ላይ በመስፈር መፍትሄ ካላገኘን አንነቃነቅም እንዳሉ ነው። አካባቢውን ፌደራል ፖሊስ ከቦታል ሕዝቡ ግን ካለምንም ፍራቻ ተቀምጦ መብቱን እየጠየቅ እንደሚገኝ የዘ-ሐበሻ ዘጋቢዎች አስታውቀዋል።
ፎቶዎችን ተመልከቱ፤ ተጨማሪ መረጃዎች እንደደረሱን እንመለሳለን። ዘ-ሐበሻ የትኩስ መረጃ ምንጭ።

self addis 1
self addis 2
self 3

No comments:

Post a Comment