Friday, August 15, 2014

የዝክረ መለስ 2ኛ የሙት ዓመት አከባበርን ምክንያት በማድረግ በአዲስ አበባ በነበረው የፓናል ውይይት የመንግስትን ስራተኛው ለግማሽ ቀን ስራ ሳይሰራ መዋሉን ዘጋያችን ገልጿል።


ለዝክረ መለስ በሚል የአዲስ አበባ መስተዳድር ሰራተኞች ስራቸውን አቋርጠው ውይይቱን እንዲሳተፉ ታዘዙ
በተለያዩ ቦታዎች የተዘጋጁትን የፓናል ውይይቶች የመስተዳድሩ የአመራር አባል አቶ ፋቃዱ ወ/አረጋይ፣ የአዲስ አበባ ሴቶችና ወጣቶች ቢሮ ኃላፊና የምክትል ቢሮ ኃላፊ በተናጠል መርተዋል።
የወጣቶች መድረክ በሃገር ፍቅር አዳራሽ፣ የሴቶች መድረክ በአዲስ አበባ ማዘጋጃ ቤት የባህል አዳራሽ እንዲሁም የልዩ ልዩ አካላት መድረክ በስድስት ኪሎ በሚገኘው የባህል ማዕከል የፓናል ውይይት ተካሂዷል።
በሶስቱም ውይይቶች ለተሳታፊዎች የሃሳብና የጥያቄ ማቅረቢያ ሰዓት በተጊቢው መንገድ ያላተሰጠ ሲሆን ሁሉም የመድረኩ ተናጋሪዎች አቶ መለስ ዜናዊን በማወደስ ላይ ትኩረት አድርገው ነበር።
በመድረኩ ላይ አቶ መለስ ዜናዊ አዋቂ መሪ፣ የሰብዓዊ መብት ታጋይ፤ የአፍሪካ መሪ ፤ የመልካም አስተዳደር ችግርን የፈታ መሪ፤ የአለም መሪ፤ አለማቀፋዊ ደረጃ ያለው ጭንቅላት ባለቤት ፣ ተዝቆ የማያልክ የእውቀት ምንጭ እንደነበር ተወስቷል።
የመለስ ሌጋሲን ብቻ እየመነዘሩ መሄድ እንደሚገባ የተነገረ ሲሆን መለስ በመሪነት ዘመኑ በተለያየ ጊዜ ያደረጋቸውን ቃለ መጠይቆች ማንበብ እንደሚገባ ለሰራተኛው ተነግሯል።
መለስ "ድህነትን ያስወገደ ፤የሃገርና የትውልድ ችግር የቀረፈ ፤የመልካም አስተዳደር ችግርን ገና ተማሪ እያለ ጀምሮ የሚያውቅ ፤የውጪ ጉዳይ ፖሊሲው በሰላምና በድህነት ላይ ብቻ እንዲመሰረት ያደረገ ፤የኢትዮጵያን ሉዓላዊነት ያስከበረ ፤በአፍሪካ መሪዎችና በዓለም መሪዎች ስብሰባ ላይ ተጽእኖ ሲፈጥር የነበረ ፤በእውቀትና በንባብ ላይ የተመሰረተ ትንታኔ የሚሰጥ ፣የህዳሴ ግድብን መሰረት የጣለ ታሪካዊ መሪ" መሆኑን በማወቅ ፣ ማንኛውም ዜጋ የእሱን ሌጋሲ ማስቀጠል እንዳለበት በመድረኩ ላይ ተወስቷል። የመለስ ሌጋሲ የአፍሪካም ሌጋሲ እንደሆነም ተገልጿል።
በማዘጋጃ ቤት በነበረው የሴቶች መድረክ ከተሳታፊ ሴቶች ምንም ጥያቄ ሳይነሳ ውይይቱ ያለቀ ሲሆን ፣ መድረክ ላይ ስታወያይ የነበረችሁ የአዲስ አበባ ከተማ ሴቶች ወጣቶችና ህፃናት ቢሮ ኃላፊ በመድረኩ ላይ ማይክራፎኑን ተቀብላ ማልቀሷን ዘጋቢያችን ገልጻለች።
በሀገር ፍቅር በነበረው መድረክ ደግሞ ስለመለስ ብዙ ገለጻዎች ከተሰጡ በሁዋላ፣ ተሳታፊው አስተያየት እንዲሰጥበት እድል ሲቀርብ ፣ አንድ ተሳታፊ " ስለ መለስ ብዙ ተብሏል ፣ ነገር ግን በአዲስ አበባ ብዙ ቁጥር ያላቸው ዜጎች ዳቦ መብላት አልቻሉም፤የኑሮ ውድነቱ ሰማይ ነክቷል፣ እናንተ ድህነት ጠፍቷል ትላላችሁ.." እያለ መናገር ሲጀምር፣ መድረክ ላይ ያሉ ሰዎች አስቁመውታል።
ጠያቂው ያነሳውን ጥያቄ ለመደገፍና ንግግሩ እንዲቋረጥ መደረጉን ለመቃወም በሚመስል መልኩ አዳራሹ በጭብጫ የተናጋ ሲሆን ፣ የመድረኩ መሪዎች " እንዲህ አይነት ጥያቄዎች በሌላ የመልካም አስተዳደር መድረኮች የሚመለሱ በመሆናቸውና የዛሬው ውይይት በዝክረ መለስ ላይ ብቻ ማተኮር እንደለበት በማሳሰባቸው ከድጋፍ ማብራሪያ ውጪ ሌላ የተቃውሞ ሃሳብ ሳይነሳ መቅረቱን በውይይቱ የተሳተፈው ዘጋቢያችን ገልጿል።
አወያዩ አቶ ፋቃዱ ወ/ገብርኤል " አንድ በሽተኛ የሬዲዮ እና ቴሌቪዥ ጣቢያ አለ፣ ኢትዮጵያን በመንግስታዊ ድርጅቶች እንድትጥለቀለቅ አድርጌ በእርዳታ ሃገሪቱን እመራታለሁ ብሎ የሚያስብ ብለው የተናገሩ ሲሆን፣ የጣቢያውን ስም ከመግለጽ ተቆጥበዋል። ንግግራቸውን በመቀጠልም " መንግስት ስለልማት ይለፈልፋል! መብራት ግን ይጠፋል፤መንግስት ስለልማት ይለፈልፋል! ውሃ ግን ይጠፋል፤ መንግስት ስለልማት ይለፈልፋል! ትራንስፖርት ግን ይጠፋል" በማለት ህዝቡ እንደሚናገር ገልጸው፣ ይህ አስተሳሰብ እንደማይጠቅም፣ የያዝነውን ልማት በአግባቡ ይዘን ለሌላውን ጠንክረን መስራት ብቻ ነው የሚያዋጣን ብለዋል።
በ3ቱም መድረኮች ተሳታፊ የነበሩት በአዲስ አበባ መስተዳድር ስር የሚገኙ ከወረዳና ክ/ከተማ በላይ ያሉ የሁሉም ቢሮዎችና ተቋማት ሰራተኞች ናቸው፡፡
ኢሳት ዝክረ መለስ በአል አከባበር ዝርዝር መመሪያው የደረሰው ሲሆን፣ ከመመሪያው ለመረዳት እንደሚቻለው መለስና ልማታዊ ዲሞክራሲያዊ መንግስት፣ መለስና የህዳሴው ግድብ፣ መለስና የድህነት ጥላቻ፣ መለስና ብህሃነትን በብቃት ማስተናገድ፣ መለስና የረቀቀ የዲፕሎማሲ ትግል በሚሉ ርእሶች ዙሪያ በመላው አገሪቱ ውይይቶች ይካሄዳሉ፡፤ ከዚህ በተጨማሪ መለስ በራሱ ንግግር በተመረጡ ጉዳዮች ላይ ያደረጋቸው ንግግሮች በሚዲያ እንዲቀርቡ እንዲደረግ በመመሪያው ላይ ተቀምጧል።
በሌላ ዜና ደግሞ በአዲስ አበባ ሚሊኒየም አዳራሽ በጠ/ሚ/ር ኃይለማርያም ደሳለኝ የሚመራ 2ኛው ሃገራዊ የመልካም አስተዳደር ውይይት እየተካሄደ ነው። የከፍተኛ ት/ት ተቋማት አመራሮች፤የክልል መስተዳድሮች፣ የቢሮ ኃላፊዎችና ሚኒስትሮች ስብሰባ እያካሄዱ መሆኑ ታውቋል።
አቶ አዲሱ ለገሰ ኢህአዴግ በገጠመው የአመራር ችግር የተነሳ የትራንስፎርሜሸንኑን እቅድ ለማሳካት አለመቻሉን መግለጻቸው ይታወቃል።ኢህአዴግ ከፍተኛ አመራሮች እያደረጉት በሚገኘው ስብሰባ የአመራር ችግሩ ዋናው የመመያያ አጀንዳ ይሆናል ተብሎ ይጠበቃል።ለዝክረ መለስ በሚል የአዲስ አበባ መስተዳድር ሰራተኞች ስራቸውን አቋርጠው ውይይቱን እንዲሳተፉ ታዘዙ
የዝክረ መለስ 2ኛ የሙት ዓመት አከባበርን ምክንያት በማድረግ በአዲስ አበባ በነበረው የፓናል ውይይት የመንግስትን ስራተኛው ለግማሽ ቀን ስራ ሳይሰራ መዋሉን ዘጋያችን ገልጿል።
በተለያዩ ቦታዎች የተዘጋጁትን የፓናል ውይይቶች የመስተዳድሩ የአመራር አባል አቶ ፋቃዱ ወ/አረጋይ፣ የአዲስ አበባ ሴቶችና ወጣቶች ቢሮ ኃላፊና የምክትል ቢሮ ኃላፊ በተናጠል መርተዋል።
የወጣቶች መድረክ በሃገር ፍቅር አዳራሽ፣ የሴቶች መድረክ በአዲስ አበባ ማዘጋጃ ቤት የባህል አዳራሽ እንዲሁም የልዩ ልዩ አካላት መድረክ በስድስት ኪሎ በሚገኘው የባህል ማዕከል የፓናል ውይይት ተካሂዷል።
በሶስቱም ውይይቶች ለተሳታፊዎች የሃሳብና የጥያቄ ማቅረቢያ ሰዓት በተጊቢው መንገድ ያላተሰጠ ሲሆን ሁሉም የመድረኩ ተናጋሪዎች አቶ መለስ ዜናዊን በማወደስ ላይ ትኩረት አድርገው ነበር።
በመድረኩ ላይ አቶ መለስ ዜናዊ አዋቂ መሪ፣ የሰብዓዊ መብት ታጋይ፤ የአፍሪካ መሪ ፤ የመልካም አስተዳደር ችግርን የፈታ መሪ፤ የአለም መሪ፤ አለማቀፋዊ ደረጃ ያለው ጭንቅላት ባለቤት ፣ ተዝቆ የማያልክ የእውቀት ምንጭ እንደነበር ተወስቷል።
የመለስ ሌጋሲን ብቻ እየመነዘሩ መሄድ እንደሚገባ የተነገረ ሲሆን መለስ በመሪነት ዘመኑ በተለያየ ጊዜ ያደረጋቸውን ቃለ መጠይቆች ማንበብ እንደሚገባ ለሰራተኛው ተነግሯል።
መለስ "ድህነትን ያስወገደ ፤የሃገርና የትውልድ ችግር የቀረፈ ፤የመልካም አስተዳደር ችግርን ገና ተማሪ እያለ ጀምሮ የሚያውቅ ፤የውጪ ጉዳይ ፖሊሲው በሰላምና በድህነት ላይ ብቻ እንዲመሰረት ያደረገ ፤የኢትዮጵያን ሉዓላዊነት ያስከበረ ፤በአፍሪካ መሪዎችና በዓለም መሪዎች ስብሰባ ላይ ተጽእኖ ሲፈጥር የነበረ ፤በእውቀትና በንባብ ላይ የተመሰረተ ትንታኔ የሚሰጥ ፣የህዳሴ ግድብን መሰረት የጣለ ታሪካዊ መሪ" መሆኑን በማወቅ ፣ ማንኛውም ዜጋ የእሱን ሌጋሲ ማስቀጠል እንዳለበት በመድረኩ ላይ ተወስቷል። የመለስ ሌጋሲ የአፍሪካም ሌጋሲ እንደሆነም ተገልጿል።
በማዘጋጃ ቤት በነበረው የሴቶች መድረክ ከተሳታፊ ሴቶች ምንም ጥያቄ ሳይነሳ ውይይቱ ያለቀ ሲሆን ፣ መድረክ ላይ ስታወያይ የነበረችሁ የአዲስ አበባ ከተማ ሴቶች ወጣቶችና ህፃናት ቢሮ ኃላፊ በመድረኩ ላይ ማይክራፎኑን ተቀብላ ማልቀሷን ዘጋቢያችን ገልጻለች።
በሀገር ፍቅር በነበረው መድረክ ደግሞ ስለመለስ ብዙ ገለጻዎች ከተሰጡ በሁዋላ፣ ተሳታፊው አስተያየት እንዲሰጥበት እድል ሲቀርብ ፣ አንድ ተሳታፊ " ስለ መለስ ብዙ ተብሏል ፣ ነገር ግን በአዲስ አበባ ብዙ ቁጥር ያላቸው ዜጎች ዳቦ መብላት አልቻሉም፤የኑሮ ውድነቱ ሰማይ ነክቷል፣ እናንተ ድህነት ጠፍቷል ትላላችሁ.." እያለ መናገር ሲጀምር፣ መድረክ ላይ ያሉ ሰዎች አስቁመውታል።
ጠያቂው ያነሳውን ጥያቄ ለመደገፍና ንግግሩ እንዲቋረጥ መደረጉን ለመቃወም በሚመስል መልኩ አዳራሹ በጭብጫ የተናጋ ሲሆን ፣ የመድረኩ መሪዎች " እንዲህ አይነት ጥያቄዎች በሌላ የመልካም አስተዳደር መድረኮች የሚመለሱ በመሆናቸውና የዛሬው ውይይት በዝክረ መለስ ላይ ብቻ ማተኮር እንደለበት በማሳሰባቸው ከድጋፍ ማብራሪያ ውጪ ሌላ የተቃውሞ ሃሳብ ሳይነሳ መቅረቱን በውይይቱ የተሳተፈው ዘጋቢያችን ገልጿል።
አወያዩ አቶ ፋቃዱ ወ/ገብርኤል " አንድ በሽተኛ የሬዲዮ እና ቴሌቪዥ ጣቢያ አለ፣ ኢትዮጵያን በመንግስታዊ ድርጅቶች እንድትጥለቀለቅ አድርጌ በእርዳታ ሃገሪቱን እመራታለሁ ብሎ የሚያስብ ብለው የተናገሩ ሲሆን፣ የጣቢያውን ስም ከመግለጽ ተቆጥበዋል። ንግግራቸውን በመቀጠልም " መንግስት ስለልማት ይለፈልፋል! መብራት ግን ይጠፋል፤መንግስት ስለልማት ይለፈልፋል! ውሃ ግን ይጠፋል፤ መንግስት ስለልማት ይለፈልፋል! ትራንስፖርት ግን ይጠፋል" በማለት ህዝቡ እንደሚናገር ገልጸው፣ ይህ አስተሳሰብ እንደማይጠቅም፣ የያዝነውን ልማት በአግባቡ ይዘን ለሌላውን ጠንክረን መስራት ብቻ ነው የሚያዋጣን ብለዋል።
በ3ቱም መድረኮች ተሳታፊ የነበሩት በአዲስ አበባ መስተዳድር ስር የሚገኙ ከወረዳና ክ/ከተማ በላይ ያሉ የሁሉም ቢሮዎችና ተቋማት ሰራተኞች ናቸው፡፡
ኢሳት ዝክረ መለስ በአል አከባበር ዝርዝር መመሪያው የደረሰው ሲሆን፣ ከመመሪያው ለመረዳት እንደሚቻለው መለስና ልማታዊ ዲሞክራሲያዊ መንግስት፣ መለስና የህዳሴው ግድብ፣ መለስና የድህነት ጥላቻ፣ መለስና ብህሃነትን በብቃት ማስተናገድ፣ መለስና የረቀቀ የዲፕሎማሲ ትግል በሚሉ ርእሶች ዙሪያ በመላው አገሪቱ ውይይቶች ይካሄዳሉ፡፤ ከዚህ በተጨማሪ መለስ በራሱ ንግግር በተመረጡ ጉዳዮች ላይ ያደረጋቸው ንግግሮች በሚዲያ እንዲቀርቡ እንዲደረግ በመመሪያው ላይ ተቀምጧል።
በሌላ ዜና ደግሞ በአዲስ አበባ ሚሊኒየም አዳራሽ በጠ/ሚ/ር ኃይለማርያም ደሳለኝ የሚመራ 2ኛው ሃገራዊ የመልካም አስተዳደር ውይይት እየተካሄደ ነው። የከፍተኛ ት/ት ተቋማት አመራሮች፤የክልል መስተዳድሮች፣ የቢሮ ኃላፊዎችና ሚኒስትሮች ስብሰባ እያካሄዱ መሆኑ ታውቋል።
አቶ አዲሱ ለገሰ ኢህአዴግ በገጠመው የአመራር ችግር የተነሳ የትራንስፎርሜሸንኑን እቅድ ለማሳካት አለመቻሉን መግለጻቸው ይታወቃል።ኢህአዴግ ከፍተኛ አመራሮች እያደረጉት በሚገኘው ስብሰባ የአመራር ችግሩ ዋናው የመመያያ አጀንዳ ይሆናል ተብሎ ይጠበቃል።

No comments:

Post a Comment