Wednesday, May 21, 2014

በጋዜጠኞቹ እና በጦማሪያኑ ላይ ተጨማሪ የምርመራ ጊዜ ተሰጠ


May 21/2014 
ሰበር ዜና፡- ፍርድ ቤቱ በተጠረጠሩት ጋዜጠኞችና ጦማሪያን ላይ የ10 ቀን ተጨማሪ ጊዜ ፈቀደ
-    “ከአሸባሪ ድርጅቶች ጋር ስልጠና ወስደዋል፤ ብርም ተቀብለዋል” ፖሊስ
-    “ስልጠና የወሰዱት ‘አርቲክል 19’ እና ‘ፍሪደም ሀውስ’ ከተሰኙ በአሜሪካና በእንግሊዝ መንግሥታት ዕውቅና ከተሰጣቸው ዓለም አቀፍ ህጋዊ ድርጅቶች ነው” ጠበቆች
-    “ከአሸባሪ ድርጅቶች ጋር ስልጠና ወስደዋል፤ ብርም ተቀብለዋል” ፖሊስ
-    “ስልጠና የወሰዱት ‘አርቲክል 19’ እና ‘ፍሪደም ሀውስ’ ከተሰኙ በአሜሪካና በእንግሊዝ መንግሥታት ዕውቅና ከተሰጣቸው ዓለም አቀፍ ህጋዊ ድርጅቶች ነው” ጠበቆች

ምስጢራዊ በሆነ መንገድ በህቡዕ በመድራጀት፣ በህጋዊ መንገድ ስልጣን የያዘውን መንግስት በህገወጥ መንገድ ከስልጣን ለማውረድ በማሰብ፣ ውጪ ሀገር ከሚገኙ አሸባሪ ድርጅቶች ጋር በመስማማትና ሀገሪቱን ለማተራመስ ትዕዛዝ በመቀበል የገንዘብና የስልጠና ድጋፍ በመውሰድ፤ በአገሪቱ ላይ ብጥብጥ ለማስነሳትና ብጥብጡንም ለመምራት በመንቀሳቀስ የሽብር ተግባር ፈፅመዋል ሲል የፌዴራል ፖሊስ ወንጀል ምርመራ ቡድን በሶስት መዝገቦች ከፋፍሎ እየመረመራቸው የሚገኙት ጋዜጠኞችና ጦማሪያን የ28 እና የ14 ቀናት የምርመራ ጊዜ ቀጠሮ ተሰጠባቸው።
ቅዳሜ ግንቦት 10 ቀን 2006 ዓ.ም በፌዴራሉ የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት አንደኛ አራዳ ምድብ ችሎት በቅድሚያ የቀረቡት በእነ አጥናፍ መዝገብ ስር የሚገኙት ጦማሪያኑ አጥናፍ ብርሃነ፣ ናትናኤል ፈለቀ እና ጋዜጠኛ ኤደም ካሳዬ ናቸው።
በተመሳሳይም በእነዘላለም መዝገብ ስር የዞን ዘጠኝ ጦማሪውና የህግ መምህሩ ዘላለም ክብረት፣ ጋዜጠኛ ተስፋለም ወልደየስና ጋዜጠኛ አስማማው ወ/ጊዮርጊስ እንዲቀርቡ ተደርጓል።
ሁለቱ መዝገቦች ተለያይተው ቢቀርቡም የምርመራ ቡድኑ በሁሉም መዝገቦች ላይ ተመሳሳይ ሀሳብ ያቀረበ ሲሆን በክርክር ይዘትም ሲታይ የሶስቱም ተመሳሳይነት የሚታይበት ነው።
ተጠራጠሪዎቹ በቁጥጥር ስር ከዋሉ በኋላ ለሁለተኛ ጊዜ ችሎት ቀርበው ፖሊስ በጠየቀው እና ፍርድ ቤቱም በፈቀደው የ10 ቀናት ተጨማሪ የምርመራ ጊዜ ቀጠሮ ውስጥ ፖሊስ ያከናወናቸውን ተግባራት ዳኛው በመጠየቅ የተጀመረው ይህ ችሎት ከፖሊስ የተገኘው ምላሽ፣ “ተጠርጣሪዎቹ የተፃፋፏቸውን ፅሁፎች ለማስተርጎም በሂደት ላይ መሆናቸውን፤ የምስክሮችን ቃል ለመቀበል የማስፈራራት ሁኔታ በመግጠሙ አዳጋች መሆኑን፤ ቀሪ ግብረአበሮችን በአድራሻ መለዋወጥ ምክንያት አለመያዛቸው በመጥቀስ ለዚህም ድርጊቱ በቡድንና በህቡዕ የሚከናወን መሆኑን ለፍርድ ቤቱ አስረድቶ ሊፈፀም የታቀደው የሽብር ተግባር ነው ሲል ተጨማሪ 28 ቀናት የምርመራ ጊዜ እንዲሰጠው ጠይቋል።
በተጠርጣሪዎቹ ጠበቆች በኩልም፤ ፖሊስ ተጠርጣሪዎቹን በቁጥጥር ስር ካዋለ 23 ቀናት ቢልፉም ምንም አዲስ ነገር አለመፈፀሙን በመጠቆም፤ ሲጀመር ለጥርጣሬው ዋና ምክንያት አድርጎ ያቀረበውን በማህበራዊ ድረ-ገፅ ላይ መፃፍ የሚል ሃሳብ ቀይሮ የሽብር ተግበራ ፈፅመዋል ማለቱ አዲስ እንደሆነባቸው፤ ለዚህም ፍርድ ቤቱ ጉዳዩን ከመዝገቡ መርምሮ በመደበኛ የወንጀል ህግ ጊዜ ቀጠሮ እንዲሰጥ አሳስበዋል። አያይዘውም መርማሪ ቡድኑ በመዝገቡ በይፋ የጠቀሰው ኢትዮጵያም ሆነ አለማቀፋዊ የሽብር ድርጅት አለመኖሩን በማስታወስ ተጠርጣሪዎቹ ስልጠና ወስደዋል ከተባለም የአሜሪካና የእንግሊዝ መንግስታት እውቅና ከሰጧቸው “አርቲክል 19” እና “ፍሪደም ሀውስ” ከተባሉ ድርጅቶች እንደሆነ፣ እነዚህም በአለም አቀፍ ደረጃ ሀሳብን በነፃነት የመግለፅ መብት ላይ የሚሰሩ ሕጋዊ ተቋማት ናቸው ሲሉ አስታውሰዋል።
ፖሊስም በሰጠው ምላሽ፤ ድርጊቱ በቡድንና በህቡዕ የተፈፀመ መሆኑን፤ ምስክሮች ቃላቸውን እንዳይሰጡ በተጠርጣሪዎቹ ግብአበሮች ዛቻና ማስፈራሪያ እየተፈፀመባቸውና አድራሻቸውን እንዲቀይሩ መደረጋቸው ቃላቸውን ለመቀበል አዳጋች እየሆነበት መምጣቱን፤ ከተጠርጣሪዎቹ ኢሜይሎች የተገኙት ማስረጃዎች አስተርጉሞ ለማቅረብ በሂደት ላይ መሆኑን እና በዳታ ክፍሉ ውስጥ ፖሊስ ያለው ኮምፒዩተር አንድ ብቻ በመሆኑ በኢሜይል የቀረቡትን ፅሁፎች መርምሮ ለመጨረስ እንቅፋት እንደሆነበት ለፍርድ ቤቱ አስረድቷል።
የግራ ቀኙን ሀሳብ የመረመረው ፍርድ ቤቱም ፖሊስ ባለፈው የተሰጠውን የ10 ቀናት የምርመራ ጊዜ ቀጠሮን በሚገባ እንዳልተጠቀመበት አስታውሶ፤ ነገር ግን መዝገቡ ከሽብር ድርጊት ጋር የተያያዘ ለጥርጣሬ የሚያበቃ በቂ ምክንያት አለኝ ካለ ተጨማሪ የምርመራ ጊዜ ሊሰጠው ይገባል በሚሉት በሁለቱም መዝገቦች ላይ የ28 ቀናትን የምርመራ ጊዜ ፈቅዷል። በመሆኑም ተጠርጣሪዎቹ ሰኔ 7 ቀን በ2006ዓ.ም እንዲቀርቡ ታዟል።
በተያያዘም በማግስቱ እሁድ ቀጠሮ ተይዞለት የነበረው ሶስተኛ መዝገብ በጦማሪያኑ አቤል ዋበላ፣ በፍቃዱ ኃይሉና ማህሌት ፋንታሁን የቀረቡ ሲሆን በችሎቱ የተሰየሙት ዳኛ ከመቀየራቸው ውጪ የፌዴራል ፖሊስ ወንጀል ምርመራ ቡድን አባላቱ ከቅዳሜው መዝገብ ጋር ተመሳሳይ የሆነ ሃሳብ የያዘ ደብዳቤ በማቅረብ ጉዳዩን ለመመርመር ተጨማሪ የ28 ቀን የጊዜ ቀጠሮ እንዲሰጠው ፍ/ቤቱን ጠይቋል።
ፖሊስ በተሰጠው የጊዜ ቀጠሮ ውስጥ ስላከናወናቸው ተግባራት በፍርድ ቤቱ ሲጠየቅ፤ “ፖሊስ ወረዳቸውን ተቀብሎ ኢሜይላቸውን ፈትሸናል። ከዚያም ውስጥ ከሽብርተኛ ድርጅት ጋር የተፃፃፉትን መልዕክት አግኝተናል” የሚል ምላሽ ሰጥቷል። ያም ሆኖ ይህ አገኘነው የሚሉትና የተላኩትን መልዕክት ከመዝገቡ ጋር መያያዝ አስመልክቶ ፍርድ ቤቱ ላቀረበው ጥያቄ ፖሊስ፤ አለማያያዙን ተናግሯል። ይህን ተከትሎም ዳኛዋ፣ “መዝገቡ እንደሚያሳየው መጀመሪያ ሲከፈት ከተከፈተበት የጥርጣሬ ምክንያት በተለየ የጠቀሳችሁ አዲስ ነገር የለም” በሚል በፖሊስ ከሽብር ሕጉ ጋር በማገናኘት የጠየቀውን የ28 ቀናት ጊዜ ቀጠሮ ውድቅ በማድረግ የ14 ቀናት የጊዜ ቀጠሮ በመፍቀድ ለግንቦት 24 ቀን 2006 ዓ.ም ቀጥሯል።
በሁለቱም ቀናት በፍርድ ቤቱ ቅጥር ግቢ ውስጥ በርከት ያሉ የተጠርጣሪዎቹ ቤተሰቦች፣ ወዳጅ ዘመድ፣ የአገር ውስጥና የውጪ ጋዜጠኞች እንዲሁም አምባሳደሮችና ዲፕሎማቶች ተገኝተው ነበር።
ምስጢራዊ በሆነ መንገድ በህቡዕ በመድራጀት፣ በህጋዊ መንገድ ስልጣን የያዘውን መንግስት በህገወጥ መንገድ ከስልጣን ለማውረድ በማሰብ፣ ውጪ ሀገር ከሚገኙ አሸባሪ ድርጅቶች ጋር በመስማማትና ሀገሪቱን ለማተራመስ ትዕዛዝ በመቀበል የገንዘብና የስልጠና ድጋፍ በመውሰድ፤ በአገሪቱ ላይ ብጥብጥ ለማስነሳትና ብጥብጡንም ለመምራት በመንቀሳቀስ የሽብር ተግባር ፈፅመዋል ሲል የፌዴራል ፖሊስ ወንጀል ምርመራ ቡድን በሶስት መዝገቦች ከፋፍሎ እየመረመራቸው የሚገኙት ጋዜጠኞችና ጦማሪያን የ28 እና የ14 ቀናት የምርመራ ጊዜ ቀጠሮ ተሰጠባቸው።
ቅዳሜ ግንቦት 10 ቀን 2006 ዓ.ም በፌዴራሉ የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት አንደኛ አራዳ ምድብ ችሎት በቅድሚያ የቀረቡት በእነ አጥናፍ መዝገብ ስር የሚገኙት ጦማሪያኑ አጥናፍ ብርሃነ፣ ናትናኤል ፈለቀ እና ጋዜጠኛ ኤደም ካሳዬ ናቸው።
በተመሳሳይም በእነዘላለም መዝገብ ስር የዞን ዘጠኝ ጦማሪውና የህግ መምህሩ ዘላለም ክብረት፣ ጋዜጠኛ ተስፋለም ወልደየስና ጋዜጠኛ አስማማው ወ/ጊዮርጊስ እንዲቀርቡ ተደርጓል።
ሁለቱ መዝገቦች ተለያይተው ቢቀርቡም የምርመራ ቡድኑ በሁሉም መዝገቦች ላይ ተመሳሳይ ሀሳብ ያቀረበ ሲሆን በክርክር ይዘትም ሲታይ የሶስቱም ተመሳሳይነት የሚታይበት ነው።
ተጠራጠሪዎቹ በቁጥጥር ስር ከዋሉ በኋላ ለሁለተኛ ጊዜ ችሎት ቀርበው ፖሊስ በጠየቀው እና ፍርድ ቤቱም በፈቀደው የ10 ቀናት ተጨማሪ የምርመራ ጊዜ ቀጠሮ ውስጥ ፖሊስ ያከናወናቸውን ተግባራት ዳኛው በመጠየቅ የተጀመረው ይህ ችሎት ከፖሊስ የተገኘው ምላሽ፣ “ተጠርጣሪዎቹ የተፃፋፏቸውን ፅሁፎች ለማስተርጎም በሂደት ላይ መሆናቸውን፤ የምስክሮችን ቃል ለመቀበል የማስፈራራት ሁኔታ በመግጠሙ አዳጋች መሆኑን፤ ቀሪ ግብረአበሮችን በአድራሻ መለዋወጥ ምክንያት አለመያዛቸው በመጥቀስ ለዚህም ድርጊቱ በቡድንና በህቡዕ የሚከናወን መሆኑን ለፍርድ ቤቱ አስረድቶ ሊፈፀም የታቀደው የሽብር ተግባር ነው ሲል ተጨማሪ 28 ቀናት የምርመራ ጊዜ እንዲሰጠው ጠይቋል።
በተጠርጣሪዎቹ ጠበቆች በኩልም፤ ፖሊስ ተጠርጣሪዎቹን በቁጥጥር ስር ካዋለ 23 ቀናት ቢልፉም ምንም አዲስ ነገር አለመፈፀሙን በመጠቆም፤ ሲጀመር ለጥርጣሬው ዋና ምክንያት አድርጎ ያቀረበውን በማህበራዊ ድረ-ገፅ ላይ መፃፍ የሚል ሃሳብ ቀይሮ የሽብር ተግበራ ፈፅመዋል ማለቱ አዲስ እንደሆነባቸው፤ ለዚህም ፍርድ ቤቱ ጉዳዩን ከመዝገቡ መርምሮ በመደበኛ የወንጀል ህግ ጊዜ ቀጠሮ እንዲሰጥ አሳስበዋል። አያይዘውም መርማሪ ቡድኑ በመዝገቡ በይፋ የጠቀሰው ኢትዮጵያም ሆነ አለማቀፋዊ የሽብር ድርጅት አለመኖሩን በማስታወስ ተጠርጣሪዎቹ ስልጠና ወስደዋል ከተባለም የአሜሪካና የእንግሊዝ መንግስታት እውቅና ከሰጧቸው “አርቲክል 19” እና “ፍሪደም ሀውስ” ከተባሉ ድርጅቶች እንደሆነ፣ እነዚህም በአለም አቀፍ ደረጃ ሀሳብን በነፃነት የመግለፅ መብት ላይ የሚሰሩ ሕጋዊ ተቋማት ናቸው ሲሉ አስታውሰዋል።
ፖሊስም በሰጠው ምላሽ፤ ድርጊቱ በቡድንና በህቡዕ የተፈፀመ መሆኑን፤ ምስክሮች ቃላቸውን እንዳይሰጡ በተጠርጣሪዎቹ ግብአበሮች ዛቻና ማስፈራሪያ እየተፈፀመባቸውና አድራሻቸውን እንዲቀይሩ መደረጋቸው ቃላቸውን ለመቀበል አዳጋች እየሆነበት መምጣቱን፤ ከተጠርጣሪዎቹ ኢሜይሎች የተገኙት ማስረጃዎች አስተርጉሞ ለማቅረብ በሂደት ላይ መሆኑን እና በዳታ ክፍሉ ውስጥ ፖሊስ ያለው ኮምፒዩተር አንድ ብቻ በመሆኑ በኢሜይል የቀረቡትን ፅሁፎች መርምሮ ለመጨረስ እንቅፋት እንደሆነበት ለፍርድ ቤቱ አስረድቷል።
የግራ ቀኙን ሀሳብ የመረመረው ፍርድ ቤቱም ፖሊስ ባለፈው የተሰጠውን የ10 ቀናት የምርመራ ጊዜ ቀጠሮን በሚገባ እንዳልተጠቀመበት አስታውሶ፤ ነገር ግን መዝገቡ ከሽብር ድርጊት ጋር የተያያዘ ለጥርጣሬ የሚያበቃ በቂ ምክንያት አለኝ ካለ ተጨማሪ የምርመራ ጊዜ ሊሰጠው ይገባል በሚሉት በሁለቱም መዝገቦች ላይ የ28 ቀናትን የምርመራ ጊዜ ፈቅዷል። በመሆኑም ተጠርጣሪዎቹ ሰኔ 7 ቀን በ2006ዓ.ም እንዲቀርቡ ታዟል።
በተያያዘም በማግስቱ እሁድ ቀጠሮ ተይዞለት የነበረው ሶስተኛ መዝገብ በጦማሪያኑ አቤል ዋበላ፣ በፍቃዱ ኃይሉና ማህሌት ፋንታሁን የቀረቡ ሲሆን በችሎቱ የተሰየሙት ዳኛ ከመቀየራቸው ውጪ የፌዴራል ፖሊስ ወንጀል ምርመራ ቡድን አባላቱ ከቅዳሜው መዝገብ ጋር ተመሳሳይ የሆነ ሃሳብ የያዘ ደብዳቤ በማቅረብ ጉዳዩን ለመመርመር ተጨማሪ የ28 ቀን የጊዜ ቀጠሮ እንዲሰጠው ፍ/ቤቱን ጠይቋል።
ፖሊስ በተሰጠው የጊዜ ቀጠሮ ውስጥ ስላከናወናቸው ተግባራት በፍርድ ቤቱ ሲጠየቅ፤ “ፖሊስ ወረዳቸውን ተቀብሎ ኢሜይላቸውን ፈትሸናል። ከዚያም ውስጥ ከሽብርተኛ ድርጅት ጋር የተፃፃፉትን መልዕክት አግኝተናል” የሚል ምላሽ ሰጥቷል። ያም ሆኖ ይህ አገኘነው የሚሉትና የተላኩትን መልዕክት ከመዝገቡ ጋር መያያዝ አስመልክቶ ፍርድ ቤቱ ላቀረበው ጥያቄ ፖሊስ፤ አለማያያዙን ተናግሯል። ይህን ተከትሎም ዳኛዋ፣ “መዝገቡ እንደሚያሳየው መጀመሪያ ሲከፈት ከተከፈተበት የጥርጣሬ ምክንያት በተለየ የጠቀሳችሁ አዲስ ነገር የለም” በሚል በፖሊስ ከሽብር ሕጉ ጋር በማገናኘት የጠየቀውን የ28 ቀናት ጊዜ ቀጠሮ ውድቅ በማድረግ የ14 ቀናት የጊዜ ቀጠሮ በመፍቀድ ለግንቦት 24 ቀን 2006 ዓ.ም ቀጥሯል።
በሁለቱም ቀናት በፍርድ ቤቱ ቅጥር ግቢ ውስጥ በርከት ያሉ የተጠርጣሪዎቹ ቤተሰቦች፣ ወዳጅ ዘመድ፣ የአገር ውስጥና የውጪ ጋዜጠኞች እንዲሁም አምባሳደሮችና ዲፕሎማቶች ተገኝተው ነበር።

Monday, May 19, 2014

TPLF Dominated Import- Export Business in Ethiopian And Apartheid/Discrimination System


TPLF Dominated Import- Export Business in Ethiopian And Apartheid/Discrimination System
I had informed the majority Ethiopians in diaspora about the big discount the Ethiopian Airlines is giving to Tigrean Origin people only by totally discriminating the majority Oromo, Amara, Somalia, Afars and other ethnic Ethiopia. A 40% discount to Tigrean from diaspora is a big loss to the airline but an intentional discrimination to the majority. Now, the Ethiopian Shipping lines with its “HIDDEN MAIN” head quarter in Mekele purchased nine new cargo fleets from China at cost of $300 million while 6.5 Ethiopians from Amara, Somalia and Oromo are starving at this time.
These cargo fleets will help the import and export business in the country which is 100% controlled by the minority ethnic clan called Tigrai People (5% of the total population of Ethiopia). In the last 23 years the import and export of all business in Ethiopia is controlled by Tigrean’s minority clan.
They don’t pay Customs tariff on imports and exports – Free taxes and transportation service. All this at the cost of “the other colonized Oromo, Amara and Somali majority’” – which cannot compete with “TIGRAI People” since they don’t have privileges for such an advantage on FREE Custom Tariffs and Transportation Cost.
The main reason Gurage, Amara and Oromo are closing their business in Ethiopia such as in Markato. Now these nine cargo vessels will accelerate the import/export business of Tigreans Minority NOT the Majority Ethiopian unless they do something before too late.The nine vessels are named after the capital cities of the nine regional states in Ethiopia. President Ismail said at the inauguration, “Djibouti gives a port service to Ethiopia but it does not consider that it is giving the service to another country but regards it as it is doing it for itself, we believe that Ethiopia is Djibouti and Djibouti is Ethiopia, no difference at all “.Prime Minister Hailemariam Desalegn said on his speech “The vessels are not only Ethiopian assets but they are also
The Question is Does Each Ethnic Controlled their Cargo? Why Tigrean Controlled them? Giving Awasa or Bahr-Dar name is a Futile attempt to Mislead the Public.
source mereja.com

”ወያኔ ትግሬ በመሆኑ ብቻ ትግሬ ሁሉ ዕዳ አለበት ማለት እንደወያኔ ማሰብ ነው”

የወያኔ ጥላቻ ፍሬመስፍን ወልደ ማርያም

Imageወያኔ ለትግራይ ሕዝብ ሀብትንና ብልጽግናን አመጣ ብለው የሚያምኑ ሰዎች ብዙ ናቸው፤ ወያኔ የሥልጣን ወንበሩ ላይ በመውጣቱ ትግሬዎች ሁሉ አልፎላቸዋል ተብሎ ይታመናል፤ በተለይ በአውሮፓና በአሜሪካ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን በዚህ ላይ የጠነከረ እምነት አላቸው፤ በዚህ ጉዳይ ላይ ከኢትዮጵያ ውጭ ብዙ ውይይትም ይሁን ንትርክ ይደረጋል፤ በኢትዮጵያ ውስጥ ግን የተፈራ ርእስ ነው፤ ውስጥ-ውስጡን እንጂ አደባባይ አይወጣም፤ ይህንን ጉዳይ በኢትዮጵያ ውስጥ አደባባይ ለማውጣት ጊዜው የደረሰ ይመስለኛል፤ አረጋዊ በርሄ፣ ገብረ መድኅን አርአያ፣ አስገደ ገብረ ሥላሴ፣ አብርሃ ደስታ (አሥር ቢሞሉልኝ ደስ ይለኝ ነበር!) እየደጋገሙ ቢያነሡትም ሌሎች በቁም-ነገር የተቀበሉት አይመስልም፤ ሕዝቡ ግን በራሱ መንገድ እየተናገረና ምስክርነቱን እየሰጠ ነው፤ በመቀሌ የተሠራውን የመኳንንት መንደር ሕዝቡ አፓርቴይድ ብሎ ሲሰይመው፣ በአዲስ አበባ የተሠራውን መንደር መቀሌ ብሎ ሲሰይመው እየመሰከረ ነው፤ ‹‹የለሁበትም!›› እያለ ነው።

የትግራይ ሕዝብ መደህየቱ አልበቃ ብሎት ሲለምንም እየተሳቀቀ ነው፤ የሚለምነው ትግሬ ለብዙ ሰዎች ትግሬና ወያኔ አንድ መስሎ እንደሚታየው ያውቃል፤ አብዛኛው ሰው በወያኔ ላይ ያለውን ስሜት ያውቃል፤ ስለዚህም ሲለምን ሰዎች በወያኔ ላይ ያላቸውን ስሜት ስለሚያራግፉበት እየተሸማቀቀ ነው፤ አንድ የትግራይ ቄስ ከአርሲ ነኝ አሉኝና ለምን እውነቱን አይናገሩም ስላቸው እውነቱን ስናገር የማገኘው ስድብ ብቻ ነው አሉኝ፤ እኒህ ሰው ምን በወጣቸው የወያኔን ኃጢአት ተሸካሚ ይሆናሉ፤ በሌላ በኩል ደግሞ በትግሬነቱ የተጠቀመ አለ፤ እኔ የማውቀው የደርግ ወታደር የነበረ ትግሬ ቆስሎ ከውትድርና ወጣና በአንድ የመንግሥት መሥሪያ ቤት የጥበቃ ሥራ ላይ ነበር፤ በጣም ይቸግረው ነበር፤ ሚስቱ ሕመምተኛ ነበረች፤ የቤት ኪራይ መክፈል ይቸገር ነበር፤ ዛሬ ግን የሚለብሰው ልብስ ሌላ ነው፤ ከኑሮውም ተርፎ ለሲጃራና ለጫት እያወጣ ነው፤ ወይም ሌሎች እያወጡለት ነው፤ ትግሬነታቸው ብቻ እንዲህ የደላቸው በጣም፣ በጣም ጥቂቶች ናቸው፤ ስለዚህም በወያኔ አገዛዝ ትግሬ ሁሉ ተጠቅሞአል ማለት ከጉልሁ እውነት ጋር የሚጋጭ ስሕተት ነው፤ አብርሃ ሰዎች ትግሬ ሁሉ ተጠቃሚ ሆኗል ሲሉ ‹‹ያመኛል›› ማለቱ ይገባኛል።
ወያኔ ትግሬ በመሆኑ ብቻ ትግሬ ሁሉ ዕዳ አለበት ማለት እንደወያኔ ማሰብ ነው፤ ወንጀል በዘር አይተላለፍም፤ እያንዳንዱ ሰው ለሠራው ሥራ ሁሉ ኃላፊነትን ይወስዳል፤ ጊዜው ሲደርስ ውጤቱንም ለመቀበል ይገደዳል፤ ይህ የሚሆነው ሰው ሁሉ በመንፈሳዊ ኃይል በጎ መንፈስ አድሮበት፣ አእምሮው በትምህርት ተገርቶ በትክክል ማሰብ ሲችል ነው፤ የኢትዮጵያ ሕዝብ አሁን በአለበት ሁኔታ በጎ መንፈስ የራቀው ይመስላል፤ አእምሮም ጭራሹኑ በእኩይ መንፈስና በጥላቻ እየዛገ ነው፤ ስለዚህ ያስፈራል፤ በደቡብ ሱዳን ሁለት መቶ ሰዎች በዘር ተለይተው ታረዱ ሲባል ያስፈራል፤ በናይጂርያ፣ በኮንጎ የሚካሄደውን የዘርና የሃይማኖት እልቂት ስንሰማ ያስፈራል፤ በ1997 ዓ.ም. መለስ ዜናዊና አዲሱ ለገሰ እንዳስታወሱን የሩዋንዳ የጎሣ እልቂት በብዙ ሰዎች አእምሮ ውስጥ አለ፤ የቅርብ ተኳሽ የሆነው የአግዓዚ ጦርም አድፍጦ መጠበቅ ያስፈራል፤ ሌላውም ይህንን አውቆ አድፍጦ መጠበቁ ያስፈራል፤ ሰማይ ጠቀስ የሠሩት፣ የሥልጣን ኃላፊነትን ችላ ብለው በሥልጣን የሚነግዱና የሚከብሩት፣ የማይኖሩበትን ሕንጻ የሚክቡት፣ ከሕዝብ ጋር ያላቸው የአይጥና የድመት ኑሮ ያስፈራል፤ አቶ አስገደ ወያኔ መደንገጡን ይነግረናል፤ መደንገጥ የማይቆጣጠሩት ፍርሃት ነውና አደጋ ያመጣል፤ አደጋው አደጋን ይጠራል፤ ይህም ያስፈራል።
በትግራይ ዙሪያ ያለው ምንድን ነው? የትግራይ ሕዝብ በየትኛው አቅጣጫ ነው አንደልቡ እየተዘዋወረ ለመሥራትና ለመኖር የሚችለው? ወያኔ የትግራይን ሕዝብ ከሰሜን ከወገኑ ከኤርትራ ሕዝብ ጋር ደም አቃብቶታል፤ በደቡብ-ምሥራቅ ከወሎ መሬት ቆርሶ የወሎን ሕዝብ ቂም አስቋጥሯል፤ በደቡብ-ምዕራብ ከጎንደር መሬት ቆርሶ የጎንደርን ሕዝብ ቂም አስቋጥሯል፤ የራስን ወገኖች አስቀይሞ ሱዳንን በመሬት ለመደለል የሚደረገው ጥረት ሁሉ ፋይዳ የለውም፤ ሱዳን ለራሱም ያልበጀ አገር መሆኑ እየታየ ነው፤ ወደፊት ደግሞ ይበልጥ ይታያል፤ በትግራይ ውስጥ ደግሞ ወያኔ የፈጠረው አፓርቴይድ የወያኔን የኑሮ ደረጃ ወደሰማይ ሲያስጠጋው፣ የቀረውን ወደአንጦርጦስ የደሀነት ገደል ውስጥ ከቶታል፤ በዚህም ምክንያት በአዲስ አበባ ከተማ ከነልጆቻቸው እየተዘዋወሩ የሚለምኑ ሞልተዋል፤ ይህ ልመናም ለወያኔ ለመገበር ነው፤ ብዙዎቹ እንደሚናገሩት የሚለምኑት የማዳበሪያ ዕዳቸውን ለወያኔ ለመክፈል ነው።
ወያኔ ከሀያ ዓመታት በላይ አፍንጫ እየያዘ ያስከፈለውን የሚመልስበት ጊዜ እየተቃረበ ነው፤ ጥያቄው ወያኔ እንዲመልስ የሚገደደው እንዴት ነው? የሚል ነው፤ጥላቻ ወደንዴት፣ ንዴት ወደቁጣ ተለውጦ ሲገነፍል ምጽዓት ደረሰ ማለት ነው፤ ሁሉምሰው ራቁቱን ይሆናል፤ አንደአውሬ ከጥፍሩና ከጥርሱ በቀር ሌላ መሣሪያ አይኖረውም፤ ሰው ሁሉ በክፋት ወደአውሬነት ይለወጣል፤ ጠመንጃና ቦምብ አያገለግሉም፤ ሕንጻው ምሽግ አይሆንም፤ መኪናው፣ ባቡሩ፣ ታንኩ ከቆመበት አይነቃነቅም፤ የትም አያደርስም፤ ጭፍራ ሁሉ በየራሱ ፍዳ ታንቆ እንኳን ለሌላ ሊተርፍ ለራሱም የማይበቃ ይሆናል፤ ለነገሩ ጌታና ሎሌም የለም፤ ሁሉም በአውሬ እኩልነት የተፋጠጠ ነው፤ ርኅራኄ ተሟጦ፣ መግል ያዘለ ልብ ፈርጦ፣ ውይይትና ክርክር አብቅቶ፣ ጥርሱን ያገጠጠና ጥፍሩን የሳለ መንጋ በደም የሚራጭበት ሁኔታ ነው።

የወያኔ ጥላቻ ፍሬ (ፕ/ር መስፍን ወልደ ማርያም)

May 11/2014

ወያኔ ለትግራይ ሕዝብ ሀብትንና ብልጽግናን አመጣ ብለው የሚያምኑ ሰዎች ብዙ ናቸው፤ ወያኔ የሥልጣን ወንበሩ ላይ በመውጣቱ ትግሬዎች ሁሉ አልፎላቸዋል ተብሎ ይታመናል፤ በተለይ በአውሮፓና በአሜሪካ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን በዚህ ላይ የጠነከረ እምነት አላቸው፤ በዚህ ጉዳይ ላይ ከኢትዮጵያ ውጭ ብዙ ውይይትም ይሁን ንትርክ ይደረጋል፤ በኢትዮጵያ ውስጥ ግን የተፈራ ርእስ ነው፤ ውስጥ-ውስጡን እንጂ አደባባይ አይወጣም፤ ይህንን ጉዳይ በኢትዮጵያ ውስጥ አደባባይ ለማውጣት ጊዜው የደረሰ ይመስለኛል፤ አረጋዊ በርሄ፣ ገብረ መድኅን አርአያ፣ አስገደ ገብረ ሥላሴ፣ አብርሃ ደስታ (አሥር ቢሞሉልኝ ደስ ይለኝ ነበር!) እየደጋገሙ ቢያነሡትም ሌሎች በቁም-ነገር የተቀበሉት አይመስልም፤ ሕዝቡ ግን በራሱ መንገድ እየተናገረና ምስክርነቱን እየሰጠ ነው፤ በመቀሌ የተሠራውን የመኳንንት መንደር ሕዝቡ አፓርቴይድ ብሎ ሲሰይመው፣ በአዲስ አበባ የተሠራውን መንደር መቀሌ ብሎ ሲሰይመው እየመሰከረ ነው፤ ‹‹የለሁበትም!›› እያለ ነው።

የትግራይ ሕዝብ መደህየቱ አልበቃ ብሎት ሲለምንም እየተሳቀቀ ነው፤ የሚለምነው ትግሬ ለብዙ ሰዎች ትግሬና ወያኔ አንድ መስሎ እንደሚታየው ያውቃል፤ አብዛኛው ሰው በወያኔ ላይ ያለውን ስሜት ያውቃል፤ ስለዚህም ሲለምን ሰዎች በወያኔ ላይ ያላቸውን ስሜት ስለሚያራግፉበት እየተሸማቀቀ ነው፤ አንድ የትግራይ ቄስ ከአርሲ ነኝ አሉኝና ለምን እውነቱን አይናገሩም ስላቸው እውነቱን ስናገር የማገኘው ስድብ ብቻ ነው አሉኝ፤ እኒህ ሰው ምን በወጣቸው የወያኔን ኃጢአት ተሸካሚ ይሆናሉ፤ በሌላ በኩል ደግሞ በትግሬነቱ የተጠቀመ አለ፤ እኔ የማውቀው የደርግ ወታደር የነበረ ትግሬ ቆስሎ ከውትድርና ወጣና በአንድ የመንግሥት መሥሪያ ቤት የጥበቃ ሥራ ላይ ነበር፤ በጣም ይቸግረው ነበር፤ ሚስቱ ሕመምተኛ ነበረች፤ የቤት ኪራይ መክፈል ይቸገር ነበር፤ ዛሬ ግን የሚለብሰው ልብስ ሌላ ነው፤ ከኑሮውም ተርፎ ለሲጃራና ለጫት እያወጣ ነው፤ ወይም ሌሎች እያወጡለት ነው፤ ትግሬነታቸው ብቻ እንዲህ የደላቸው በጣም፣ በጣም ጥቂቶች ናቸው፤ ስለዚህም በወያኔ አገዛዝ ትግሬ ሁሉ ተጠቅሞአል ማለት ከጉልሁ እውነት ጋር የሚጋጭ ስሕተት ነው፤ አብርሃ ሰዎች ትግሬ ሁሉ ተጠቃሚ ሆኗል ሲሉ ‹‹ያመኛል›› ማለቱ ይገባኛል።

ወያኔ ትግሬ በመሆኑ ብቻ ትግሬ ሁሉ ዕዳ አለበት ማለት እንደወያኔ ማሰብ ነው፤ ወንጀል በዘር አይተላለፍም፤ እያንዳንዱ ሰው ለሠራው ሥራ ሁሉ ኃላፊነትን ይወስዳል፤ ጊዜው ሲደርስ ውጤቱንም ለመቀበል ይገደዳል፤ ይህ የሚሆነው ሰው ሁሉ በመንፈሳዊ ኃይል በጎ መንፈስ አድሮበት፣ አእምሮው በትምህርት ተገርቶ በትክክል ማሰብ ሲችል ነው፤ የኢትዮጵያ ሕዝብ አሁን በአለበት ሁኔታ በጎ መንፈስ የራቀው ይመስላል፤ አእምሮም ጭራሹኑ በእኩይ መንፈስና በጥላቻ እየዛገ ነው፤ ስለዚህ ያስፈራል፤ በደቡብ ሱዳን ሁለት መቶ ሰዎች በዘር ተለይተው ታረዱ ሲባል ያስፈራል፤ በናይጂርያ፣ በኮንጎ የሚካሄደውን የዘርና የሃይማኖት እልቂት ስንሰማ ያስፈራል፤ በ1997 ዓ.ም. መለስ ዜናዊና አዲሱ ለገሰ እንዳስታወሱን የሩዋንዳ የጎሣ እልቂት በብዙ ሰዎች አእምሮ ውስጥ አለ፤ የቅርብ ተኳሽ የሆነው የአግዓዚ ጦርም አድፍጦ መጠበቅ ያስፈራል፤ ሌላውም ይህንን አውቆ አድፍጦ መጠበቁ ያስፈራል፤ ሰማይ ጠቀስ የሠሩት፣ የሥልጣን ኃላፊነትን ችላ ብለው በሥልጣን የሚነግዱና የሚከብሩት፣ የማይኖሩበትን ሕንጻ የሚክቡት፣ ከሕዝብ ጋር ያላቸው የአይጥና የድመት ኑሮ ያስፈራል፤ አቶ አስገደ ወያኔ መደንገጡን ይነግረናል፤ መደንገጥ የማይቆጣጠሩት ፍርሃት ነውና አደጋ ያመጣል፤ አደጋው አደጋን ይጠራል፤ ይህም ያስፈራል።

በትግራይ ዙሪያ ያለው ምንድን ነው? የትግራይ ሕዝብ በየትኛው አቅጣጫ ነው አንደልቡ እየተዘዋወረ ለመሥራትና ለመኖር የሚችለው? ወያኔ የትግራይን ሕዝብ ከሰሜን ከወገኑ ከኤርትራ ሕዝብ ጋር ደም አቃብቶታል፤ በደቡብ-ምሥራቅ ከወሎ መሬት ቆርሶ የወሎን ሕዝብ ቂም አስቋጥሯል፤ በደቡብ-ምዕራብ ከጎንደር መሬት ቆርሶ የጎንደርን ሕዝብ ቂም አስቋጥሯል፤ የራስን ወገኖች አስቀይሞ ሱዳንን በመሬት ለመደለል የሚደረገው ጥረት ሁሉ ፋይዳ የለውም፤ ሱዳን ለራሱም ያልበጀ አገር መሆኑ እየታየ ነው፤ ወደፊት ደግሞ ይበልጥ ይታያል፤ በትግራይ ውስጥ ደግሞ ወያኔ የፈጠረው አፓርቴይድ የወያኔን የኑሮ ደረጃ ወደሰማይ ሲያስጠጋው፣ የቀረውን ወደአንጦርጦስ የደሀነት ገደል ውስጥ ከቶታል፤ በዚህም ምክንያት በአዲስ አበባ ከተማ ከነልጆቻቸው እየተዘዋወሩ የሚለምኑ ሞልተዋል፤ ይህ ልመናም ለወያኔ ለመገበር ነው፤ ብዙዎቹ እንደሚናገሩት የሚለምኑት የማዳበሪያ ዕዳቸውን ለወያኔ ለመክፈል ነው።

ወያኔ ከሀያ ዓመታት በላይ አፍንጫ እየያዘ ያስከፈለውን የሚመልስበት ጊዜ እየተቃረበ ነው፤ ጥያቄው ወያኔ እንዲመልስ የሚገደደው እንዴት ነው? የሚል ነው፤ጥላቻ ወደንዴት፣ ንዴት ወደቁጣ ተለውጦ ሲገነፍል ምጽዓት ደረሰ ማለት ነው፤ ሁሉምሰው ራቁቱን ይሆናል፤ አንደአውሬ ከጥፍሩና ከጥርሱ በቀር ሌላ መሣሪያ አይኖረውም፤ ሰው ሁሉ በክፋት ወደአውሬነት ይለወጣል፤ ጠመንጃና ቦምብ አያገለግሉም፤ ሕንጻው ምሽግ አይሆንም፤ መኪናው፣ ባቡሩ፣ ታንኩ ከቆመበት አይነቃነቅም፤ የትም አያደርስም፤ ጭፍራ ሁሉ በየራሱ ፍዳ ታንቆ እንኳን ለሌላ ሊተርፍ ለራሱም የማይበቃ ይሆናል፤ ለነገሩ ጌታና ሎሌም የለም፤ ሁሉም በአውሬ እኩልነት የተፋጠጠ ነው፤ ርኅራኄ ተሟጦ፣ መግል ያዘለ ልብ ፈርጦ፣ ውይይትና ክርክር አብቅቶ፣ ጥርሱን ያገጠጠና ጥፍሩን የሳለ መንጋ በደም የሚራጭበት ሁኔታ ነው።

ሌላ አገር እንዲህ አልሆነም፤ እዚያ አገር እንዲህ አልሆነም፤ የሚባል ነገር የለም፤ እኛ ዘንድ ሌላ ነው፤ የኢትዮጵያ ደሀዎች እንባ የእግዚአብሔርን ሰማይ አጨቀየው!

ክፋት እንደእሳት ይቃጠላል፤ ኵርንችቱንና እሾሁን ይበላል፤ ጭፍቅ የሆነውንም ዱር ያቃጥላል፤ ጢሱም ተትጐልጕሎ እንደዓምድ ይወጣል፤ በሠራዊት ጌታ በእግዚአብሔር ቁጣ ምድር ተቃጥላለች፤ ሕዝቡም እሳት እንደሚበላው እንጨት ሆኖአል፤ ሰውም ለወንድሙ አይራራም፤ ሰው በቀኙ በኩል ይነቅላል፤ ይራብማል፤ በግራም በኩል ይበላል፤ አይጠግብምም፤ እያንዳንዱም የክንዱን ሥጋ ይበላል፤ ምናሴ ኤፍሬምን፣ ኤፍሬምም ምናሴን ይበላል፤… ኢሳይያስ 9/18-21

ትንቢተ ኢሳይያስ ለሩዋንዳውያን ብቻ አይደለም፤ ጥላቻና ክፋት በተዘራበት ቦታ ሁሉ ውጤቱ ጥፋት ነው፤ ምናሴ ኤፍሬምን በልቶ አይቀርም፤ ኤፍሬምም ምናሴን ይበላዋል።

የኢትዮ-ሱዳን ድንበር ክለላ ዛሬ በድብቅ ሊፈረም ነው! – አብርሃ ደስታ

የኢትዮ ሱዳን ዳር ድንበር በግልፅ የተከለለ እንዳልሆነ ይታወቃል። የኢትዮጵያ አርሶአደሮች የሚጠቀሙት መሬት የኢትዮጵያ እንደሆነ ሲወሰድ ሱዳናውያን የሚገለገሉበትም የሱዳን ነው ተብሎ ይታሰባል። ከቅርብ ግዜ ወዲህ ግን የኢህአዴግ መንግስት ኢትዮጵያውያን አርሶአደሮችን ከቀያቸው እያፈናቀለ ለሱዳን ማስረከቡ ይታወቃል። ብዙ የኢትዮጵያ አርሶአደሮች ተፈናቅለዋል፣ የተወሰኑ ተለዋጭ መሬት ሲሰጣቸው ምንም ያላገኙም አሉ።
SUDANድንበሩ ብዙ ዉዝግብና ተቃውሞ ያለው ሲሆን የኢህአዴግ መንግስት ከሱዳኖች ጋር በመተባበር በድብቅ ለመከለል ተስማምቷል። እንዲህ ነው የተደረገው፥ በድንበሩ አከባቢ የሚገኙ ኗሪዎች (የኢትዮጵያና የሱዳን) ድንበራቸውን አይተው ክለላውን ይፈፅማሉ፣ ይፈራረማሉ። ለሱዳን የተሰጠው መሬት ታውቋል። ሁሉም ነገር በኢህአዴግና የሱዳን መንግስት አልቋል። አሁን “የሀገር ሽማግሌዎች” እንዲፈርሙ እየተደረገ ነው። የሀገር ሽማግሌዎች እንዲፈርሙ የተፈለገበት ምክንያት የድንበር ክለላ የተከናወነው በኗሪዎች ነው እንዲባል ነው። ለሌላ ግዜም ምስክር ሁነው እንዲቀርቡ ነው።
በዚህ መሰረት በድንበሩ አከባቢ ከሚገኙ የኢትዮጵያ ከተሞች ማይካድራና በረከት የተወሰኑ ሰዎች በካድሬዎች ተመርጠው “ኮሚቴ” ተሰኝተው ዛሬ ግንቦት 8, 2006 ዓም እንዲፈርሙ ወደ ሱዳን ድንበር ተጉዘዋል። እነዚህ ኮሚቴ ተብለው የተመረጡ ሰዎች ስለ ድንበሩ ይሁን አከባቢው እውቀት የሌላቸው፣ የአከባቢው ኗሪዎች ሳይሆኑ በቅርብ ግዜ ባከባቢው መሬት የተሰጣቸው ሰፈርተኞች ናቸው። ዕድሜየቸውም ከአርባ በታች ነው፣ ትምህርት የላቸውም፣ የድንበሩ ታሪክ አያውቁም፣ መሬት ስለተሰጣቸውና በካድሬዎች ስለታዘዙ ብቻ ሊፈርሙ የሚችሉ ናቸው። ስለዚህ የሀገር ሽማግሌዎች ሊባሉ አይችሉም። ምክንያቱም ሰፈርተኞች እንጂ ኗሪዎች አይደሉም፣ ወጣቶች ናቸው (ድንበሩ ላያውቁት ይችላሉ)፣ ትምህርት የላቸውም (የድንበር ጉዳይ ምን ያህል ጥንቃቄ የሚያስፈልገው እንደሆነ ላይረዱ ይችላሉ) ወዘተ። ዛሬ እንዲፈርሙ የተወሰዱት በድብቅ መሆኑ ነው።
SUDAN
የድንበር ጉዳይና ሌሎች የሑመራ አከባቢ ኗሪዎች በማየሉ ተቃውሞ እየተቀሰቀሰ በመሆኑ ባከባቢው ተገኝቶ መረጃ ማሰባሰብ አስቸጋሪ እየሆነ ነው። የመንግስት አካላት ኗሪዎች ለሌሎች አካላት መረጃ እንዳይሰጡ እያስፈራሩ ነው። መረጃ መሰብሰብም አይፈቀድም። በዚሁ አጋጣሚ ግርማይ ወልደግዮርግስ የተባለ የድምፂ ወያነ ሬድዮ ጋዜጠኛ ባስተዳዳሪዎች ከቀረቡለት አራት ካድሬዎች ዉጭ ሌሎች ኗሪዎችን በማነጋገሩ ምክንያት ባለስልጣናት ፖሊስ ጠርተው አስረውታል። የድምፂ ወያነ ሬድዮ ጋዜጠኛ ህዝብን ሳንፈቅድልህ አገጋግረሃል ተብሎ ነው የታሰረው።
በሑመራ አከባቢ ብዙ ተደራራቢ ችግሮች አሉ። ሕገወጥ የመሬት ሽንሸና እየተደረገ ነው። ኗሪዎችን ከቀያቸው እየተፈናቀሉ ስርዓቱ ያገለግላሉ ለተባሉ ሰዎች መሬት እየተሰጠ ይገኛል። ለምሳሌ አቶ ካሕሳይ ገብረሚካኤል የተባሉ ያከባቢው ኗሪ መሬታቸው ተወስዶ ለሌላ የህወሓት ካድሬ ዉሽማ ተሰጥቷል። ፍትሐዊ ያልሆነ እርምጃ እየተወሰደ ይገኛል።
በድንበሩ ጉዳይ በድብቅ እየተፈረመ ያለው ነገር ተቀባይነት የለውም። ለሱዳን የሚሰጥ መሬት መኖር የለበትም። ተግባሩ ሕገወጥ ነው። ኢህአዴግም ለተግባሩ ይጠየቃል።

Wednesday, May 14, 2014

መሠረታዊ የአገልግሎት ማሻሻያ ፕሮግራም የክልልና የፌደራል መንግሥታትን አከራከረ May14/2014

-ለጋሾች በበጀት አጠቃቀም ላይ ጥያቄ እያነሱ ነው
የመሠረታዊ አግልግሎቶች ማሻሻያ ፕሮግራም በኢትዮጵያ መተግበር የጀመረው ከ1997 ዓ.ም. ምርጫ ማግሥት ለጋሽ አገሮች መንግሥት ላይ ባሳደሩት ጫና ነበር፡፡
በተለይ የአውሮፓ ኅብረት ከምርጫው ማግሥት በኋላ በተፈጠረው አለመረጋጋት ሳቢያ መንግሥትን በመኮነን ለአንድ ዓመት ያህል ዕርዳታ ከመስጠት ታቅቦ ቆይቶ ነበር፡፡

ሆኖም ለጋሽ አገሮች በቀጥታ ድሀ ተኮር የሆኑ ፕሮግራሞች በአግባቡ ስለመተግበራቸው እርግጠኛ ለመሆን፣ በጋራ ከማቀድ ጀምሮ አፈጻጸማቸውና ያስገኙትን ውጤት በጋራ መገምገም የሚያስችላቸውን መድረክ ከመንግሥት ጋር በመፍጠር ባለፉት ሦስት ዓመታት፣ በያመቱ የአሥር ቢሊዮን ብር ዕርዳታ ሲሰጡ ቆይተዋል፡፡

ለሦስተኛ ጊዜ የተተገበረውንና በ2005 ዓ.ም. የተጠናቀቀውን የመሠረታዊ አገልግሎቶች ማሻሻያ ፕሮግራም የግማሽ ዓመት የበጀትና ዕርዳታ አፈጻጸም ግምገማ ከለጋሽ አገሮች ጋር በግዮን ሆቴል ማካሄድ የተጀመረው ሰኞ ግንቦት 4 ቀን 2006 ዓ.ም. ሲሆን፣ በመጪው ግንቦት 8 እንደሚጠናቀቅ ይጠበቃል፡፡

በግምገማው መክፈቻ ወቅት የገንዘብና ኢኮኖሚ ልማት ሚኒስቴር ይፋ እንዳደረገው የመሠረታዊ አገልግሎቶች ማሻሻያ ፕሮግራም በጤና፣ በትህምርት፣ በግብርና፣ በውኃና በመንገድ ንዑስ ዘርፎች ላይ ለጋሾች ለአፈጻጸማቸው የገንዘብ ድጎማ ያደርጋሉ፡፡ የሠራተኞችን ደመወዝ፣ የሥራ ማስኬጃ በጀትና ሌሎች ወቅታዊ በጀት የሚያካትታቸውን የፕሮግራሙን ወጪዎችን ይደጉማሉ፡፡ በተለይም በሰው ኃይልና በአስተዳዳራዊ ዘርፎች፣ በፋይናንስና በጀት ግልጽነትና ተጠያቂነት ላይ ያተኩራሉ፡፡ በመሠረታዊ አግልግሎቶች ማሻሻያ ፕሮግራም ላይ  እስካሁን የታዩ ለውጦች ጥሩ የሚባሉ ቢሆኑም፣ በታዳጊ ክልሎች የተመዘገቡት ለውጦች ከታቀደው በታች ነው በማለት መረጃዎችን አቅርቧል፡፡

ከዕድገትና ትራንስፎርሜሽን ዕቅዱ ተውጣጥቶ የቀረበው የ2005 በጀት ዓመት የመሠረታዊ አገልግሎቶች ማሻሻያ ፕሮግራም ውጤቶች ሪፖርት ላይ ጥቂት የማይባሉ መስኮች ላይ ከታቀደው በታች ውጤት መመዝገቡን ቢገልጽም፣ ክልሎች ሳይቀበሉት ቀርተዋል፡፡

በትምህርት መስክ በአንደኛ ደረጃ የትምህርት ሽፋን ላይ የተመዘገቡትን ውጤቶች በማስመልከት ገንዘብና ኢኮኖሚ ልማት ሚኒስቴር እንዳቀረበው፣ ባለፈው በጀት ዓመት ከአንደኛ እስከ ስምንተኛ ክፍል የተመዘገው የተጣራ የተማሪዎች ቁጥር 86 ከመቶ አቅራቢያ ነው፡፡ በዕቅድ ይመዘገባል የተባለው መጠን ግን 94 ከመቶ ገደማ ነው፡፡ ይህም ማለት በመላ አገሪቱ ከአንድ እስከ ስምንት የሚሰጠው የትምህርት አገልግሎት ሽፋን 94 ከመቶ ይደርሳል የሚል ነበር፡፡ ከአምስተኛ እስከ ስምንተኛ ክፍል ባለው የትምህርት ዕርከንም ይጠበቅ የነበረው የተማሪ ቁጥር 69 ከመቶ አቅራቢያ ሲሆን፣ በተጨባጭ የተመዘገበው ግን 47 ከመቶ በመሆኑ ከዕቅዱ በብዙ ርቆ ታይቷል፡፡ የስምንተኛ ክፍልን የሚያጠናቅቁ ተማሪዎች ቁጥር በአገር አቀፍ ደረጃ 53 ከመቶ አቅራቢያ ሲሆን፣ ይጠበቅ የነበረው ግን 78 ከመቶ ይደርሳል ተብሎ ነበር፡፡

ከ86 ከመቶው አገራዊ አማካይ ውጤት በታች ውጤት አስመዝግበዋል የተባሉት ክልሎች፣ አፋር ክልል 42 ከመቶ በማስመዝገብ ዋናው ሲሆን፣ አዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር 69 ከመቶ፣ ሐረሪ ክልል 75 ከመቶ በማስዝገብ ወደኋላ መቅረታቸው ተመልክቷል፡፡ ከዚህ ባሻገር በመምህራን ሥልጠናና ብቃት ላይም አማራ፣ አፋር፣ ሶማሌና ደቡብ ሕዝቦች በዝቅተኛ ደረጃ ውጤት ያሳዩ ተብለው ተተችተዋል፡፡

የቀረቡትን አኃዞች የአዲስ አበባ አስተዳደርም ሆነ የአፋርና የሶማሌ ክልሎች አጣጥለዋል፡፡ የአፋር ክልል ያጣጣለው የራሱን መረጃ በማጣቀስ ሲሆን፣ በክልሉ የሠለጠኑ የአንደኛ ደረጃ መምህራን ቁጥር 95 ከመቶ ደርሶ እያለ ገንዘብና ኢኮኖሚ ልማት ሚኒስቴር 53 ከመቶ አቅራቢያ ነው ማለቱ ከምን በመነሳት እንደሆነ እንዲገለጽለት ጠይቋል፡፡ የአዲስ አበባ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ በበኩሉ በተማሪዎች ቁጥር ላይ ያለበትን ችግር ይፋ አድርጓል፡፡ ለአንደኛ ደረጃ ትምህርት ዕድሜያቸው የደረሱ ሕፃናት ትምህርት የሚጀምሩት በሰባተኛ ዓመታቸው ነው፡፡ ቢሮው አንደኛ ደረጃ ትምህርታቸውን የሚያጠናቅቁበት ዕድሜም 14 ዓመት መሆኑን ገልጾ፣ በአዲስ አበባ ከሚገኙ አንደኛ ደረጃ ተማሪዎች ውስጥ 40 ከመቶው በግል ትምህርት ቤቶች የሚማሩና ከተቀመጠው የትምህርት ዕድሜ በታች የአንደኛ ደረጃ ትምርትን የሚጀምሩና የሚያጠናቅቁ በመሆናቸው፣ ስታቲስቲካዊ መረጃ አያያዝ ላይ መቸገሩን አመልክቷል፡፡

በግል ትምህርት ቤቶች ውስጥ የሚማሩት ሕፃናት አንደኛ ደረጃ ትምህርት የሚጀምሩት በስድስት ዓመታቸው ሲሆን፣ የሚያጠናቅቁትም በ13ኛ ዓመታቸው ነው፡፡ ይህንን የገለጸው የአዲስ አበባ ትምህርት ቢሮ፣ ከዚህ ባሻገርም ከመደበኛው የትምህርት ዕድሜ በላይ የሆኑ ታዳጊዎች በማታው ክፍለ ጊዜ ትምህርታቸውን የሚከታተሉ በመሆኑ እነሱም የሚያካትት አኃዝ እንዳልቀረበ ይፋ አድርጓል፡፡

የትምትርት ሚኒስቴር ዴኤታ አቶ ፉአድ ኢብራሒም በበኩላቸው በአሁኑ ወቅት 22 ሚሊዮን ተማሪዎች በአገሪቱ እንደሚገኙ ገልጸው፣ ሁለት ሚሊዮን አዲስ ተማሪዎች ወደ ትምህርት ገበታው መምጣት እንደቻሉ ተናግረዋል፡፡ ትምህርት ማቋረጥና መቅረት አሳሳቢ መሆኑን ያመኑት አቶ ፉአድ፣ ይህም ሆኖ በመረጃ አሰባሰብ ላይ ከማዕከላዊ ስታቲስቲክስ ኤጀንሲ ጋር ልዩነት እየታየ በመሆኑ የአኃዝ ተቃርኖ መፈጠሩን ገልጸዋል፡፡ ኤጀንሲው የሚሰበስበው መረጃ በቤሰተብ ደረጃ ሲሆን ትምህርት ሚኒስቴር ግን ከየትምርት ቤቶቹ መረጃ የሚሰበስብ በመሆኑ በመረጃ ምንጭ ላይ ያለው ልዩነት ችግር እየፈጠረ መሆኑን አስታውቀዋል፡፡ በአዲስ አበባ ትምህርት ቢሮ ከቀረበው የዕድሜ ጉዳይ በተጨማሪ 44 ትምህርት ቤቶች ለግምገማው አለመካተታቸውን አቶ ፉኣድ ተናግረዋል፡፡

በግብርና በኩል የታየው ችግር በኤክስቴንሽን ሠራተኞች ቁጥር ላይና በምርታማነት ላይ ያተኮረ ነው፡፡ ባለፈው ዓመት በሔክታር ይጠበቅ የነበረው ምርት ከ19 ኩንታል በላይ ቢሆንም፣ ውጤቱ ግን በሔክታር 18 ኩንታል አልሞላም፡፡ በዋና ዋና ሰብሎች ላይ የታየው አዝጋሚ ምርታማነት በዕድገትና ትራንስፎርሜሽን ዕቅዱ መሠረት ወደ ኋላ ሊቀር ችሏል ተብሏል፡፡ በዚህ አኃዝ ላይ ደስተኛ ያልሆኑት የግብርና ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታው አቶ ወንድይራድ ማንደፍሮ ያለፈው ዓመት መረጃ የዚህን ዓመት አፈጻጸም ሊገልጽ የማይችል ከመሆኑም በላይ፣ ባለፈው ላይ ከመነጋገር አሁን ባለው ላይ መወያየት እንደሚመርጡ ተናግረዋል፡፡ በዚያም ላይ ባለፈው ዓመት የተዘራው በዚህ ዓመት ውጤት የሚሰጥ በመሆኑ ምክንያት፣ ያለፈው ዓመት ዝቅተኛ ነው ብሎ መደምደም አስቸጋሪ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ በጤና በኩልም በጤና ኤክስቴንሽን ሠራተኞች ቁጥር ከጊዜ ወደ ጊዜ እያሽቆለቆለ መምጣት ላይ ሪፖርት ቀርቦ ጤና ጥበቃ ማብራሪያ ሰጥቷል፡፡ በድኅረ ወሊድ እንቅብካቤና በፀረ አምስት ሦስተኛ ዙር ክትባት አግልግሎት ላይም የታዩ ለውጦች ለቤቱ ቀርበዋል፡፡  ጤና ጥበቃ የመረጃ ጥራትና ብዛት፣ የአስተዳደር ችግር፣ ከታሰበው ዓላማ ማፈንገጥ የመሳሰሉት ችግሮች በክልሎች እያጋጠመው መሆኑን አስታውቋል፡፡

በመንገድ ዘርፍ ላይ የታውን በተመለከተ እንደቀረበውም ከዚህ በፊት በሁሉም ዓይነት የአየር ጠባይ የሚያገለግሉ መንገዶች ሽፋን እተሸሻለ መምጣቱ ታይቷል፡፡ ከአራት ዓመት በፊት ከነበረው ወደ እነዚህ መንገዶች ለመድረስ 3.7 ኪሎ ሜትር መንገድ መጓዝ ይጠይቅ የነበረ ሲሆን፣ ባለፈው ዓመት ወደ 2.1 ኪሎ ሜትር ዝቅ ማለቱ ተጠቁሟል፡፡ በጥሩ ደረጃ ላይ የሚገኙ መንገዶች ሽፋን 90 ከመቶ የደረሰ ሲሆን፣ በዕቅድ የሚጠበቀው ግን 85 ከመቶ ገደማ ነበር፡፡

ከገንዘብና ኢኮኖሚ ልማት ሚኒስቴር ባሻገር የእንግሊዝ ዓለም አቀፍ የልማት ትብብር ተቋም (ደፊድ)ም በበጀት፣ በፋይናንስ ግልጽነትና ተጠያቂነት እንዲሁም በሌሎች መስኮች ላይ ታይተዋል ያላቸውን ጉድለቶችና ጥሩ ውጤቶችን አስገኝተዋል ያላቸውን አፈጻጸሞች ገምግሟል፡፡

በኢትዮጵያ የዓለም ባንክ ዳይሬክተርና የለጋሽ አገሮች ተወካይ ጉዋንግ ዚ ቼን እንደተናገሩት፣ ምንም እንኳ ላለፉት ሦስት ዙሮች ሲተገበር የቆየው ፕሮግራም ለውጦችን ቢያስመዘግብም ችግሮች ግን አልተለዩትም፡፡ በመሠረታዊ አገልግሎት ማሻሻያ ፕሮግራሙ ላይ ከሚቀርቡ ዕቅዶች ውስጥ በበጀት አጠቃቀም ላይ የታዩ ችግሮች መኖራቸውን ጠቁመዋል፡፡ በመንገድ ዘርፉ ላይ የሚመደብ ፈንድ በአግባቡ ጥቅም ላይ አለመዋሉ፣ የሀብት አመዳደብ ችግር፣ የበጀት አደላደል፣ የመረጃ ምንጭ ላይ ችግሮች መኖራቸውን ጠቁመዋል፡፡ ጥራት ያለው መረጃ በወረዳና በቀበሌ ደረጃ ባሉ መዋቅሮች ላይ ማግኘት አስቸጋሪ መሆኑን የጠቆሙት ቼን፣ የአገልግሎት አሰጣጡ በሠራተኛው ላይ የሚንጠለጠል በመሆኑም የሰው ኃይል ላይ ትኩረት ሊደረግ ይገባል ብለዋል፡፡

በትምህርት፣ በጤና፣ በግብርናና በውኃ አቅርቦቶች ላይ የፌደራል መንግሥት ድጋፍ በሚሰጣቸው ታዳጊ ክልሎች ላይ ጎልቶ ታይቷል፡፡ ይህንን በተመለከተ ሪፖርተር ያነጋራቸው የዓለም ባንክ ዳይሬክተር፣ ክልሎቹ ራሳቸው ከዝቅተኛ ደረጃ ላይ እየተነሱ ያሉ በመሆኑ ነው ብለዋል፡፡

የገንዘብና ኢኮኖሚ ልማት ሚኒስትር ዴኤታ ዶክተር አብርሃም ተከስተ ምንም እንኳ የመሠረታዊ አገልግሎቶች አቅርቦት እየተሻሻለም ቢሆንም፣ ዕርዳታ ሰጪ አገሮች ቃል ከገቡት ውስጥ የተወሰነ መጠን እስካሁን እንዳልቀቁና በቀሩት ወራት ውስጥ በጀቱን እንዲለቁ አሳስበው ነበር፡፡ ስለዚህ ጉዳይ ሪፖርተር ጥያቄ ያቀረበላቸው ቼን በበኩላቸው አልተቀቀም የተባለው በጀት በዝቅተኛ አፈጻጸም ጋር የተያያዘ መሆኑን ይፋ አድርገዋል፡፡ በተለይ የተመደበው ገንዘብ እንዴትና በምን አኳኋን ሥራ ላይ እንደዋለ በአግባቡ መረጃ ስለማይገኝ፣ የሚሰጠው ዕርዳታ ሊዘገይ መቻሉን ቼን ተናግረዋል፡፡

በገንዘብና ኢኮኖሚ ልማት ሚኒስቴር የቻናል አንድ ፕሮግሞች አስተባባሪ አቶ ጌታቸው ነገራ ግን በታቀደው መሠረት ገንዘብ መለቀቁን ይናገራሉ፡፡ ለ2005/2006 በጀት ዓመት ፈሰስ ይደረጋል የተባለው በሙሉ ተለቅቋል ያሉት አቶ ጌታቸው፣ ከግንቦት ወር በኋላ መለቀቅ አለበት ተብሎ በሚጠበቀው የበጀት መጠን ላይ ያተኮረ ግምገማ እየተካሄደ መሆኑን ገልጸዋል፡፡ 

እናስራችኋለን? ለካንስ የነአጅሬ ጋጠወጥነት ከድንበርም ተሻግሯልና! May 14, 2014

President Salva Kir of Sudan
ነፃነት ዘለቀ (ከአዲስ አበባ)
በሀገራችን ባደመነው አጠቃላይ የሀዘን ድባብ ሳቢያ ፈገግታ እያማረኝ ፈገግ ለማለት ምንም ዕድል ሳላገኝ ብዙ ሰሞኖችን ባጀሁ፡፡ ዕድሜ ለዚህ ነገረኛ ኢሳት የሚባል ቴሌቪዥን ዛሬ ማታ ግና በሣቅ የሚያፈርስ ዜና ሰማሁና ምሽቱን ብቻ ሳይሆን ትዝ ባለኝ ቁጥር ሌቱን ሁሉ በሣቅ ስፈርስ አደርኩ – የግራ ጎን አጥንቶቼ ክፋይ ጉድ እስክትለኝ፡፡ ሣቅ ጥሩ ነው፡፡ አንዳንዴ በሣቅ የሚገድል ነገር ማግኘት የመታደል ያህል ነው፡፡ እውነተኛው ሣቅ ሞቶ ቢቀበርም ወያኔን መሰል ጅላንፎ ጉጅሌ የሚሠራቸው አንዳንድ ነገሮችን በመታዘብ ለጊዜውም ቢሆን ፈገግ መሰኘት ሲያስፈልግም ሆድን ያዝ አድርጎ በሣቅ መንፈርፈር ሰውነትን ያፍታታል፤ ወቅታዊ እፎይታንም ይሰጣል፡፡ እኔ – እውነቴን ነው – ለብዙ ጊዜ ያጣሁትን ሣቅ ዛሬ አገኘሁትና ከልቤ ተዝናናሁ፡፡ ወያኔ እኮ አልታወቀለትም እንጂ ደምበኛ የኮሜዲ መፍለቂያ ውድብ ነው፡፡ ልዩ የኢትዮጵያ ቻርሊ ቻፕሊን ሆነው የለም እንዴ!
ይህን የወያኔን ሞኝነት ጉዳዩ ለሚመለከተው የዓለም ክፍል ያንጸባረቀ ጉዳይ ለፖለቲካችን ቅርብ የሆነ ሰው ባያጣውም ለእንደኔ ዓይነቶች የማይሞላላቸው አንዳንድ ባዘኔዎች ማስታወሱ ደግ ይመስለኛል – ‹ቦዘኔ› እንዳላልኩ ይታወስልኝ፡፡ ብዙ ሰው እኮ የማይሞቀው የማይበርደው ሆኗል፡፡ ደንዘናል፤ በቁም ሞተናል፤ ‹ብታምኑም ባታምኑም› ብዙዎቻችን ከሰውነት ተራ ወጥተን የአምልኮተ ንዋይ ሰለባዎች ሆነናል፡፡ በሀገር ውስጥ ትንሽ ትልቁን ብታዩት ከሞላ ጎደል ሁሉም ሊባል በሚችል ሁኔታ ገንዘብ እንዴት ሊያገኝና በአቋራጭ ሊከብር እንደሚችል ሲጨነቅና ሲጠበብ ይታያል፡፡ ኅሊና ብሎ ነገር ጠፍቷል፡፡ ወንድም ወንድሙን፣ እህት እህቷን እስከመግደል በሚደርስ ሰይጣናዊ ጭካኔ ተሞልተን እየተፋጀን ነው፡፡ ወያኔ በቀደደው የጥፋት ጎዳና እየተመምን ከሰውነት ደረጃ በሚያስወጣ የሀብት ፍቅር ተነድፈን ልንጨራረስ የቀረን ጊዜ ሩብ ሐሙስ ቢሆን ነው፡፡ አልተነሳሁበትም እንጂ በዚህስ ትንሽ ባወራሁ፡፡
ወያኔም ባቅሙ አስታራቂና የሰላም አባት ሆኖ የደቡብ ሱዳን ተፋላሚዎችን በዕርቅ ለማስማማት አዲስ አበባ ይጠራቸዋል፡፡ ሳልቫኪር የሚሉት ባለባበሱና በዐይነ ውኃው ፊውዳላዊ አምባገነን የሚመስለኝ አማቻችን ሰውዬና ዶክተር ማቻር የሚባለው ሞገደኛ ሰውዬ ወደ አዲስ አበባ መጥተው (እንዳሁኑ ሁኔታ ደግሞ በመስፈራርቾ ተጠርተው) ሼራተን ሆቴል ሁለት ክፍሎች ውስጥ ይመሽጋሉ – ‹አማቻችን› ያልኩት የሳልቫኪር ይሁን የማቻር ልጅ የኛን ሀገር ልጅ እንዳገባ/ች በሚዲያ ስለሰማሁ ነው፡፡ ድርድሩም በወያኔ ጉጅሌ አማካይነት ተከናወነ ይባልና የዕርቁ ስምምነት ተፈረመ ተብሎ በወያኔው ቱሪናፋ ሚዲያዎች ይለፈፋል – (ከብቱ ወያኔ በሰሞኑ ጭፍጨፋው የጠለሸ ስሙን ያደሰ መስሎት በገባበት ወጥመድ የኋላ የኋላ ራሱ ገብቶበት ተተበተበበት እንጂ)፡፡ የወያኔ ኢትዮጵያ ለራሷ ብቻ ሣይሆን ለጎረቤት የሚተርፍ ሰላምና ዴሞክራሲ መጋዘኗ ውስጥ ጢም ብሎ እንዳለና ለሱዳንም፣ ለሶማሊያም፣ ለግብጽም፣ ለሦርያም፣ ለአፍጋኒስታንም፣ ለኢራቅም፣ ለቬንዝዌላም፣ ለ“ዴሞክራክ ሪፓብሊክ” ኮንጎም፣ ለሤንትራል አፍሪካ “ሪፓብሊክ”ም፣ ለሃይቲም፣ ለኡክሬንና ራሽያም፣ ለሰሜን ኮሪያም፣ ለ‹ኤርትራ›ም፣ ለሊቢያም፣ ለፓኪስታንም፣ ለበርማም፤ ለፍልስጥኤምም፣ (እንዴ፣ ዓለም ለካንስ በትርምስ ላይ ናትና ጎበዝ – የወያኔ የሰላም በረከት የሚላክላቸው ሁከት የነገሠባቸው ሀገሮች ዝርዝር አላልቅልኝ እኮ አለ!) ኤክስፖርት ለማድረግ ዝግጅቷን እንዳጠናቀቀች በነዚሁ በእውነት ዕርሙ የወያኔ ሚዲያዎች ከጥንፍ እስከ ጥንፍ ተስተጋባ፡፡ እኛም ይሄ የቤት ቀጋ የውጪ አልጋ የሆነ የወሮበሎች ቡድን ምን መተት ቢኖረው ይሆን እንዲህ ዓለምን ጉድ ባሰኘ መልክ የሰላም አባት ሊሆን የበቃው ብለን ተገረምን፡፡ የገዛ “ዜጎቹ”ን ባልተወለደ አንጀት እየጨፈጨፈና የስምንት ዓመት ሕጻን ሣይቀር ደረቱን በጥይት ዝናብ እየበሳሳ ባለበት ወቅት እንዲህ ያለ ሰላም ለሱዳናውያኑ ማስገኘቱ በርግጥም አንዳች ነገር አለው አልንና በጣም ተደነቅን፡፡ ኢትዮጵያችንም ስሟ ታደሰልን ብለን ደስ አለን – ደስታችን አንድ ጀምበር እንኳን ሳይዘልቅ ጠወለገብን እንጂ፡፡
ነገሩ ለካንስ ሌላ ኖሯል፡፡ ሳልቫኪር ሀገሩ እንደገባ ለሀገሩ መገናኛ ብዙኃንና ለባለሥልጣናቱ ሲናገር እንደተደመጠውና በሚዛናውያን ሚዲያዎች ሲዘገብ እንደተከታተልነው የሰላሙ ስምምነት የተፈረመው በወያኔ አስገዳጅነት ነበር፡፡ የአስገዳጅነቱ አካሄድም ነው በአስቂኝነቱ ወደር ያልተገኘለት፡፡
ከፍ ሲል እንደተገለጸው ወያኔ ሁለቱን ሰዎች ሼራተን ውስጥ በሁለት የተለያዩ ክፍሎች ያስቀምጣቸዋል፡፡ ፊት ለፊት ሳይገናኙም በተላላኪ ሃሳብ እንዲለዋወጡ ያደርጋል፡፡ መገናኘት ያልፈለጉት ምናልባት ራሳቸው ሊሆኑ እንደሚችሉ እንገምት፡፡ ወያኔ ግን የሁለቱ ሰዎች ያለመታረቅና ዕርቁን በፊርማ ያለማጽደቅ አዝማሚያ ሲገባው ያቺን የጫካ ህግ በመምዘዝ “ካልፈረማችሁ እዚሁ አስራችኋለሁ፤ ወደ ሀገራችሁ መሄድ ህልም እንደሆነባችሁ እንደነ እስክንድር ነጋና ርዕዮት ዓለሙ ከርቸሌ ትወረወራላችሁ፤ ከዚህ የሚያወጣችሁ አንድም ኃይል የለም” ብሏቸው ያርፋል፡፡ ይህ ያላሳቀ ምን ሊያስቅ ይችላል? እንዴ፣ በዚህማ ድዳችንን ተወቅረንም ሆነ ተነቅሰን መሣቅ አለብን፡፡ ግሩም እኮ ነው እናንተ ሆዬ!
ትርፋ ትርፉን እንተወውና ቃል በቃል ወያኔ ያላቸው “ስምምነቱን በፊርማችሁ ካላጸደቃችሁ ትታሰራላችሁ!” የሚል ነው – ከሌሎች የማስፈራሪያ አንድምታዎች ጋር፡፡ አስገዳጁ ደግሞ ራሱ ተገድዶ ቤት ጠባቂ የሆነው ደሳለኝ ነው አሉ – ማነው – ኃይለማርያም – ከአለቆቹ በተነገረው ጥብቅ ማስጠንቀቂያ መሠረት፡፡
ልብ አድርጉ! እነዚህ ሰዎች – እነሳልቫኪር – አነሰም አደገም የአንዲት ሉዓላዊት ሀገር መሪዎች ናቸው – አሁን ቢጣሉምና ከሁለት አንድኛቸው ዓለም አቀፍ ተቀባይነት ያለው መንግሥት በመምራት ላይ መገኘቱ እንዳለ ሆኖ፡፡ ወያኔን ታዲያ ምን ገጠመው? ይህችን እጅ እየጠመዘዙ ማስፈረምን ከሀገር ደረጃ አውጥቶ አህጉራዊ ቅርጽ እንዲኖራት የማድረግን ከፍተኛ ጉጉት ማን አሳደረበት? “የገቡበት የፖለቲካ ቀውስ የሚሠሩትን አሳጥቷቸው ለአንዳች የፖለቲካ ትርፍ ብለው ይሆን እንዲህ ያለ ‹ሪስክ› ውስጥ የገቡት?” ብዬም ተጨንቄላቸዋለሁ – ለወያኔዎቹ – እንዲያ ካልሆነ መቼም ጡት ያልጠባ ማለቴ ያልጣለ ሕጻን ሣይቀር መዘዙን ጠንቅቆ ሊገምተው የሚችለውን ይህን የመሰለ ጅልነት ውስጥ ባልገቡ ነበር፡፡ አሁን አስገድዶ ቢያስፈርማቸው ወደሀገራቸው ሲመለሱ ጉዱን ማለትም ምሥጢሩን እንደሚያወጡት እንዴት ወያኔዎች ሊገምቱ አልቻሉም? እንዴትስ ቢንቋቸው ነው? በኛ የለመዱትን ንቀት እኮ ነው በ‹ኮፒ ፔስት› እነሱም ላይ እውን ያደረጉት፡፡ በውነቱ እነዚህን የመርገምት ፍሬዎች ሰው ናቸው ብሎ መቀበል እንዴት ይቻላል? ኢትዮጵያ በታሪኳ እንዲህ ያለ አሣፋሪ ነገር የፈጸመባት በስሟ የተቀመጠ “መንግሥት” የለም፡፡ እዚህ ላይ አንዲት ብጫቂ ማሳሰቢያ አለችኝ፡- በተለይ ኢሳቶች ይህንን የወንበዴ ጥርቃሞ ቡድን “የኢትዮጵያ መንግሥት” እያላችሁ በዜና ዕወጃችሁ የምትናገሩትን ነገር ባፋጣኝ ብታርሙ ይሻላል፡፡ ይህ ‹መንግሥት› መንግሥት ሣይሆን የከተማ ሽፍታ ነው፤ በአንድ ጎሣ የተዋቀረ፣ ለአንድ ጎሣ ኢኮኖሚያዊና ፖለቲካዊ ጥቅም ያደረ፣ ለዓለም አቀፍ የውንብድና ተቋማት የሰገደና አንዲትን ሀገር ከነሕዝቧ መቀመቅ ለማውረድ ታጥቆ የተነሣን ወሮበላ የአማጊዶዎችን ስብስብ መንግሥት ማለት በመንግሥት ተቋማዊ ምንነት ላይ መቀለድ ነው፡፡ ስለዚህ ቢያንስ “የኢትዮጵያ መንግሥት ተብዬው” በሚል ቢነገር የተሻለ ነውና አንዳንድ ወገኖች አታቁስሉን፡፡ የነሱው ይበቃናል፡፡
አንድ ፈረንጅኛ አባባል አሁን ትዝ አለኝ፡፡ A man cat take a horse to a river; but twenty cannot make it drink. ወዳማርኛው ሲመለስ – አንድ ሰው አንድን ፈረስ ወደ ወንዝ ሊወስደው ይችላል፤ ሃያ ሰዎች ግን ውኃ(ውን) እንዲጠጣ ሊያደርጉት አይችሉም፡፡ የወያኔ ቂልነት፣ የወያኔ ባልጩት ራስነትና አባጉልቤነት እዚህ ላይ ነው፡፡ እነሱ የሚያስቡት ነገር ሁሉ ገዢ ይመስላቸዋል፡፡ የድንቁርናቸው መጠን በምንም ምድራዊ መለኪያ የሚሠፈር አይደለም፡፡ በመንግሥትነት ለሃያ ሦስት ዓመታት የቆዬ አንድ ኃይል የዚችን ፊርማ መነሻና መድረሻ ከነመዘዟ ጭምር ካላወቀ ትልቅ የአስተሳሰብም እንበለው የአመለካከት ችግር አለ ማለት ነው፡፡ እንዲያው ግን ኢትዮጵያ ምን ያህል ብትረገም ፣ እኛም ምን ያህል ባንታደል ይሆን ፈጣሪ እነዚህን ሰዎች የሰጠን? አይጨንቅም? ሳስበው በጣም ይጨንቀኛል – ማይግሬይን የተሰኘውን ከፍተኛ ራስ ምታት የሚለቅ ችግር ነው የገጠመን፡፡
የዚህ ችግር መባቀያ ደግሞ ውስብስብ ነው፡፡ ምዕራባውያንም ይጠየቁበታል – አሉበትና፡፡ ማፈሪያ የሰውነት አካል እንደወያኔው የላቸውም እንጂ ካላቸው በእጅጉ ሊያፍሩበት ይገባል፡፡ በብዙ ነገር እየደገፉ ከበረሃ ወደ ቤተ መንግሥት ያስገቡ ኃይሎች ቆም ብለው ሊያስብቡበት የሚገባ ወቅት ላይ መድረስ የሚገባቸው ይመስለኛል፡፡ እኛን ማመን ስላልፈለጉ እስካሁን አላመኑንም፡፡ የወያኔን ጉድ ቢያውቁትም እንደዚህ ቁልጭ ብሎ የወጣበት ዘመን ባለመኖሩ ይህን ሃቅ ማመን ባይፈልጉና በቆዬ ወያኔን የመደገፍ አቋማቸው የሚጸኑ ከሆነ ከሌላ ከማንም ጋር ሣይሆን ከገዛ ኅሊናቸው ጋር የሚጣሉበት ጊዜ እየደረሰ መሆኑን እየመረራቸውም ቢሆን መገንዘብ አለባቸው፡፡ ወያኔ የአንድን ሉዓላዊ ሀገር ፕሬዝደንት “አስርሃለሁ!” ካለና ካለውድ በግዱ ካስፈረመ ከዚህ በላይ ዓለም አቀፍ ውንብድናና ማፊያነት የለም፤ ወያኔ በዓለም አቀፍ ደረጃ ፕሬዝደንታዊ ስብዕናንና ሀገራዊ ክብርን የሚነካ እንዲህ ያለ ጠያፍ የማንአለብኝነት ተግባር ከፈጸመ የገዛ ምድሩን ዜጎች ምን ሊያደርግ እንደሚችል ማንም ወገን በዚህ ኹነት አማካነት ሊረዳ ይገባዋልና ይህ የሰሞኑ ወያኔያዊ ቅሌት ውርደታዊ ክስተት ለሀገራችን በጎ ገጽታ አለው (ፈረንጆቹ blessing in disguise እንደሚሉት ማለቴ ነው)፡፡ ይህ ነገር እንደሚመስለኝ ወያኔን ብቻ ሣይሆን ምዕራባውያንንም ከነሤራዊ ተንኮላቸው ለማጋለጥ ፈጣሪ ያመቻቸው ነገር መሆን አለበት፡፡ ከፍ ሲል እንደጠቆምኩት ዓለም እስኪታዘበን ድረስ የወያኔን አምባገነንነትና ገዳይነት ስናጋልጥ ብንቆይም ያመነን አልነበረም፡፡ የማቻርንና የሳልቫኪርን ምስክርነት ግን ሊጠራጠር የሚገባ ሰው አይኖርም ብዬ እገምታለሁ ፤ ምንም እንኳን እነሱ ራሳቸውም የአፍሪካዊ አምባገነንነት ወረርሽኝ ሰለባ ቢሆኑም፡፡
አሁን ፈረሱም ሜዳውም ያለው በወያኔ ደጋፊዎች ደጅ ነው፡፡ እስካሁን ያርመጠምጡት የነበረውን የኢትዮጵያ ፖለቲካ ማቃናት የሚያስችላቸው ወርቃማ ዕድል አሁን እፊታቸው አለ፡፡ አንዳንድ ልፍስፍስ ፖለቲከኞቻችንንና ወያኔ ተከል ተቃዋሚ ተብዬዎችን እንዲሁም በወያኔ ቅኝት የሚዘምሩ የነገ ራስ ምታቶችን ትተው ሁነኛ ዴሞክራሲ በሀገራችን የሚመጣበትን መንገድ ሊደግፉ የሚችሉበት ዕድል አሁንም አለ፡፡ አለበለዚያ በኃይል የሚመጣ ሥልጣን ለነሱም ሆነ ለሀገራት እንደማይበጅ የታወቀ ነውና እነዚህ ምዕራባውያን የእጃቸውን የሚያገኙበት ጊዜ ሩቅ አይሆንም፡፡ ብዙዎቹ በዓለም የሚታዩ አመፆችና የሽብር ተግባራት ሥረ መሠረታቸው ሲጠና መነሻቸው እነሱው ራሳቸው ምዕራባውያኑ ናቸው፡፡ ለዐይን ይበጃል ብለው የሚኳሉት ኩል ዐይንን እንደሚያጠፋ ሁሉ ለአንዳንድ ሤራዎቻቸው ስኬታማነት ብለው – ለምሳሌ እንደ አዲሱ የዓለም ሥርዓት (NWO) – የሚተልሟቸው ዕቅዶች በጊዜ ሂደት ወደነሱው እየዞሩ በመተኮሳቸው ባላስፈላጊ ጥቃቶች ዜጎቻቸውንና ንብረታቸውን አስፈጅተዋል፤ እያስፈጁም ነው – 9/11ን፣ 5/7ንና የናይሮቢን የሽብር ጥቃት ማስታወስ በቂ ነው፡፡ ቢን ላደንን ማነው እዚያ ላይ አድርሶት የነበረው? አዎ፣ ሁሉም የሥራውን ነው የሚያገኘው፡፡ የተከልካት ተክል ትጸድቃለች፤ ጠቃሚ ከሆነች ትጠቀምባታለህ፤ ጎጂ ከሆነች ግን ትጎዳባታለህ፤ ሰውን አለኃጢኣቱ ልታጠቃ ብለህ የወረወርካት ጦር ዞራ ተመልሳ ወዳንተው እንደምትመጣ ካላወቅህ ተሳስተሃል፤ ጊዜ ይፍጅ እንጂ በቆፈርከው ጉድጓድ የመግባት ዕድልህ እጅግ ሰፊና የማይቀርም የመጨረሻ ዕጣ ፋንታህ መሆኑን ማወቅ አለብህ፡፡ የበግ ግልገል መስላህ መንገድ ላይ ያገኘሃትን የጅብ ግልገል ቤትህ ውስጥ ብታሳድጋት ተፈጥሯዊ ባህርይዋን አትለቅምና የኋላ ኋላ የምትጎዳው አንተው ነህ፡፡ እናም ወያኔም ሆነ የስምሪት ኃላፊዎቹ ሁሉ የዘሩትን ያጭዳሉ፤ የጊዜና የቋት መሙላት/አለመሙላት ካልሆነ በስተቀር ወያኔ በኢትዮጵያ ምድርና ሰማይ እንደፏለለ የሚኖርበት ዘመን ያከትማል፤ ጦስ ጥምቡሱ ግን ለብዙዎች ይተርፋል፡፡ አርቆ ማሰብ የሚያስፈልገው ለዚህ ነው፡፡ ዛሬ ለምሳሌ አማራውና ኦሮሞው እንዲሁም ሌላው በገርጂም ሆነ በሰሚትና በቦሌ ከመሬቱና ከንብረቱ እየተነቀለ ለባለጊዜው የጎሣ አባላት እንደልብ ቢታደል ይህ ዘመን ሲገለበጥ ተከፍሎ የማያልቅ ዕዳ ይመጣል፡፡ ይህን የምለው ውሻ ሆድ ውስጥ ቅቤ አያድርምና ሰሞኑን ወደሰሚት ሄጄ ሰዎች ያሳዩኝ ትልቅ መንደር ውስጥ ካለሀብቶምና ካለአብረኸት በስተቀር አንድም – ለውርርድ ያህል እንኳን – አንድም ዘበርጋና ደቻሳ ወይም ሸዋርካብሽና አሰጋኸኝ የሚባሉ ዜጎች የማይኖሩበት ምድረ ገነት በአዲስ አበባ መኖሩን ስለተረዳሁ ነው፤ አዲስ አበባና መቀሌን መለየት የማንችልበት አስገራሚ የታሪክ አንጓ ላይ መድረሳችንን የምገልጥላችሁ ነገ ሊከሰት የሚችለውን አደጋ ከወዲሁ በማጤን በታላቅ ፍርሀት ተውጬ ጭምር ነው – ወያኔና ይሉኝታ የማይተዋወቁ መሆናቸውን ቀድሜ ባውቅም ተጋሩ(ትግራውያን) ወገኖቼ ይህን ያህል ኅሊናቸውን ስተው የወያኔን የአድልዖ አሠራር በጭፍን ይከተላሉ ብዬ አምኜ አላውቅም – አዝናለሁ – ሀዘነይ ካብ ልበይ ኢዩ፡፡ ይህ ሁሉ ግፍ ጊዜው ሲደርስ የሚያስከትለውን ጠንቅ የማይረዳ ሰው ካለ የመጨረሻው ከንቱ ነው፡፡ “ፍቅር ያዘኝ ብለህ አትበል ደንበር ገተር፤ እኛም አንድ ሰሞን እንዲህ አርጎን ነበር” አለች አሉ ያቺ ምስኪን አቀንቃኝ፡፡ የተራ ጉዳይ ነው፡፡ ተራ ሲባል ደግሞ እንደወያኔ ያለ ዐይን ያወጣ አድልዖና ፍርደ ገምድልነት በእስካሁኑ ታሪካችን በግልጽ ታይቷል ለማለት እንዳልሆነ ይሰመርበት፡፡ በአፄው ዘመን በፊውዳላዊ መድሎ፣ በደርጉም በወታደራዊ መድሎ የተወሰነ ብልሹ አሠራር እንደነበር መናገር በደልን ያጥባል እንጂ ክፋት የለውም፡፡ የአሁኑ ግን በሀገራችን ቀርቶ በየትም ሀገር ያልተመዘገበ የአንድ ጎሣ ሁሉንም ነገር የማግበስበስ ሁኔታ በግልጽና ክፉኛ በሚያሳፍር አኳኋን እየታዬ ነው፡፡ በነዚህ ልጆቿ የነገይቷ ትግራይ እንዴት እንደምትሸማቀቅ ሳስበው የትግራይ መሬት ራሷ ታሳዝነኛለች፡፡ በርግጥም ላም እሳት ወለደች፡፡ አሁንም አዝናለሁ፡፡ እግዚአብሔርና አስተዋይ የአብራኳ ክፋይ የሆኑ ልጆቿ ይሁኗት ከማለት ውጪ ምን እላለሁ፡፡ እየታዬ ካው አሰቃቂ መድሎ አኳያ ለጊዜው ከዚህ የዘለለ ነገር መናገር አይቻለኝም – ችግር አለ!!!!!!!!….
ሕዝብን የሚመለከት፣ የሕዝብን ዕንባ የሚጠርግ፣ የሕዝብን ብሶት የሚያዳምጥ፣ ሕዝብን ማዕከል ያደረገ ዓለማቀፋዊ ዘመቻ ያስፈልገናል፡፡ የየሀገሩ ሕዝብ በአንድ ወይ በሌላ ምክንያት እያለቀሰ ነው፡፡ ጥቂቶች በሚፈጥሩት ችግር ቢሊዮኖች እየተሰቃዩ ነው፡፡ ይህ የጥቂቶች የበላይነትና ችግር ፈጣሪነት እስካልተወገደ ድረስ መዘዙ ለሁሉም ነው፡፡ ያስለቀሰ እያለቀሰ፣ ያለቀሰም እያስለቀሰ የሚሄድበት መጥፎ አዙሪት እስካልተወገደ ድረስ ዘላቂ መፍትሔ የለም፡፡ … የሰው ልጅ አእምሯዊ ይዘቱ የተዛባ ይመስለኛል፡፡ ራስህን በማለፊያ ምግብ አጥግበህ ሌላውን ስታስርብና ስታሰቃይ የምትደሰት ከሆነ ከእንስሳነትም ወርደሃል ማለት ነውና ሰብኣዊ ዕድገትህ ላይ ችግር መከሰቱን ልብ ማለት ሊኖርብህ ነው፡፡ አሳዛኝ ወቅት ላይ እንገኛለን፡፡
ወያኔን ግን በደምብ ዐወቅናት አይደል? እስኪ እዚች ላይም ትንሽ እንሳቅና እንዝናና – “ካልፈረማቸሁ እናስራችኋለን!!!” ጥጃ ገዝተው ወይም ወደማርካቶ ወጣ በማለት አንድ አምስትና ስድስት ሺህ ኢትዮጵያውያን የሰው እንስሳትን እንደለመዱት አያስሩም? ቅብጠታቸው ግን ለከትና ድንበር አጣ፡፡ ለነገሩ በጌታዋ የተማነች በግ ላቷን ቀለበት መንገድ ላይና አባይ ላይ ታስራለች ይባል የለም? ዘይገርም ሻሸመኔ ትብስ ኮፈኔ፡፡ ጉድ ነው፡፡
የሠራዊት ጌታ እግዚአብሔር በሰሞኑ ግርግር በአምቦና በሌሎች የሀገራችን አካባቢዎች ሕይወታቸውን ያጡ ወገኖቻችንን ነፍሳት በአብርሃምና በያዕቆብ ነፍሳት አጠገብ ያኑርልን፣ በጠባቡ ቃሊቲ የታሰሩትንም፣ በሰፊው “ዞን 9” የታሰርነውን እኛንም ፈጣሪ በቸርነቱ ይጎብኘን፡፡ አስቡ – ቀኒቷ ቀርባለች፡፡ ምልክቶች ሁሉ ታይተዋልና “ፕሊዝ” ወደየኅሊናችን በመመለስ ውስጣችንን እናጽዳ፡፡ ተመልሰን ሰው እንሁን፡፡ ሰው መሆን እንችላለን፤ መብትም አለን፤ ሰው ለመሆን ደግሞ በሕይወት እስካለን ድረስ ሁላችንም ልንሞክረው የሚገባን ታላቅ አምላካዊ ፀጋ እንጂ ቀነ ገደብ የተጣለበት ለማንም የተከለከለ ጉዳይ አይደለም፤ እናም ተስፋ ሳንቆርጥ ሰው ለመሆን እንሞክር፡፡ ያኔ ነው ከነዚህ ጉግማንጉጎች ነጻ የምንወጣው፡፡ አለበለዚያ በባርነት እየዳከርን ብዙ ጊዜ እንቆያለን – የባርነቱ ዘመን ይረዝምብናል፡፡ እናም ሰው በመሆን ፈጣሪን እናግዘው – የነጻነታችንን ጊዜም እናቅርብ፡፡