Monday, March 3, 2014

አንድነት ፓርቲ የአድዋ በዓልን በአዳማ-ናዝሬት አከበረ አዲሱ ጽ/ቤትም ተዋውቋል


March 3, 2014 8:05 am
  • digg
  • 45
     
    Share
በየወሩ የውይይት እና የስነጥበብ ዝግጅት ለአዳማ ነዋሪ ለማዘጋጀት ታቅዷል
14503_674175845958128_994809339_n1496665_674175672624812_1285987063_n
1897752_674176455958067_2007401352_n1969156_674175975958115_522142282_n1969173_674175899291456_133761572_n1975062_674175745958138_1460244598_n1979585_674176709291375_2033597934_n1690549_674175795958133_253429363_n

የአንድነት ፓርቲ ትላንት የካቲት 23, 2006 ዓ.ም በመሃል ቀጠና ዞን በአዳማ-ናዝሬት የአድዋ በዓልን አከበረ፡፡ በዕለቱ የአንድነት ፓርቲ የአዳማ-ናዝሬት ጽ/ቤትም ለአባላት መተዋወቁን የፓርቲው የአዳማ ከተማ ሰብሳቢ አቶ ምርቱ ጉታ እንዲሁም የህዝብ ግንኙነት ኃላፊው አቶ ተስፋዬ ዋቅቶላ ለፍኖተ ነፃነት ገልፀዋል ፡፡
የአዳማ ከተማ የአንድነት ፓርቲ ሰብሳቢ አቶ ምርቱ ጉታ እንደገለፀው በከተማው ያሉ አዳዲስና ነባር የአንድነት ፓርቲ አባላት በተገኙበት በተከበረው የአደዋ በዓል ላይ የተለያዩ ግጥሞች የቀረቡ ሲሆን በአድዋ ድል ዙሪያ ሰፊ ውይይት ተደርጓል፡፡
የአዳማ ከተማ የአንድነት ፓርቲ የህዝብ ግንኙነት ኃላፊ አቶ ተስፋዬ ዋቅቶላ ጨምሮ እንደገለፀው የአድዋ በዓል በትላንትናው ዕለት ከ10 እስከ 12፡30 ሲከበር ታዋቂው አርቲስት አቶ መስፍን ገብሬ እንዲሁም ከአዳማ ዩኒቨርሲቲ የተለያዩ የትምህርት ክፍሎች ውስጥ የሚማሩ ተማሪዎች ተገኝተዋል፡፡ ከበዓሉ አከባበር አስቀድሞ ከ8 እስከ 10 ሰዓት በከተማው ያሉ አዳዲስና ነባር የአንድነት ፓርቲ አባላት አዲሱን ቀበሌ 11 ከሃኒ ኬክ ቤት በስተቀኝ ቁጥር 4 ት/ቤት ፊት ለፊት የሚገኘውን የፓርቲውን ጽ/ቤት እንዲጎበኙ መደረጉንና በአዳማ በሚደረጉ ፖለቲካዊ እንቅስቃሴዎች ዙሪያ ሰፊ ውይይትም መደረጉን ጨምረው ገልፀዋል፡፡ የህዝብ ግንኙነት ኃላፊው አቶ ተስፋዬ ዋቅቶላ አክሎም በየወሩ የውይይት እና የስነጥበብ ዝግጅት ለአዳማ ነዋሪ ለማዘጋጀት መታቀዱንም አስታውቀዋል፡፡
- See more at: http://www.fnotenetsanet.com/?p=6378#sthash.E3csrWxm.dpuf

No comments:

Post a Comment