Thursday, March 13, 2014

“የኦነግ ጭፍጨፋ ተብለው ከሚጠቀሱ ትራጄዲዎች መካከል አብዛኛዎቹ በኦነግ የተፈጸሙ አልነበሩም” – ከአፈንዲ ሙተቂ

ከአፈንዲ ሙተቂ


“ዳውድ ኢብሳ ሲሞት ጥሩኝ” በሚል ርዕስ በለጠፍኩት አነስተኛ ሐተታ ላይ ሁለት ዓይነት ተቃውሞዎች ቀርበውብኛል፡፡ አንደኛው “ኦነግ በአማራው ላይ የሰራውን ሴራ እና ሸፍጥ እያወቅክ ጥብቅና ቆመህለታል” የሚለው ሲሆን ሁለተኛው “የኦፒዲኦን ድርጅታዊ ህልውና አንኳሰስክ፤ አቶ አለማየሁንም ረገጥክ” የሚል ነው፡፡ ስለ ኦፒዲኦ የጻፍኩት አዲስ ነገር አይደለም፡፡ የድርጅቱ አባላት እራሳቸው በየአጋጣሚው የሚናገሩትን ነው በፌስቡክ የደገምኩት፡፡ በተለይ ደግሞ አባላቱ ከስራቸው ሲባረሩ፣ ወይ ደግሞ ከድርጅቱ ከድተው ወደ ውጪ ሀገር ሲኮበልሉ “ኦፒዲኦ የኦሮሞን ህዝብ ለማጭበርበር ሆን ተብሎ የተፈጠረ ድርጅት ነው” የሚል ጩኸት በማሰማት ነው የሚታወቁት፡፡ እነ ዮናታን ዲቢሳ፣ ዱባለ ጃሌ፣ ኢብራሂም መልካ ሲያደርጉት የነበረው ይህንኑ ነው፡፡ ነገር ግን እኔ የነርሱን ፈለግ በመከተል አይደለም እንዲያ ብዬ የጻፍኩት፡፡ ከነርሱ በፊትም እንደዚያ ስል ነበር፡፡
——
ኦነግን ለመጀመሪያ ጊዜ ካየሁበት ግንቦት 1983 ጀምሮ የድርጅቱን የፖለቲካ መስመር ስደግፍ ቆይቻለሁ፡፡ ዩኒቨርሲቲ ስገባ ግን ድርጅቱ በሚያራምደው ርዕዮተ ዓለምና በፖለቲካ ፕሮግራሙ ላይ ጥያቄዎች ማንሳት ጀመርኩ፡፡ በዋነኛነትም “የመገንጠል ፖለቲካው የኦሮሞን ጥያቄ የትም አያደርሰውም” የሚል ሀሳብ አነሳሁ፡፡ እንዲሁም የሚከተላቸው ስትራቴጂዎቹ ፍጹም ሊዋጡልኝ አልቻሉም፡፡ በዚህም ከኦሮሞ ወንድሞቼ ጋር ብዙ ጊዜ እነታረክ ነበር፡፡ በተለይም በዚያ ጊዜ ኦነግን መተቸት Taboo ተደርጎ ይቆጠር ስለነበር ከቅርብ ጓደኞቼ ጭምር እስከመጣላት ደርሰናል፡፡ እናም ከ1990 ጀምሮ የድርጅቱ ተቃራኒ እንጂ ደጋፊ አይደለሁም፡፡
እንዲህ በመሆኑ ግን ድርጅቱን በሐሰት መክሰስ ያለብኝ አይመስለኝም፡፡ ድርጅቱን በሰራው ጥፋት ብወቅሰው ማለፊያ ነው፡፡ ባልሰራው ወንጀል መክሰስ ግን ለማንም የሚበጅ አይሆንም፡፡ እንደምሳሌም ኦነግ የሚከሰስባቸውን ጭፍጨፋዎች እንመልከት፡፡ በደኖ፣ አርባ ጉጉ፣ ወተር፣ አረካ፣ አሰቦት ገዳም ወዘተ…
እነዚህ ጭፍጨፋዎች መከሰታቸው ሁላችንንም ያሳዝነናል፡፡ አንድ ቀን እውነቱን ፈልፍለን የማውጣት ግዴታም ተጥሎብናል፡፡፡ ነገር ግን በርካታ ሰዎች በሁሉም ጭፍጨፋዎች ኦነግን ተጠያቂ ሲያደርጉ በጣም እገረማለሁ፡፡ በተለይም ዛሬ በህትመት ላይ የሌሉ ሁለት የግል ጋዜጦች ይህንን ፕሮፓጋንዳ እየደጋገሙ ሲያስተጋቡት ሳይ “ስለ የትኛው ሀገር ነው የሚያወሩት” እያልኩ እደነቅባቸው ነበር፡፡ እንዲህ የምለው ጋዜጦቹ የመረጃ እጥረት የነበራቸው መሆኑን በማወቄ ብቻ አይደለም፤ የጂኦግራፊ እውቀትም ያጠራቸው ስለሚመስለኝም ጭምር ነው፡፡ ለምሳሌ “አረካ”ን እንውሰድ፡፡ ይህቺ ከተማ የት ነው ያለችው? ኦሮሚያ ውስጥ ነው? ወይስ ሌላ ቦታ?
ይገርማል! አረካ ማለት በደቡብ ክልል በወላይታ አውራጃ ከሶዶ ከተማ በቅርብ ርቀት ላይ ያለች ከተማ ናት፡፡ እኔ እስከማውቀው ድረስ ኦነግ እዚያ ድረስ ሄዶ ሀገር አላስተዳደረም፡፡ “አረካ የኦሮሚያ ግዛት ናት” ብሎ የሚያውቅም አይመስለኝም፡፡ እናም ጂኦግራፊን በትክክል የሚያውቅ ጋዜጠኛ የአረካውን ግጭትና ጭፍጨፋ ለኦነግ አይሰጥም ነበር፡፡ በተጨማሪም የአረካው ግጭት የደረሰው ኦነግ የሽግግር መንግሥቱን ለቆ ከወጣና በእጁ የነበሩት መሬቶች በሙሉ በኢህአዴግ ቁጥጥር ስር ከወደቁ በኋላ ነው፡፡
የአረካው ግጭት በሽግግሩ ዘመን ለነበረው የተወካዮች ምክር ቤት የውይይት አጀንዳ ሆኖ እንደቀረበ ይታወሳል፡፡ በከተማዋ ያለቁት የ31 ሰዎች ግድያ በመከላከያ ሰራዊቱ እንደተፈጸመ መንግሥቱ በይፋ አምኗል፡፡ ዳሩ ግን ለግድያው የተሰጠው ምክንያት በጣም አነጋጋሪ ነበር፡፡ መንግሥት ያቀረበው ምክንያት “ሰልፈኞቹ የተገደሉት ቦንብ በመወርወራቸው ሳቢያ የመከላከያ ሰራዊቱ ራሱን ለመከላከል በወሰደው እርምጃ ነው” የሚል ነው፡፡ ይሁንና ይህንን ምክንያት ብዙዎች አልተቀበሉትም፡፡ ብዙዎች እንደተጠራጠሩት እስከ ዛሬ ድረስ ቆይቷል፡፡ በነገራችን ላይ በአረካ የሞቱት የቀድሞ መንግሥት ወታደሮች ነበሩ፡፡ እነዚያ ወታደሮች “የጡረታ መብታችን ይከበርልን” በማለት የተቃውሞ ሰልፍ በማድረጋቸው ነው ከመከላከያ ሰራዊቱ ጋር የተጋጩት፡፡
——–
በሚያዚያ ወር 1984 በወተር ከተማ በተካሄደ ጭፍጨፋ የሞቱትም በተመሳሳይ መልኩ በመከላከያ ሰራዊቱ እንደተገደሉ የሽግግር መንግሥቱ በወቅቱ አምኗል፡፡ ይሁን እንጂ በወተር የተገደሉት 230 ሰዎች በሙሉ ኦሮሞዎች እንጂ አማራዎች አልነበሩም፡፡ እነዚያ ሰዎች የተገደሉት ኢህአዴግ ከከተማቸው ወጥቶ ኦነግ ወደ ከተማዋ እንዲመለስ በመጠየቃቸው ነው (ወተር ለአንድ ዓመት ያህል በኦነግ ቁጥጥር ስር ነበረች፤ ኦነግ ከከተማዋ ሲወጣ ኢህአዴግ ገብቶባታል፤ ነዋሪዎቹ “እንደ ቀድሞው ጊዜያችን ኦነግ ወደ ከተማዋ ይመለስ” በማለታቸው ነው ከመከላከያ ሰራዊቱ ጋር የተጋጩት)፡፡ ጋዜጦቹ ግን “ኦነግ አማራዎችን ጨፈጨፈ” እያሉ ነበር የሚዘግቡት፡፡
——-
በ1984 (ወሩን አላስታውሰውም) በአሰቦት ገዳም በተካሄደ ግድያ ሰባት መነኮሳት ሞተዋል፡፡ ይህንን ግድያ የፈጸሙትም በወቅቱ የአሰቦት ከተማን ለትንሽ ጊዜ ተቆጣጥሮ የነበረው የኦሮሞ ነጻነት እስላማዊ ግንባር (IFLO) ታጣቂዎች ነበሩ፡፡ ግድያው ስር ሳይሰድ በአፋጣኝ ያስቆሙት ደግሞ ኢህአዴግና ኦነግ ነበሩ፡፡ ሁለቱ ድርጅቶች አንድ ጥምር ኮሚቴ በማቋቋም በወሰኑት ውሳኔ መሰረት IFLO ከከተማው ተባርሮ አካባቢው በኢህአዴግ ቁጥጥር ስር እንዲውል ተደርጓል፡፡
——
በአርባ ጉጉ የተፈጸመው እልቂት በሁለት ተጎራባች መንደሮች መካከል በተካሄደ ግጭት ነበር የተለኮሰው፡፡ እያደር ግን መርቲ ጀጁ እና አሰኮ የሚባሉ የአርባ ጉጉ ወረዳዎችን አዳርሷል፡፡ በግጭቱ የኦሮሞ እና የአማራ ተወላጆች በእኩል ደረጃ ተጎድተዋል፡፡
በአርባ ጉጉ ግጭት የራሳቸውን የፖለቲካ ትርፍ ለማጋበስ የፈለጉ ወገኖች እጃቸውን አስገብተውበታል ይባላል፡፡ በመሆኑም በውጤቱ ከሁሉም ግጭቶች የከፋ ሊሆን ችሏል፡፡ በዚህ ግጭት ከሁለቱም ወገን እስከ ስድስት መቶ ያህል ሰዎች መሞታቸው ይነገራል፡፡ ከመቶ ሺህ ያላነሰ ሰው ወደ ሀረርጌና ሸዋ ክፍለ ሀገሮች ተፈናቅሏል፡፡ ሆኖም ኦነግ በዚህ ግጭት ውስጥ እጁን ማስገባቱን የሚያረጋግጥ ፍንጭ እስከ አሁን ድረስ የለም፡፡ ኦነግ በወቅቱ በአርባ ጉጉ አውራጃ ምንም ይዞታ አልነበረውም፡፡ የመላው አማራ ህዝብ ድርጅትም ቢሆን በግጭቱ የከሰሰው ኦህዴድን (OPDO) እንጂ ኦነግን አልነበረም፡፡ በተለይም እስከ ቅርብ ጊዜ ድረስ የምዕራብ ሸዋ ፖሊስ መምሪያ ሃላፊ የነበረው ኮሎኔል ዲማ ጉርሜሳ ከግጭቱ ጋር ተያይዞ ስሙ በሰፊው ይነሳ እንደነበረ ይታወሳል፡፡ በዚያን ጊዜ የኦሮሚያ ክልል ፕሬዚዳንት የነበሩት አቶ ሐሰን ዓሊ ከእፎይታ መጽሔት ጋር (ግንቦት 1985) ባደረጉት ቃለ-ምልልስ “አቶ ዲማ ጉርሜሳ ንጹሕ ነው” በማለት ከመከላከላቸውም በላይ ለግጭቱ ዋነኛ ተጠያቂ ያደረጉት መአሕድን እንጂ ኦነግን አልነበረም፡፡
የግል ጋዜጦች ግን ነገሩን አራግበው በኦነግ ላይ አላከኩት፡፡ ነገሩን ሳያውቁት ቀርተው የተደረገ አይመስለኝም፡፡ አንዳንድ ጋዜጦች -ተከፍሎአቸው እንዲህ እንደሚያደርጉ በደንብ እናውቃለን፡፡
——–
የበደኖ ጭፍጨፋ! አዎን! ኦነግ ሊጠየቅበት የሚገባው ብቸኛው ትራጄዲ ይህኛው ነው፡፡ በርግጥም እልቂቱ በተፈጸመበት ወቅት በደኖ በኦነግ ቁጥጥር ስር ነበረች፡፡ የሞቱት ሀምሳ ያህል ሰዎች ለምን እንደተገደሉ ባይታወቅም አድራጎቱ በኦነግ ወታደሮች እንደተፈጸመ ድርጅቱ ራሱ አምኗል፡፡ ኦነግ በወቅቱ በወታደሮቹና በአዛዦቹ ላይ እርምጃ ወስጃለሁ ቢልም የተወሰደውን እርምጃ ምንነት አልገለጸም፡፡ በነገራችን ላይ በዚህኛውም እልቂት ከሞቱት መካከል ግማሽ ያህሉ ኦሮሞዎች ነበሩ፡፡
—–
ከላይ በዝርዝር እንዳስረዳሁት የኦነግ ጭፍጨፋ ተብለው ከሚጠቀሱ ትራጄዲዎች መካከል አብዛኛዎቹ በኦነግ የተፈጸሙ አልነበሩም፡፡ ኦነግ ሊጠየቅበት የሚገባው ብቸኛው ድርጊት በበደኖ የተፈጸመው ነው፡፡ የእውነት ቀን ሲመጣ ያንን ፋይል ማውጣታችንም አይቀሬ ነው፡፡ ይሁንና በኦነግ ያልተፈጸመውን ከርሱ ጋር አያይዞ መጻፍ ጥቅሙ ምን እንደሆነ ሊገባኝ አይችልም፡፡ እንዲያውም የያኔዎቹ የግል ጋዜጦች የሚያራግቡት ወሬ በተወሰነ መልኩ የኦነግ ጨካኝነትን ከመግለጽ ይልቅ “ኦሮሞ ጨካኝ ነው” የሚል እድምታ ለመፍጠር የታለመ ነበር የሚመስለው፡፡
እርግጥ የኦነግ ወታደሮች በብዙ አጋጣሚዎች ልዩ ልዩ የጭካኔ ተግባራትን ሲፈጽሙ ተስተውለዋል፡፡ እርሱን አንክድም፡፡ የነርሱ ገፈት ቀማሽ ሆኖ የዘለቀው ግን በአብዛኛው ኦሮሞው ነው እንጂ የሌላ ብሄረሰብ ተወላጅ አልነበረም፡፡ በተለይ አንዳንዶቹ የኦነግ ወታደሮች “ጎበና፤ ቢተምቱ.፤ ወዘተ..” ለሚሏቸው ግለሰቦች ምህረት አልነበራቸውም፡፡ እንዲሁም ተጻራሪ ድርጅት ሊያቋቁሙ ነው በሚል ፍርሃት አባላቶቻቸውን ጭምር እስከ መግደል ይደርሱ ነበር (የኦነግ የሀረር ቢሮ ሃላፊ የነበሩትን አቶ አራርሶ ወዳይን እና በመቻራ ከተማ የተገደለውን የሀረማያ ዩኒቨርሲቲ ምሩቅ ካሊድ ሃጂ ኑራን መጥቀሱ ይበቃል)፡፡ ሆኖም ጋዜጦቻችን ድርጅቱ የፈጸመውን ማውራት ይተውና ድርጅቱ ያልፈጸመውን ወንጀል ይነግሩን ነበር! ላም ባልዋለበት ኩበት ለቀማ ማለት ይህ ነው፡፡
ለማጠቃለል ያህል እኔ ለኦነግ አልተከላከልኩለትም፡፡ አንዳች ጥብቅና አልቆምኩለትም፡፡ የጻፍኩት የማውቀውን ሐቅና የማምንበትን አቋሜን ነው፡፡ ይሁንና ይህ አባባሌ ኦነግን ከመፍራት እንዳይወሰድብኝ አደራ እላለሁ! አስፈላጊ ከሆነ በኦነግም የተፈጸሙ ስህተቶችና ጥፋቶችን አንድ በአንድ መዘርዘር እችላለሁ፡፡
ሰናይ ቀን ይሁንላችሁ!!

ትዝብት – ደርሶ መልስ ዲያስፖራ (አንደኛ)

ነገሩ የሆነው አዋሳ ዩኒቨርሲቲ ነው። ቆነጃጅት ወጣት ሴት ተማሪዎች ከዩኒቨርሲቲው ቅጥር ግቢ ውጭ ባሉ የከተማው ደለላዎች ጋር በመተባበር እጅግ ዘግናኝ ስራ ይሰራሉ። ደላሎቹ የቆነጃጅቶቹን ተማሪዎች ፎቶ የያዘ ትልቅ ካታሎግ ይዘው ከአዲስ አበባም ሆነ ከአቅራቢያው ከተሞች አለዚያም ከዚያው ከአዋሳ ከተማ ብቅ የሚሉ ሃብታም ደንበኞቻቸውን የተማሪ ኮረዶችን ፎቶ በመስጠት ያስመርጣሉ።

ሰውየው ውብ ወጣት ተማሪ ኮረዳ እንደሚፈልግ በሰው በሰው የተገናኘውን ደላላ ይጠይቃል። እናም ከተሰጠው የፎቶ ድርድር ላይ ማመን ያቃተውን የአንዷን ውብ ፎቶ እያሳየ ‘ይህችን ታውቃታለህ?’ ሲል ይጠይቃል። የደላላ መልስ አንድ ነው… ሁሉንም ስለሚያውቃቸው አልተቸገረም ‘አዎ እሷን ይፈልጋሉ?’ ሲል ይጠይቃል። ሰውየውም ‘እባክህ’ ሲል በመማጸን ፈቃደኝነቱን ይገልጻል። ከፊቱ የመጣለትን ገቢ ተደራድሮ ልጅትን ለመጥራት ይሮጣል። ደላላው።
እናም ቆንጅት ተበጃጅታ፣ አምራና ደምቃ ትመጣለች። በቀጥታ ወደ ሰውየው መኪና ስትደርስ ሰውነቷ ይርዳል። በቁጣ አይኑ የተንቀለቀለው ሰውየም ወደ ልጅቷ ያፈጣል… በቀጥታ ተንደርድሮ የልጅቷን ክርን ይይዛል… ደላላው እየሆነ ያለውን ሊረዳ አልቻለም… የልጅቷን እጅ የያዘው ሰው (ደንበኛ) የልጅቷ ወላጅ አባት ኖሯል።
ኢትዮጵያ ደርሶ የሚመጣ የውጭ ሀገር ነዋሪ (ደርሶ መልስ ዲያስፖራ) በተለያየ አይነት እይታ የተለያዩ እውነታዎችን ይዞላችሁ ይመጣል።
አንዳንዱ የህንጻውን ግንባታ አዳንቆ ሲያወራ፤ ሌላው ስለጭፈራ ቤቶች ይዘክራል። ጓደኞቹን በስራ ብዛት ሊያገኝ እንዳልቻለ የሚያወራላችሁ እንደመኖሩ ሁሉ በስራ አጥነት ችግር የተነሳ ዱርየ መበራከቱን የሚተርክላችሁ አታጡም። የቆነጃጅቶችን ውበትና የዳንኪራ ቤቶችን ሁናቴ የሚነግራችሁ፤ በየቡና ቤቱ ብሎም በየትምህርት ቤቱ ያሉ ወጣቶችን ችግር ያስረዳችኋል። የሀገሪቱን እድገት በኮንስትራክሽን መጥለቅለቅ የሚያጫውታችሁ፤ በመንገዱን መቆፋፈር ሰው ስለመማረሩ በማንሳት ያትትላችኋል። አዲስ አበባን በመመስረት ላይ እንዳለች ታላቅ ከተማ አድርጎ የሚተርክም አታጡም።
ይሄ ሁሉ እንደ እድገት በአንዲት መንግስት የሚባል አካል አላት በተባለች ሀገር መታየቱ ምኑ ይገርማል?። አንዳንዴ ሀገሩን አይቶ ዘመድ ወዳጅ ጠይቆ መምጣትም ሆነ ሰው ሀገሩ ደርሶ መመለሱ እጅግ መልካም ነገር ነው። ያየውን ግልብ ነገር ከራሱ አይን ጥግ ስር አንጻር ብቻ ተመልክቶ በሰዎች ላይ የሚደርስን ስቆቃ ሸፋፍኖ ያለጥናት የተሰሩ መንገዶችንና ህንጻዎችን እንደትልቅ ለውጥ ማውራት ግን የሞራል ጥያቄን ያመጣል።
በእርግጥ የውብ ሀገር ነችና ውቦች ሊኖሩ ይችላሉ። መሸታ ቤቶቹም ደማምቀው ሊሆን ይችላል። ህንጻ ግምባታውም ቢጧጧፍ አያስነውርም። መንገዶች ተንጣለው ቢታዮም ጸጸት የሚገባው የለም። ነገር ግን ሰው በቀላሉ ቆሎ ሽጦ ይኖርበት ከነበረ መንደር ተባሮ መግቢያ ያጣበት ሀገር፤ ውሃ ልማት የቆፈረውንና ውሃ ቧንቧ ቀብሮ ያበጀውን መንገድ ነገ ቴሌ የሚያፈርሰው ከሆነ… ከዚያም ማዘጋጃ ቦይ ተደፈነ ብሎ ከተረተረው… ወጣት እንስት ህጻን ታናሽ እህቷንና ወንድሟን ትምህርት ቤት ለመስደድ መንገድ ከወጣች፤ ጥቂት የባለጊዜ ልጆች የሚሰሩት አጥተው በተንፈላሰሱባት ሀገር መለመንን ተጠይፈው ዱሮ የነበራቸውን ጽዱ ልብስ ለብሰው ፊታቸውን የከለሉ ሰዎች በየጥጋጥጉ የሚለምኑባት ሀገር ከሆነች… አባት ትምህርት ቤት ብሎ የላካት ወጣት በኮሌጅ ያለውን ፍላጎቷን ለማሳካት ገበያ መውጣት… ዘግናኝ ነው…
የሚሰራው መንገድ ተሸርሽሮ ከአመት በላይ አገልግሎቱ አልቆለት ተቦርቡሮና ውሃ ቋጥሮ የሚታይበት ሀገር እየገነቡ መሰረት መጣል አይቻልም ነው ጥያቄው። ደረጃቸውን ባልጠበቁና በይድረስ ይድረስ የተሰሩ ህንጻዎች ጋጋታ የከተማንም የሀገርንም እድገት ሊያሳዩ አይችሉም ነው እየተጮኸበት ያለው ነገር። ፍትህ ራሷን ችላ የምትራመድበትን ሀገር የሚመራ መንግስት ይኑር ነው ልፈፋው። የህወሃት ሰዎችና ጥቂት አሸርጋጆች የሚያደርጉት አገራዊ ጥፋት ይቁም። ልጆቻችን እርስበርስ የዚህና የዚያ ብሄር ወይንም ከወዲያ አለዚያም ከወዲህ መንደር የመጡ እየተባባሉ በጥርጣሬ እየተያዩ የሚኖሩበትንና የሚያድጉበትን ሀገር እናፈራርስ ነው እሪታው። የህወሀት አለያም ጥቂት ሽርጉደኞች በገፍ የሚገነቧቸው ህንጻዎች ከሙስና ባሻገር ሆኖ ራሳቸው ኢንጂኒዬርና አርክቴክት ሆነው የሚገነቡት ሀገር ሀገር አይሆንም ነው ጉዳዩ።
22 አካባቢ የተሰራው ጎላጎል ህንጻ ባለጊዜው ባለቤት ህንጻውን ሲያስገነባ ዋናው መንገድ ውስጥ መግባቱን ያየ መሀንዲስ ወይንም ኢንጂኒዬር ‘አግባብ አይደለም፤ ወደፊት መንገድ ይዘጋል’ ብሎ ምክር ቢሰጠው ‘እኔ ያልኩህን አድርግ’ ብሎ ጀርባውን የተማመነው ባለቤት ሲያዘውና ያ ባለሙያ የታዘዘውን በማድረጉ ግንባታው ከተጠናቀቀ በኋለ አሁን መንገዱን የዘጋውን ህንጻ የሚደፍረው ጠፍቶ፤ መረማመጃው ዘግቶ መታየቱ የሚወራው ዝም ብሎ ከመሬት ተነስቶ አይደለም።
አሁንማ የህወሃት ሰዎች እጅግ ከመድፈራቸው የተነሳ አዲስ አበባ ውስጥ በስማቸው ሆኗል ፎቅ የሚያስገነቡት ተክላይ ህንጻ፣ ገብረጻዲቅ ህንጻ… ብሎ ያጫወተኝ ወዳጄ ታዲያ ምን ችግር አለው? ስለው ‘ምንም ችግር የለውም በህዝቡ ውስጥ ግን የማህበራዊ ህይወት መራራቅንና ሃሜትል ያስከትላል ብሎም ህዝቡን እነሱ እና እኛ የሚያስብል የሳይኮሎጅ ጣጣ ውስጥ ከቶታል።” አለኝ
ሀገሪቱን የህወሃት ጄኔራሎችና መኮንኖች ብቻ በሀብት የወረሯት ሀገር ተሸክሞ የት እንደሚደረስ ማሰብ ሰው መሆን ነው። ይህ ወዳጄ ታዲያ በአንጻሩ የሽንኩርትን ገበያ ለማየት ጉሊት ወርዶ ያየውን ጉድ በልኩ አስተውሎ መጥቷል። አንድና ሁለት ራስ ትንንሽ ሽንኩርት አልያም ቲማቲም ለሳምንት ለማብቃቃት የሚሰቃይ ህዝብን ይዞ ጉዞው የት ነው የሚያደርሰን።
የአገሪቱን የዘር ችግር ጥግ ላይ መድረስ ባለፈው 767 አውሮፕላንን ይዞ ጄኔቫ የገባው ወጣት ረዳት አብራሪን በሚመለከት መግለጫ የሰጡት ሬድዋን ሁሴን “ጠላፊው ከየት ነው?’ ተብለው ሲጠየቁ ‘ኢትዮጵያዊ ነው’ ብለው ሲመልሱ አረ ከየትኛው ክልል ተብለው መጠየቃቸው ጉድጓድ ውስጥ የሚከት ቅሌት ነው። መልሳቸውም እረሪሪሪሪሪ የሚያስብል ነበር። ‘ከየትኛው ብሔር እንደሆነ አልታወቀም።’
መጠጥና ዳንኪራ ቤቶች
ከ5 ሚሊየን ህዝብ በላይ (እስከ 8 ሚሊዮን ይገመታል) የሚኖርባት አዲስ አበባ የጭፈራ ቤቶችን ብዛትና የጨፋሪውን አይነት የነገረኝ ወዳጄን ቀኑን ሙሉ ሲተራመስ የሚውለው አዲሳቤ በጊዜ በ12 ሰዓት ከቶ በየፊናው ሲገባ ከተማው ምን ያህል ጭር እንደሚል አላስተዋለም። 100 የማይበልጡ ምሽት ቤቶች (አጋንኘው ነው) 100 ሰው እያንዳንዳቸው ቢያገኙና ቢያስጨፍሩ 10ሺህ ሰው… እንጨምረው እና 50ሺህ ሰው በምሽት ስለጨፈረና ስለደነከረ ሀገር በጥጋብ እንደዘለለ ማውራት ነውር ነው ነው ጨዋታው። ይሄንኑ ግምት እናስላው ከተባለ የገዥው ህወሃት/ኢህአዴግ ባለስልጣናትና ጥቅም ተሻራኪዎች 70 በመቶውን ቢያነሱ 15 በመቶ በዲያስፖራና ዘመዶች እንዲሁም የተቀረው ለፍቶ አዳሪ አለያም ከቤተሰቡ የሚቃርም ሊሆን ይችላል።
ለነገሩማ የዘመነኞቹ ሰዎች ልጆች የሚገቡበት ቡና ቤት ውስጥ ቀድሞ የገባ ሌላ ደንበኛ ሾልኮ እንዲወጣ የሚደረግባት ምድር። በድርድር የታሰረ ብር ለአስተናጋጅ ተሰጥቶ ቆጥረሽ ውሰጅ የሚል ረብጣው ያጨናነቀው የዘመኑን ሰው ማየት የተለመደ መሆኑንም እየሰማን ነው።
ምን እዚህ እኛ በብርድ እየወጣን ሰላማዊ ሰልፍ እያልን እንጮሃለን እነሱ ሚሊየነሮች ሆነዋል ያለኝና ሀገር ቤት ሄዶ በጓደኛው የቀና ሰው ያጫወተኝም አለ። ያ ጓደኛው ከዘመንኛ ሰዎች ጋር ገጥሞ ህዝብ እየቦጠቦጠ መሆኑን የነገረኝ ደርሶ መልስ ዲያስፖራ… አሁንም እዚህ ኖርዝ አሜሪካ ከተመለሰ በኋላ እዚያው አገር ቤት ቢሆን እንደጓደኛው ሚሊየነር ይሆን እንደነበር ሲያወጋኝ በመቆጨት ነበር። ዘመንኞቹና ጓደኛው የሚቦጠቡጠው ህዝብ ስቃይ በሚሊየን ብር ተጋርዶበት። አረ እየተስተዋለ! እዚያኮ ሀገር እየተቆራረሰ ነው! አረ ስለአምላክ! ሀገሪቱም በመንደር እየተተበተበችኮ ነው! ስለእመብርሃን! ምድራችን ፍትህ የጠፋባት ሆናለችኮ! በሽብርተኛ ስም ስንቱ ታጎረ… አረ ስለአላህ! ሰው ኑሮ መረረኝ እያለ ነው እኮ! እንኳን ከአሜሪካ ከመንግስተ ሰማያትም አመጣኻለሁ የሚል ለስራው ብቁ ያልሆነ ሰው የሚሾምበት ሀገር ውስጥ የሚኖር ህዝብ እኮ ነው የያዝነው። ጭራሽ የሶማሌ ክልል ባለስልጣን ይባስ ብሎ ምኒባስ ታክሲ በከተማ እንዳይገባ ብሎ በራሱ ስልጣን አግዶ እገዳውን የጃፓን መንግስት ቢመጣም እንኳን አልቀበልም እያለ እኮ ነው ጎበዝ… ሰሚ የለም እንዴ በግዜር!?
http://ecadforum.com/

በጅጅጋ 300 እስረኞች መንገድ ላይ ተጣሉ

በጅጅጋ እስር ቤት ውስጥ ታስረው ከነበሩ ቁጥራቸው በውል ከማይታወቅ እስረኞች መካከል 300 ያክሉ ከአራት ቀናት በፊት በጅጅጋ መንገድ ላይ መጣላቸው ታውቀ።

የኦጋዴን ነጻ አውጭ ድርጅት ያላከውን መረጃ በመንተራስ ኢሳት ባደረገው ማጣራት፣ ባለፈው ሃሙስ ለአርብ አጥቢያ አካላቸው በምግብ እጦት የከሳ፣ አይናቸው የታወረ፣ እግሮቻቸው ሽባ የሆኑ፣ የአእምሮ መታወክ የደረሰባቸውና አሰቃቂ የእስር ቤት ህይወት እንዳሳለፉ የሚናገሩ እስረኞች በጅጅጋ ጎዳናዎች ላይ ተጥለዋል።
ከተጣሉት መካከል ወላጅ አልባ የሆኑ ምናልባትም በእስር ቤት ውስጥ የተወለዱ ህጻናት፣ ወጣቶችና አዋቂዎች ይገኙበታል።
አብዛኞቹ እስረኞች ከሰውነት ተራ የወጡና በበሽታ የተጠቁ እንዲሁም ለረጅም ጊዜ በእስር ቤት ውስጥ የቆዩ ናቸው። ኢሳት ለማረጋገጥ ባይችልም፣ የኦብነግ መረጃ እንደሚያሳየው ከተፈቱት እስረኞች መካከል 20ዎቹ በሶስት ቀናት ውስጥ በበሽታ ሞተዋል።
ከአንድ ወር በፊት ኢሳት ከጅጅጋ ከተማ 25 ኪሜትር ርቆ በሚገኝ እስር ቤት ውስጥ በኮሌራ በሽታ ከ40 በላይ ሰዎች ሞተው በእስር ቤቱ አካባቢ አግባብ ባልሆነ መንገድ በመቀበራቸው አስከሬናቸውን ጅቦች እያወጡ በመብላታቸውና እና አካባቢው በበሽታ በመበከሉ በድጋሜ እንዲቀበሩ መደረጉን ዘግቧል።
የክልሉ መንግስት አሁን የወሰደው እርምጃ በእስር ቤቶች ውስጥ የተነሳውን የኮሌራ በሽታ ለመከላከል እንደሆነ እየተነገረ ነው።
በሶማሌ ክልል የተካሄደውን የብሄር ብሄረሰቦችን ቀን አስመልክቶ የክልሉን ገጽታ ያበላሻሉ የተባሉ ከ700 በላይ የጎዳና ላይ ተዳዳሪዎችና መታወቂያ የሌላቸው ሰዎች እንዲታሰሩ መደረጉ ይታወቃል።

Wednesday, March 12, 2014

Ethiopia’s stolen 8.4 billion dollars and EPRDF


By Eskinder Nega

The folks at Global Financial Integrity may not know this, but their report on illicit financial flows is threatening to steal the thunder from an important milestone for the EPRDF, Ethiopia’s repressive ruling party, which will be celebrating its 20th year in power on the 28th of this month. And more than a harmless opportunity to gloat is slipping away. GFI’s report poses real danger of generating mistrust between EPRDF’s senior leadership.Commissioned grandly by the UNDP, the development arm of the UN, GFI’s report explores the flow of illicit financial flows from Least Developed Countries (LDSs), of which Ethiopia has been a enduring mainstay. (Many countries, some in Africa, have moved up the ladder of development.)
Covering the 18 years between 1990 and 2008, which are all, but one, 1990, within the realm of EPRDF’s reign, the report includes Ethiopia, one of the world’s most impoverished countries, in the top ten countries from which funds have been transferred illegally in to banks and offshore financial centers in developed countries. The amount: a whooping 8.4 billion US dollars, which places Ethiopia at a shocking 9th place in the world, just below resource rich and gruesomely autocratic Myanmar with 8.5 billion dollars.
The report attributes the bulk, 65 to 70 percent, of Ethiopia’s illicitly transferred funds to trade mispricings. Somewhere in the remaining 30 to 35 percent—up to 3 billion US dollars—are the laundered monies of corrupt government officials, almost all exclusively members of the EPRDF. Clearly, some EPRDF officials are amply prepared for a comfortable exile. And there are of course others who believe in the fairy tale of the party’s invincibility and see no need for a contingency plan. This will most probably be their wakeup call. The haste not to be left behind is now inevitable. The worst for the nation is yet to come. Export figures released by the Ministry of Trade in late February 2011 show coffee still dominating the sector. Of the infinitesimal 1.14 billion US dollars the nation earned in six months from goods sold overseas in 2003(in the Ethiopian calendar), 320 million dollars were attributed to coffee. Guna Trading House PLC, a holding of the Endowment Fund for the Rehabilitation of Tigray, EFFORT, a business empire managed exclusively by senior members of the EPRDF, is an exporter of coffee.
Guna is also a significant exporter of sesame seeds, another key export for the nation. Moreover, it has involvement in the import business. There is no conclusive proof that EFFORT’s holdings are involved in trade mispricings, but the possibilities that exist for party leaders are cause for particular concern. Perhaps, only the tenure of Seye Abraha , who was EFFORT’s CEO before his fallout with Meles Zenawi and subsequent six years imprisonment, has been thoroughly scrutinized. (He came out clean.) With the EPRDF’s obvious old boy’s network cutting across party, government, and business circles, EFFORT is suspected by many of being a convenient conduit for illicit financial flows. But again, the hard proofs are lacking so far. (Ditto for the much smaller EPRDF affiliated endowment funds for other regions.) Gold is now Ethiopia’s second biggest earner of foreign currency, bringing in about half as much as coffee. Most of it is exported by MIDROC, owned by Mohammed Al-Amoudi, an Ethio-Saudi billionaire, who owns the largest gold mine in the country. With hundreds of millions of dollars earned from exports, MIDROC is easily the nation’s principal exporter. Though instinctively apolitical, Al-Amoudi’s odd affiliation with the ruling party has long raised eye-brows. But even here, there is nothing more than a lingering suspicion that there is more than meets the eye. A favorite of corrupt officials everywhere is of course kickbacks. A kickback is the difference between market price and inflated payment to a company that wins a government contract. It’s a favorite of third world dictatorships. And though practiced at all levels of government, the real money is with foreign companies, which is an exclusive preserve of senior officials. Arms procurement is their particular favorite. Interestingly, kickback from arms purchases was an issue during the wrangling for primacy between Meles and his critics in the EPRDF ten years ago. None of the charges were ever proved. The 8.4 billions stolen from Ethiopia have no doubt mostly disappeared in to the black hole that is offshore banking. This is a huge part of international finance; more than 6 trillion US dollars lie there. The IMF estimates the illicit funds laundered annually by offshore banking at 1.5 trillion US dollars (of which half a billion is thought to come from fraud and corruption.) And until recently, Swiss was the favored haven. But since 2008, others, amongst them the Cayman Islands, have mrisen in popularity. The deposits in Cayman Island, whose population is only 54, 878, is estimated to hover around 1.9 trillion US dollars. In Africa, Ghana aspires to be the new destination for international offshore banking. There are abundant reasons to shun infamous Switzerland. Beyond the cruelty of stealing billions that could have gone a long way, in the words of UNDP, “to help children go to school, help mothers give birth safely, and expanding access to basic health care, better nutrition, and clean water and sanitation for all,” is the question of how this grand theft was possible.
The answer is simple: feeble rule of law; suffocated civil society; suppressed free media; nominal judicial independence; patronage based civil service—in sum, absence of a democracy with checks and balances. Where there is despotism there is corruption; particularly in the presence of a private sector. The problem is compounded when politics and business mix, which is the case for Ethiopia. The extent of corruption in Ethiopia, as indicated by the stolen 8.4 billion dollars, is a shocker not only to the naïve supporters of the EPRDF but also to its severest critics. Simply put, no one imagined it to be this big. But it is, and the problem requires an urgent remedy. This is money that has been stolen from Ethiopians, including all but a handful of the alleged 5 million members of the EPRDF. Rest assured that the time for accountability will come in due time. _____________ The writer can be reached at serk27@gmail.com

Is There a Way to Stop Ethiopia from Bleeding?


  • Ethiopia: The Art of Bleeding a Country Dry RATE: 0 Flag Ethio-Corruption, Inc. (Unlimited) “The people of Ethiopia are being bled dry. No matter how hard they try to fight their way out of absolute destitution and poverty, they will be swimming upstream against the current of illicit capital leakage”, wrote Economist Sarah Freitas who co-authored an upcoming report with Lead Economist Dev Kar of Global Financial Integrity (GFI). The GFI report entitled, “Illicit Financial Flows from Developing Countries over the Decade Ending 2009,” previewed in the Wall Street Journal, found that Ethiopia, which has a per-capita GDP of just US$365, lost US$11.7 billion to illicit financial outflows between 2000 and 2009. In 2009, illicit money leaving the economy totaled US$3.26 billion, which is double the amount in each of the two previous years… In 2008, Ethiopia received US$829 million in official development assistance, but this was swamped by the massive illicit outflows. The scope of Ethiopia’s capital flight is so severe that our conservative US$3.26 billion estimate greatly exceeds the US$2 billion value of Ethiopia’s total exports in 2009.” Two weeks ago in my commentary, “Why is Ethiopia Poor?”, I highlighted the fact that the Legatum Institute (LI), an independent non-partisan public policy group based in London, had recently ranked Ethiopia a pretty dismal 108th/110 countries on its 2011 Prosperity Index (LPI). Last year, the Oxford Poverty and Human Development Initiative (OPHDI) Multidimensional Poverty Index 2010 (formerly annual U.N.D.P. Human Poverty Index) ranked Ethiopia as the second poorest (ahead of famine-ravaged Mali) country on the planet. According to OPHDI, the percentage of the Ethiopian population in “severe poverty” (living on less than USD$1 a day) in 2005 was 72.3%. Six million Ethiopians needed emergency food aid in 2010 and many more millions needed food aid in 2011 in what the U.N. described as the “worst drought in over half a century to hit parts of East Africa”. The cancer of corruption is deeply embedded in the marrow of the Ethiopian body politic. The recently released Transparency International (TI) 2011 Corruption Perception Index report on Ethiopia confirms the findings of GFI and other anti-corruption international organizations. For the past decade, TI has ranked Ethiopia at the bottom of the barrel of countries ruled by the most corrupt governments. In fact, for the past ten years Ethiopia’s score on the TI index has remained virtually unchanged (TI ranks countries on a 0 (“highly corrupt”) to 10 (“very clean”) scale.
    TI Corruption Index Score for Ethiopia by Year 2011 2.7 2010 2.7 2009 2.7 2008 2.6 2007 2.4 2006 2.4 2005 2.2 2004 2.3 2003 2.5 2002 3.5 In light of the 2011 GFI and TI reports, is there any doubt today why Ethiopia is the second poorest nation in the world? Is it rocket science to figure out why Ethiopians are the second poorest people on the planet? Ethiopians are poor because they have been robbed, ripped off, flimflammed, bamboozled, conned, fleeced, scammed, hosed, swindled, suckered, hoodwinked, victimized, shafted and taken to the cleaners by those clinging to power like bloodsucking ticks on an African milk cow. Is it not mindboggling that the US$3.26 billion stolen out of Ethiopia in 2009 was double the amount stolen in 2008 and 2007!?! The Art of Bleeding Ethiopia Dry I have long argued that the business of African dictatorships is corruption. In a November 2009 commentary entitled “Africorruption Inc.”, I wrote the following about corruption in Ethiopia: The devastating impact of corruption on the continent's poor becomes self-evident as political leaders and public officials siphon off resources from critical school, hospital, road and other public works and community projects to line their pockets. For instance, reports of widespread corruption in Ethiopia in the form of outright theft and embezzlement of public funds, misuse and misappropriation of state property, nepotism, bribery, abuse of public authority and position to exact corrupt payments and gain are commonplace. The anecdotal stories of corruption in Ethiopia are shocking to the conscience. Doctors are unable to treat patients at the public hospitals because medicine and supplies are diverted for private gain. Tariffs are imposed on medicine and medical supplies brought into the country for public charity. Businessmen complain that they are unable to get permits and licenses without paying huge bribes or taking officials as silent partners. Publicly-owned assets are acquired by regime-supporters or officials through illegal transactions and fraud. Banks loan millions of dollars to front enterprises owned by regime officials or their supporters without sufficient or proper collateral. Businessmen must pay huge bribes or kickbacks to participate in public contracting and procurement. Those involved in the import/export business complain of shakedowns by corrupt customs officials. The judiciary is thoroughly corrupted through political interference and manipulation as evidenced in the various high profile political prosecutions. Ethiopians on holiday visits driving about town complain of shakedowns by police thugs on the streets. Two months ago, Ethiopia's former president Dr. Negasso Gidada offered substantial evidence of systemic political corruption by documenting the misuse and abuse of political power for partisan electoral advantage. Last week, U.S. State Department spokesman Ian Kelley stated that the U.S. is investigating allegations that "$850 million in food and anti-poverty aid from the U.S. is being distributed on the basis of political favoritism by the current prime minister's party." [As of December 2011, over two years after the investigation was launched, the State Department has not publicly released the results of its investigation.] Deceit, chicanery, paralogy and sophistry are the hallmarks of Meles Zenawi’s regime in Ethiopia. The cunning dictator has been able to shroud his corrupt empire by pursuing a propaganda policy of mass distraction and by staging one farcical political theatre after another. Zenawi has successfully distracted public attention from rampant corruption by Making wild allegations of terrorism against his critics, persecuting and prosecuting his opponents and by jailing and exiling independent journalists (a couple of weeks ago, Zenawi shuttered Awramba Times); Proclaiming a bogus Growth and Transformation Plan that will “double economic growth by an annual average of 14.9 percent” by 2015; Selling Ethiopia’s most fertile land for pennies above the table and for millions under the table; Panhandling the international community for famine and humanitarian aid and misusing that aid for political purposes; Taking massive loans from international banks without any significant accountability on how it is spent; Trying to shame and intimidate Western bankers and donors by hectoring them of the evils of “neoliberalism”; Proclaiming the construction of an imaginary hydroelectric dam over the River Nile; Sending troops to occupy Somalia and threatening war with other neighboring countries; Vilifying international human rights groups, election observers and officials of multilateral organizations who disagree with him; Dispatching swarms of officials to panhandle the Ethiopian Diaspora for nickels and dimes to buy dam bonds; Systematically extracting foreign remittances sent by Diaspora Ethiopians; Staging political theatre by a toothless anti-corruption agency to hoodwink complicit Western donors and loaners. Etc., etc. The Economics of Corruption The Economist Magazine in its November 7, 2006 editorial described “the Ethiopian government as one of the most economically illiterate in the modern world.” In 2009 at a high level meeting of Western donor policy makers in Berlin where, a German diplomat suggested that Ethiopia’s economic woes could be traced to “Meles’ poor understanding of economics”. They are all wrong! No one knows corruption, the economics of kleptocracy, better than Zenawi. The facts of Zenawi’s corruptonomics are plain for all to see: The economy is in the stranglehold of businesses owned or dominated by Zenawi family members, cronies, supporters or hangers-on. According to the World Bank, business enterprises affiliated with Zenawi’s regime control “freight transport, construction, pharmaceutical, and cement firms receive lucrative foreign aid contracts and highly favorable terms on loans from government banks.” Dataprovided by Zenawi’s regime showed that by the end of the 2009 fiscal year, Ethiopia’s outstanding debt stock was pegged at a crushing USD$5.2 billion. The USD$11.7 billion stolen over the past decade could easily retire that debt. Ethiopia is Africa’s largest recipient of foreign aid at nearly $USD4 billion in 2009, and the second largest foreign aid recipient in the world after Afghanistan.
    Is There a Way to Stop Ethiopia from Bleeding? The international community “naively” believes that corruption in Ethiopia and the rest of Africa could be controlled and significantly reduced by anti-corruption programs. The U.N. Convention Against Corruption (2003)requires signatories to “develop and implement or maintain effective, coordinated anti-corruption policies that promote the participation of society and reflect the principles of the rule of law, proper management of public affairs and public property, integrity, transparency and accountability.” Ethiopia signed the U.N. Convention in 2003. The Africa Union Convention on Preventing and Combatting Corruption (2003) established a regime to empower African countries to “prevent, detect, punish and eradicate corruption and related offences in the public and private sectors.” The Convention prescribes that “in order to combat corruption and related offences in the public service, State Parties” shall “require public officials to declare their assets at the time of assumption of office during and after their term of office in the public service.” Ethiopia signed the AU Convention in 2004. Neither of these Conventions has even made a dent in controlling the metastasizing corruption in Ethiopia.
    Zenawi knows the power of corruption. He has effectively used corruption allegations to neutralize and eliminate his political opponents. He used his “Federal Ethics and Anticorruption Commission” to railroad his comrade-in-arms and former defense minister, Seeye Abraha, to jail for six years on unsubstantiated allegations of corruption. When then-Judge Birtukan Midekssa, and later Ethiopia’s first female political party leader and long suffering political prisoner, released Seeye for lack of evidence, Zenawi rammed legislation through his rubberstamp parliament to deny Seeye bail and keep him in pretrial detention. He later fired Judge Birtukan. In 2008, Zenawi’s anticorruption commission reported that "USD$16 million dollars" worth of gold bars simply walked out of the bank in broad daylight. A number of culprits were fingered for the inside bank job, but no one was ever prosecuted. In February 2011, Zenawi publicly stated that 10,000 tons of coffee earmarked for exports had simply vanished from the warehouses. He called a meeting of commodities traders and in a videotaped statement told them he will forgive them because “we all have our hands in the disappearance of the coffee”. He warned them that if anyone should steal coffee in the future, he will “cut off their hands”. For years, I have documented and railed against corruption in Ethiopia. In December 2008, three years to the month, in a weekly commentary entitled, “The Bleeping Business of Corruption in Ethiopia”, I wrote:
    The fact of the matter is that the culture of corruption is the modus operandi in the Ethiopian body politics. Former president Dr. Negasso Gidada clearly understood that when he declared in 2001 that ‘corruption has riddled state enterprises to the core,’ adding that the government would show ‘an iron fist against corruption and graft as the illicit practices had now become endemic’. In 2007 when Ethiopia’s auditor general, Lema Aregaw, reported that Birr 600 million of state funds were missing from the regional coffers, Zenawi fired Lema and publicly defended the regional administrations’ ‘right to burn money.’…. Ironically, in 2003, Ethiopia signed the U.N. Convention Against Corruption; and a couple of months ago, a conference on institutions, culture, and corruption was hosted jointly in Addis Ababa by the United Nations Economic Commission for Africa and the Council for the Development of Social Science Research in Africa.
    The fact of the matter is that absolute power corrupts absolutely. Zenawi has absolute power in Ethiopia. Pleading for transparency and issuing moral exhortations against corruption will have no effect on the behavior of Zenawi or any of the other African dictators. Indeed, to plead the virtues of accountability, transparency and good governance with Zenawi and Co., is like preaching Scripture to a gathering of heathens. It means nothing to them. They are unfazed by moral hectoring or appeals to conscience. They sneer and jeer at those who rail and vociferate against corruption. Preaching to the corrupt, to put it simply, is an exercise in total futility! In my November 7 commentary “To Catch Africa’s Biggest Thieves Hiding in America!”, I discussed the importance of initiating and cooperating with the U.S. Justice Department (DOJ) in civil forfeiture actions to seize corruptly obtained cash, personal or real property of any person or entity that can be traced to “specified unlawful activity”. These civil court actions extend to foreign offenses involving extortion, money laundering, or the misappropriation, theft or embezzlement of public funds by or for the benefit of a public official of a foreign government. (18 U.S. C. sections 981 (a) (1) (c); 1956; 1957.) The U.S. has recently filed action to seize personal and real property of Teodoro Nguema Obiang Mangue, the 43-year old son of President Teodoro Obiang Nguema Mbasogo of Equatorial Guinea.
    Carefully review and analysis of GFI and TI data sources reveals that public assets and funds stolen from many African countries, including Ethiopia, are often hidden in banks located in the U.S. and Europe, although the clever African dictators are now diversifying by taking advantage of financial havens in countries experiencing rapid growth and industrialization. Much of the corruption activity centers around money laundering (that is, illegal or dirty money is put through a complex cycle of financial transactions or washed and is transformed into legitimate or clean money).
    The basic idea in money laundering is to minimize the chances of detection of stolen public assets and funds by breaking the direct link between the kleptocrats or “corruptocrats” and their collaborators by disguising the true ownership. Using financial consultants, shell companies (bogus companies that exist to simply create the appearance of legitimate transactions through fake invoices and balance sheets), fraudulent official documentation, wire transactions, and “smurfing” techniques (breaking up large amounts of money into smaller, less-suspicious amounts in the names of multiple persons) etc., those who have stolen public assets and funds try to sever or camouflage their loot from its illegal source by placing it in international financial institutions. The aim in money laundering is at least twofold: 1) gain anonymity and hide the audit trail in case of a criminal investigation, and 2) plough the “clean money” into the legitimate economy by buying homes, investing in legitimate businesses, starting businesses and so on. If the problem of corruption is to be addressed effectively in Ethiopia and the rest of Africa, it is not going to be at the fountainhead of the corruption itself but in the ocean where the river of corruption terminally flows. As one cannot expect the fox to safeguard the henhouse, one cannot similarly expect Africa’s dictators and corruptocrats and their collaborators to safeguard public assets and funds. A big part of the answer to the question of corruption lies in the Laundromats of financial institutions where the dirty money is washed. That’s why I believe it is the civic and moral duty of every Ethiopian and African to help the U.S. Justice Department catch Africa’s biggest thieves hiding in America. It is very easy to do, and do it anonymously. Individuals with information about possible proceeds of foreign corruption in the United States, or funds laundered through institutions in the United States, should contact Immigration and Customs Enforcement, Homeland Security Investigations (ICE HIS) toll free at 866-347-2423 or send email to: eginfo1@ice.dhs.gov. If calling from outside of the U.S., the number is: 802-872-6199 BLOW THE WHISTLE ON AFRICA’S BIGGEST THIEVES HIDING IN AMERICA!!! Previous commentaries by the author are available at: www.huffingtonpost.com/alemayehu-g-mariam/ and http://open.salon.com/blog/almariam/

Monday, March 10, 2014

ኢትዮጵያዊነት- ወንጀል፣ሀፍረት፣ውርደት.. ሆኗል።



በሆላንድና በጀመርመን በሚሊዮን የሚቆጠሩ ቱርኮችና ሞሮኮዎች አሉ።ምዕራባውያኑ በሁለተኛው የዓለም ጦርነት የፈራረሱ
ከተሞቻቸውን መልሰው ሲገነቡ ለጉልበት ሥራ ቀጥረዋቸው ነው ያመጧቸው። እናም ላባቸውን ጠብ አድርገው በመስራት አገር አቅንተዋል። በመሆኑም በአገራቱን እንደ ሁለተኛ አገራቸው ያዩዋቸዋል። ተዋልደዋል፣በዘተዋል ፤ እንደቆይታቸውም በተለይ በሱቆችና በምግብ ቤቶች ኢንቨስትመንት በስፋት ተሰማርተው የተዋጣላቸው ነጋዴዎች ሆነዋል። ያኔ ጀርመኖች- እነ አከንን የመሣሰሉ በጦርነቱ የወደሙባቸውን ከተሞች መልሰው ሲገነቡ ኢትዮጵያውያንም በሥራው እንዲሳተፉ ተመሣሳይ ጥያቄ አቅርበው ነበር። ነገሩን እንደ ባርነት የተመለከቱት ቀዳማዊ ሀይለሥላሴ ግን፤- “ ህዘቤን ለከባድ የጉልበት ሥራ ወደ ባዕድ ምድር አልልክም” ብለው ሳይፈቅዱ ቀሩ። ያኔ-ኢትዮጵያ ዓለማቀፍ ክብርና ተሰሚነት ነበራት።ድህነትም እንዳሁኑ በሰው ላይ ጢብ ጢብ አይጫዎትም ነበር። ይልቁንም እንግሊዘ ውስጥ የጎርፍ አደጋ መድረሱን ተከትሎ መርከብ ሙሉ ቡና እስከመርዳት የደረስንበት ዘመን ነበር።ለትምህርትም ሆነ ለሥራ ወደ ውጪ ሀገራት የሚላኩ ኢትዮጵያውያንም ጉጉታቸው- ተልዕኳቸውን ጨርሰው ወደ አገራቸው መመለስ እንደነበር በባለቤቶቹ ተጽፎ አንብበናል፤ ሲነገር ሰምተናል።
ያኔ በህጋዊ መንገድ በአውሮፓውያኑ ለሥራ ስንጠየቅ የኮራነው ኢትዮጵያውያን እነሆ በመካከለኛው ምሥራቅ አገሮች የሞግ ዘትነት እንጀራ ለማግኘት መከራችንን እናያለን። “ታፍራና ተከብራ..ነፃነቷን አስጠብቃ…”የኖረች አገር እነሆ ሀፍረቷ ተገላልጦና የሁሉም ማላገጫና መዘባበቻ ሆና ቀርታለች። ኢትዮጵያዊነት- ወንጀል፣ሀፍረት፣ውርደት.. ሆኗል።
አዎ! ተዋርደናል!በጣም ተዋርደናል፣ እጅግ ተዋርደናል!(እየነደደኝ)

As fire blazes markets, Harar engulfed with clashes ሐረር በእሳት አደጋ፣ በጥይት ሩምታ፣ በሕዝባዊ ተቃውሞና በቆመጥ ድብደባ ስትታመስ ዋለች


After a fire broke out inside Harar’s markets, Eastern Ethiopia, protests and clashes have began between the shop owners and government securities in the city. The cause of the fire has not been known.
Police have reportedly detained a number of people.
Details to come…
ሐረር በእሳት አደጋ፣ በጥይት ሩምታ፣ በሕዝባዊ ተቃውሞና በቆመጥ ድብደባ ስትታመስ ዋለች
march10/2014 ዘ-ሐበሻ እንደዘገበው በሐረር ትናንት ምሽት ከግምት ከሶስት ሰዓት ተኩል ጀምሮ ልዩ ስሙ መብራት ሃይል ተበሎ በሚታወቀው የገበያ ቦታ በተነሳ እሳት አደጋ የበርካታ ነጋዴዎች ንብረት ከወደመ በኋላ “የእሳት አደጋውን የክልሉ መንግስት ሆን ብሎ ያቀነባበረው ነው” በሚል የአካባቢው ነዋሪ በዛሬው ዕለት ተቃውሞን ለመግለጽ አደባባይ ወጥቶ እሳቱን ለማጥፋት ውሃ ያልነበረው የክልሉ የእሳት አደጋ ማጥፊያ የተቃውሞ ሰልፈኛውን ለመበተን ውሃና አስለቃሽ ጭስ ሲጠቀም ዋለ። የክልሉ ፖሊስም በጥይት ሩምታ በማውረድ፣ በቆመጥ በመደብደብ ሰልፈኛውን ሲበትን መዋሉን ለዘ-ሐበሻ ከስፍራው የደረሱ ዜናዎች አመልክተዋል።
የዘ-ሐበሻ ተባባሪ ዘጋቢዎች ከሐረር በትናንቱ የእሳት አደጋ ቃጠሎ ንብረታቸው ከወደመባቸው መካከል የተወሰኑትን በማነጋጋር ባጠናቀሩት መረጃ “የክልሉ መንግስት ነጋዴዎቹ ይሰሩበት የነበረውን ቦታ ይፈልገው ነበር። በተደጋጋሚም እንዲነሱ ጠይቋል። ነጋዴዎቹ ከዚህ ቀደም ከ3 ዓመታት በፊት ሸዋበር አካባቢ በተመሳሳይ ሴራ ንብረታቸው የተቃጠለባቸው መሆኑን እና በትናንቱ አደጋ ንብረታቸው ሙሉ በሙሉ በመውደሙ ለተቃውሞ አደባባይ እንዳስወጣቸው መረዳት ችለናል።

በመብራት ሃይል የገበያ ቦታ የተነሳው እሳትን ለማጥፋት የተደረገው ርብርቦሽ በጣም ደካማ እንደነበር የሚገልጹት እነዚሁ ነጋዴዎች ከድሬደዋ እና ከጅጅጋ የእሳት አደጋ ማጥፊያ ብርጌድ እስኪመጣ ድረስ ብዙ ንብረት ወድሟል። እሳቱ ሳይስፋፋ ነጋዴዎቹም የተወሰነ ንብረት እንኳ ከእሳቱ እንዲያተርፉት አለመደረጉን የገለጹት እነዚሁ ባለንብረቶች መንግስት ወዲያውኑ የተቃጠለውን አካባቢ በግሬደር ማረሱ አስገራሚ ሆኖባቸው ነጋዴዎቹ ዛሬ አደባባይ ወጥተው ተቃውሟቸውን ሲያሰሙ ነበር።

በብሶት የተወጠረው የሃረር ሕዝብ ባስነሳው ተቃውሞ የክልሉ ፖሊስ በአስለቃሽ ጭስ፣ በቆመጥ ድብደባ፣ በውሃ፣ በጥይት ሲበትን የዋለ መሆኑን የገለጹት የዘ-ሐበሻ ዘጋቢዎች በርካታ ሰዎች መታፈሳቸውንም ገልጸዋል።

በዚህ የተቃውሞ እንስቃሴ ላይ የሞተ ሰው እንዳለ ለማረጋገጥ ያደረግነው ሙከራ ባይሳካም በርካታ ሰዎች መቁሰላቸው ግን ተሰምቷል።
ተጨማሪ መረጃዎች እንደደረሱን እንመለሳለን።