Monday, September 30, 2013

አዲሱ የኢህአዴግ አሰላለፍ (ተመስገን ደሳለኝ)

አዲሱ የኢህአዴግ አሰላለፍ (ተመስገን ደሳለኝ) ኢህአዴግ ከቀድሞ ሊቀ-መንበሩ አቶ መለስ ዜናዊ ህልፈት በኋላ በተከሰተበት ውስጣዊ ልዩነት በተለዋዋጭ የኃይል ሚዛን ሥር ለማደር በመገደዱ የስልጣኑን መዘውር የሚያሽከረክረውን አካል ለመለየት አዳጋች ነበር፡፡ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ግን ይህ ሽኩቻ መፍትሄ ማግኘቱን የሚያመላክቱ ሁናቴዎች መፈጠራቸውን የውስጥ አወቅ መረጃዎች ጠቁመዋል፡፡ እንደ መግቢያ ድንገቴው የመለስ ህልፈት ህወሓትን ቢከፍለውም፣ ብአዴን ራሱን እንዲያጠናክር መደላድል ፈጥሮለታል፡፡ ይህ የሆነበት ምክንያት መለስ ዘመኑን ሙሉ በብአዴን ታማኝነት ላይ ጥርጣሬ ስላልነበረው ቀድሞውንም እንዲዳከም ባለማድረጉ ይመስለኛል፡፡ እርሱ በአይነ ቁራኛ ይጠብቀው የነበረው ህወሓትን ነበር፤ በተለይም
በሠራዊቱ እና በደህንነቱ ውስጥ ‹‹ተፅእኖ መፍጠር ይችላሉ›› የሚባሉት አቦይ ስብሃት ነጋ እና የትግራይን መዋቅር በእጁ ያደረገው የቀድሞ የክልሉ አስተዳዳሪ ፀጋዬ በርሄ በጥርጣሬ ዓይን የሚታዩ ሆነው ቆይተዋል፡፡ በምርጫ 2002ቱ ማግስትም ድርጅቱ አቦይን ‹‹በክብር›› እንዲሸኝ ሲደረግ፣ ፀጋዬ በርሄን ደግሞ ‹‹አማካሪ›› በሚል ሽፋን ከመቀሌ ወደ ቤተ-መንግስት (ጠቅላይ ሚንስትሩ ቢሮ) አዛውሮ በቅርብ እይታ ስር በማዋሉ ሁለቱንም ከጨዋታ ውጪ አድርጓቸዋል፡፡ በግልባጩ አዜብ መስፍንና ‹የመለስ ታማኞች› የሚባሉት እነአባይ ወልዱና ቴዎድሮስ ሀጎስ የፖሊት ቢሮውን ተቀላቅለዋል፡፡ ሁነቱም ከእነአቦይ ጋር በስጋ ዝምድናና በጋብቻ የተሳሰሩ ባለስልጣናትን በማስከፋቱ በድርጅቱ ውስጥ ብቻ የሚታወቅ (አደባባይ ያልወጣ) ልዩነት ፈጥሮ እንደነበረ ይታወሳል (በነገራችን ላይ ኦህዴድ የማዳከሙ ሴራ ሰለባ ነው፡፡ ይህ ሁናቴ ከመለስ ህልፈትም በኋላ ቀጥሏል፤ ለምሳሌ ባለፈው ዓመት የግንባሩ አባል ድርጅቶች፣ የየራሳቸውን ጠቅላላ ጉባኤ ባካሄዱበት ወቅት ብአዴን በ‹ክብር› ካሰናበተው ሁለት ዓመት ያለፈውን መሪውን አዲሱ ለገሰን ወደ ቦታው መልሶ ራሱን ሲያጠናክር፣ በተቃራኒው ኦህዴድ አንጋፋ አመራሮቹን፡- አባዱላ ገመዳ፣ ኩማ ደመቅሳና ግርማ ብሩን ከስራ አስፈፃሚነታቸው እንዲያነሳ ተገድዷል፡፡ ይህንን ነው መተካካት የሚሉትም፡፡ ህወሓት የመለስን ህልፈት ተከትሎ በውስጡ ያደፈጠው ቅራኔ ፈንቅሎ በመውጣቱ ህወሓትን የ‹መቀሌው› እና የ‹አዲስ አበባው› በሚል ለሁለት ከፍሎት ነበር፤ ይህ ግን የመቀሌው-በአዲስ አበባ፤ የአዲስ አበባው-በመቀሌ ደጋፊ አልነበረውም እንደማለት አይደለም (የመቀሌውን አዜብ መስፍን፣ አባይ ወልዱ፣ ቴዎድሮስ ሀጎስ… መርተውታል፤ የአዲስ አበባውን ደግሞ አቦይ ስብሃት ነጋ፣ አባይ ፀሃዬ፣ ደብረፅዮን ገ/ሚካኤል እና ጌታቸው አሰፋን ጨምሮ በርካታ አንጋፋ ታጋዮች ዘውረውታል)፡፡ ይህ አጋጣሚም ከእነ አዜብ ቡድን ጋር ትብብር የፈጠረውን ብአዴንን ለጊዜያዊ ድል አብቅቶት ነበር (በ93ቱ ክፍፍልም የብአዴን ድጋፍ መለስ በአሸናፊነት እንዲወጣ ጉልህ ድርሻ ማበርከቱ ይታወሳል)፡፡ አቦይ ስብሃት ነጋ በትግርኛ ቋንቋ በሚታተመው ‹‹ውራይና›› መፅሄት ላይ ‹‹ህዝቢ ትግራይ ዘቃልሶ ኣቃሊሱ ዝጠቕሞ ወያናይ ውድብ ይግብኦ›› (የትግራይ ህዝብ የሚያታግለው፣ ታግሎም የሚጠቅመው ወያኔያዊ ድርጅት ይገባዋል) በሚል ርዕስ በፃፉት ፅሁፍ ችግሩን እንዲህ ሲሉ ገልፀውታል፡- ‹‹አባይ ወልዱም ባለፈው የህወሓት ጉባኤ ላይ በተደጋጋሚ ‹ህወሓት ውስጥ ማጠለሻሸትና (የሥልጣን) ሽኩቻ በስፋት እየተስተዋለ ነው› በማለት ሁኔታውን ገልፆታል፡፡ ከዚህ በላይ ማረጋገጫ ደግሞ የለም፡፡ እንዲህ ያለ በኃይል አሰላለፍ ደረጃ ሊታይ የሚችል የአንድን የፖለቲካ ድርጅት አቅም ከማዳከምና መርሀ-ግብሩን ከማሰናከል አልፎ ተርፎም ድርጅቱን ለአስከፊ ውድቀት ሊጥል ከሚችል አደገኛ ሁኔታ የበለጠ አደጋ ያለ አይመስለኝም፡፡›› (‹ውራይና› ቁጥር 4 ነሐሴ 2005 ዓ.ም) ከኃይለማርያም ጀርባ ኃይለማርያም ደሳለኝ የግንባሩ ሊቀ-መንበር በመሆኑ ጉዳይ ላይ ብአዴንም ሆነ ሁለቱ የህወሓት ቡድኖች ቅሬታ አልነበራቸውም፤ ምክንያቱም እርሱም ሆነ ‹ደቡብን እወክላለሁ› የሚለው ድርጅቱ ለአሸናፊ ኃይል ከማገልገል አልፈው የፖለቲካ አመፅ ሊያስነሱ እንደማይችሉ ይታወቃልና፡፡ ይሁንና በወቅቱ ኃይለማርያም ሰልፉን በ‹መለስ ባርኔጣ› ከሚንቀሳቀሰው ከመቀሌው ህወሓትና ብአዴን ጋር ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝበማስተካከሉ የኃይል ሚዛኑ በአንፃራዊነት ወደእነርሱ እንዲያጋድል አድርጓል፡፡ በግልባጩ ለእነ አቦይ እና ደጋፊዎቻቸው የመሸነፍ መገለጫ ተደርጎ ተወስዷል፡፡ እንግዲህ እስከ ዘጠነኛው የኢህአዴግ ጉባኤ ድረስ ‹መልከ-ኢህአዴግ› በዚህ መልኩ ነበር የቀጠለው፡፡ ‹መፈንቅለ-ህወሓት› ብአዴኖች፣ ከመቀሌው ህወሓት ጋር የፈጠሩትን ግንባር፣ ከአዲሱ ጠቅላይ ሚኒስትር መንበር ካገኙት ድጋፍ ጋር በማዋሀድ፡- የአዲስ አበባውን ህወሓት የአመራር አባላት ሙሉ በሙሉ፣ የደህንነት ሀላፊው ጌታቸው አሰፋን እና አንጋፋ የህወሓት ታማኝ ጄነራሎችን ከመንግስታዊውም ሆነ ከፓርቲው ኃላፊነታቸው በማንሳት በአሸናፊነት ለመወጣት ስልታዊ እንቅስቃሴ አድርገው እንደነበር ለድርጅቱ ቅርብ ከሆነ ሰው አረጋግጫለሁ፡፡ በባህርዳሩ ጉባኤ ላይም መላኩ ፈንቴ ‹አላሰራ አሉኝ› ብሎ በአደባባይ እንዲያጋልጣቸው ከተደረጉት የንግድ ደርጅቶችና ሀብታም ነጋዴዎች አብዛኞቹ ከአዲስ አበባው ህወሓት ጋር የተሳሰሩ እንደነበረ ይታወቃል፡፡ እነዚህን ኩነቶችም ነው ‹መፈንቅለ-ህወሓት› ለማለት የተገደድኩት፡፡ ሴራው የከሸፈው በሁለት ምክንያቶች ይመስለኛል፤ የመጀመሪያው በሰውየው ህልፈት ማግስት (ተተኪው ጠቅላይ ሚንስትር ገና ባልተመረጠበት) እነአባይ ፀሀዬ ሶስት ሜጀር ጄነራል እና ሰላሳ አራት ብርጋዴር ጄነራሎች (አብዛኞቹ የህወሓት ሰዎች ናቸው) መሾማቸው ኃይላቸውን ሲያጠናክርላቸው፣ በአንፃሩ የመቀሌውን ህወሓትና ብአዴንን በሠራዊቱ ውስጥ የነበራቸውን ተፅእኖ ከማዳከሙም በላይ ኃይል የማሰባሰብ ሩጫቸውንም ገትቶታል፡፡ ሁለተኛው ምክንያት ደግሞ በደህንነት መስሪያ ቤቱ አቀናባሪነት በ‹ፀረ ሙስና› ሽፋን የተከፈተው ዘመቻ ነው፤ እነበረከትንም ስልታቸውን መልሰው እንዲያጤኑ ያስገደዳቸው ይህ አይነቱ አስደንጋጭ እርምጃ ይመስለኛል፡፡ የህወሓት ‹ቆሌ› የኢትዮጵያን ልማዳዊ ፖለቲካ ከነሴራው ጠንቅቀው ከተረዱት ጥቂት ሰዎች መሀል አቦይ ስብሃት ነጋ አንዱ መሆናቸው ተደጋግሞ ተነግሯል፡፡ አቦይ ህወሓትን ጠፍጥፎ በመስራቱም ሆነ በስልጣን ለማቆየት የመለስን ያህል (ሊበልጥም ይችላል) ለፍተዋል፡፡ ዛሬም ተፈጥሮ ላመጣባቸው እርጅና እጅ ሳይሰጡ በህወሓት ላይ የሚሴረውን-ለመበጣጠስና ለተቀናቃኞቻቸው-ጉድጓድ ለመቆፈር እንደማይሳናቸው አሳይተዋል፡፡ ይህ ሁኔታም ነው ‹የህወሓት ቆሌ› የሚል ቅጥያ ያሰጣቸው፡፡ ከመለስ ዜናዊ ጋር የነበራቸው ጥብቅ የመተባበር መንፈስም ከጓዳዊነትም በላይ እንደነበር የቅርብ ሰዎቻቸው ይመሰክራሉ፡፡ ግና ይህ የጦፈ ፍቅራቸው ከ2000 ዓ.ም ወዲህ መደብዘዝ ጀምሮ ነበር፤ ልዩነታቸውም ቅስ በቀስ እየሰፋ ለመምጣቱ ብዙ ማሳያዎች አሉ፡፡ አንዱ መለስ፣ ለአዜብ መስፍን እየሰጠ የነበረውን የፖለቲካ ጉልበት፣ አቦይ ‹ህወሓትን በሴት ቀሚስ እንደማሳደር› አድርገው መውሰዳቸው ነበር፡፡ ሌላው የሴቲቱ ኃይለኝነት የአቦይን የተሰሚነት ክልል ከመፈታተን አልፎ በአደባባይ ክብራቸውን እስከ መዳፈር መድረሱ ይመስለኛል፡፡ ችግሩን ለመፍታትም ከመለስ ጋር ተገናኝተው መነጋገር አልቻሉም፤ ለህወሓት ቅርብ የሆኑ ወዳጄ እንደነገሩኝ መለስ ህይወቱ ሲያልፍ አቦይን ካገኛቸው ከሁለት ዓመት በላይ ሆኖታል፤ ምክንያቱ ደግሞ እርሱ ማግኘት ባለመፈለጉ ነበር፤ ይህም ሆኖ አቦይ ተደጋጋሚ ጥረት ቢያደርጉም በልዩ ረዳቱ አማካኝነት ‹አስቸኳይ ጉዳይ ላይ ነው› እያስባለ መልሷቸዋል፤ በስራ አጋጣሚ ከቢሮ ውጪ ሲገናኙም ‹አጣዳፊ ስራ ስለተደራረበብኝ ነው፤ እኔ ራሴ አስጠራሀለሁ› እያለ ለሁለት ዓመት ያህል ሲርቃቸው ከቆየ በኋላ ነበር ድንገት ህይወቱ ያለፈው፡፡ አቦይ ወደ ህወሓት ተመልሰው በንቃት መሳተፍ የጀመሩት የመለስን ጤንነት ሲከታተሉ የነበሩ ሐኪሞች ‹ተስፋ የለውም› ባሉበት ማግስት ነበር፤ እንደምክንያት ያስቀመጡት ህወሓት ከድህረ-መለስ በኋላ፣ የብአዴንን የትከሻ ግፊያ መቋቋም አይችልም የሚል ስጋትን ነው፡፡ የሰውየው መጨረሻ ከታወቀ በኋላም የተፈጠረውን ክፍፍል ተከትሎ የታየው የኃይል ሚዛን ይህንኑ የሚያረጋግጥ ነበር፡፡ በወቅቱም አቦይ ‹መፍትሄ› ብለው ያቀረቡት ‹ብአዴንና ከጎኑ የተሰለፉትን የህወሓት የአመራር አባላትን ማሸነፍ ስለማንችል፣ አንጃው (የእነ ስዬ ተወልደ ቡድን) ተመልሶ ያጠናክረን› የሚል ነበር፤ በስማቸውም ‹‹ውራይና›› መፅሄት ላይ በፃፉት (ርዕሱ ከላይ በተጠቀሰው) ፅሁፍ ጉዳዩን እንዲህ በማለት ገልፀውት ነበር፡- ‹‹…ሁላችንም ህወሓት ውስጥ እያለን እኮ አንጃው ድርጅቱን ተቆጣጥሮት በትረ-መንግስቱንም ሊጨብጥ ተቃርቦ ነበር፡፡ በአንጃው የመዋጥ አደጋ ጊዜ ሁላችንም ተኝተን ነበር፡፡ እነዚያ የተሰናበቱት ሰዎች በማዕከላዊ ኮሚቴው ውስጥ ቢቆዩ ኖሮ ይተኙ ነበር ማለት ግን አይደለም፡፡ አሁን ላለው አመራር ይደግፉት ነበር ይሆን ማለቴ ነው እንጂ፡፡ …ከዚህ ቀደምም ሆነ አሁን ከህወሓት ማዕከላዊ ኮሚቴ የወጣ ሁሉ እንደአዲስ ተደራጅቶ አሁን ላለው ማ/ኮሚቴ እገዛ የሚያደርግበትን መንገድ ማፈላለግ አለበት፡፡…›› (‹ውራይና› ቁጥር 4 ነሀሴ 2005 ዓ.ም) ሆኖም አባይ ፀሀዬ፣ አርከበ እቁባይ፣ ፀጋዬ በርሄ፣ ጌታቸው አሰፋን የመሳሰሉት ‹በጭራሽ አይሆንም! የእነርሱ መመለስ ያውከናል› የሚል አቋም በመያዛቸው ሃሳቡ ተፈፃሚ ሳይሆን ቀርቷል፡፡ ከዚህ በኋላ የእነ አቦይና አባይ ቡድን ‹ህወሓትን ማዳኛ› ያለውን ሁለት ወሳኝ እርምጃ ወስዷል፤ ከህግ ውጪ ሶስት ሜጀር እና ሰላሳ አራት ብርጋዴር ጄነራሎችን ሲሾም፣ በደህንነት መስሪያ ቤት ውስጥ ቁልፍ ሰው የነበረውን ወ/ስላሴ ወ/ሚካኤልን ከየትኛውም አይነት ‹ኦፕሬሽን› እንዲገለል አደረገው፤ ቀጥሎ ደግሞ ሙሉ በሙሉ ከሀላፊነቱ አነስቶታል፡፡ በዚህ በኩል ያገኙትን የፖለቲካ ጉልበት በመመንዘር ከህገ-መንግስቱም ሆነ ከተለምዶአዊው አሰራር በማፈንገጥ ተጨማሪ ሁለት ም/ጠቅላይ ሚንስትሮች እንዲሾሙ ጫና ፈጥረው ደብረፅዮን ገ/ሚካኤል፣ ኃ/ማርያም ደሳለኝን በቅርብ ርቀት እንዲከተል አድርገዋል (በነገራችን ላይ ባለፈው ዓመት አጋማሽ ህወሓት የማዕከላዊ ኮሚቴ አባላትን በመረጠበት ወቅት ወልደስላሴ ሲጠቆም፣ ጠንካራ ተቃውሞ አቅርቦ እንዳይመርጡት ያነሳሳበት የደህንነቱ ሀላፊ ጌታቸው አሰፋ ሲሆን፣ በአንፃሩ ጌታቸው የተጠቆመ ጊዜ ወልደስላሴ እና ገብረሃዋድ ተቃውሞውን ቢያስተባብሩም ታናሽ ወንድሙ በላይ አሰፋን ጨምሮ ከመመረጥ ማደናቀፍ አልቻሉም፡፡ በአሁኑ ወቅት ደግሞ ወልደስለሴና ገብረሃውድ በሙስና ተጠርጥረው በእስር ላይ ይገኛሉ)፡፡ ሌላኛው የህወሓት ‹ጠባቂ መልአክ› አባይ ፀሀዬ ነው (በ2005 ዓ.ም ወርሃ ጥቅምት በታተመችው ‹አዲስ ታይምስ› መፅሄት ላይ አባይ፣ መለስ ያደረገውን ማድረግ የሚችል /ከንግግር ችሎታ በቀር/ አደገኛ ሰው መሆኑን መግለፄ ይታወሳል) ዘግይቶም ቢሆን ቡድኑን የበላይ ባደረገው የ‹ፖለቲካ ጨዋታ› እርሱም የአንበሳውን ድርሻ እንደሚወስድ ታይቷል፡፡ ደብረፅዮንም ቢሆን ከህወሓት ጋር ባሳለፈው ዘመን ‹ትጉህ ደቀ-መዝሙር› ስለነበር ያካበተው ልምድ ህወሓትን በታደገው ንቅናቄ ላይ አስተዋጽኦ አድርጓል፡፡ የሆነው ሆኖ እነ አባይ ከባህርዳሩ ጉባኤ በኋላ ነው ‹ከመከላከል ወደ ማጥቃት› ተሸጋግረው ብአዴንንና የመቀሌውን ህወሓት በ‹ሙስና› ስም ሰለባ ያደረጉት፡፡ ይህንን እውነታም የሚያጠናክርልን አቦይ ስብሃት ‹‹ውራይና›› መፅሄት ስለ ጉዳዩ ጠይቋቸው የሰጡት ምላሽ ነው፡- ‹‹አሁን በእስር የሚገኙት [እነመላኩ ፈንቴን ማለታቸው ነው] ሙሰኞች ብቻ አልነበሩም፡፡ የፖለቲካዊ ኃይል አሰላለፍንም ሲለውጡ የነበሩ ናቸው፤ ያስፈራሩም ነበር፤ ‹የስልጣን ሹዋሚም ሻሪም እኛ ነን› አስከማለትም ደርሰው ነበር፡፡›› (‹ውራይና› ቁጥር 2 ሠኔ 2005 ዓ.ም) የብአዴን የአመራር አባል የሆነ አንድ ሚንስትር ለእስር ሲዳረግ፣ ሌላ ሚንስትር ደግሞ ከኃላፊነቱ መነሳቱ ይታወቃል፡፡ አዲሱ ግንባር ብአዴን የአዲስ አበባው ህወሓት ክንደ-ብርቱ እየሆነ በመምጣቱ፣ የእነ አዜብን ቡድን አውላላ ሜዳ ላይ ትቶ አብሮ ለመስራት ተደራድሯል፡፡ እነ አባይም ‹ከብአዴን ተሻርኮ ሊያስበላን ነበር› ያሉትን የመቀሌውን የህወሓት ኃይል ከሞላ ጎደል ሲያስገብሩት፣ የቡድኑ መሪን አዜብ መስፍንን ደግሞ ከኤፈርት ከማሰናበታቸውም በላይ የፓርላማ ወንበሯን የሰዋችለትን የአዲስ አበባ የከንቲባነት ምኞቷን አጨልመው፣ በመለስ ፋውንዴሽን ገድበዋታል (የመለስ ሙት ዓመት በተከበረበት ወቅት የትግሉን ዘመንና የመለስን ገድል በኢቲቪ ሲተርኩልን የነበሩት የታሪኩ ዋና ተዋንያን አቦይ ስብሃት ነጋ፣ አባይ ፀሀዬ፣ ሳሞራ የኑስ…ሲሆኑ፣ በህልፈቱ ሰሞን ግን መድረኩን ተቆጣጥረውት የነበሩት ብአዴኖች፣ እነኩማ ደመቅሳ እና ትግሉን በመፅሀፍትና በቴሌቪዥን የሚያውቁት እነ ሬድዋን ሁሴን መሆናቸውን ስናስታውስ የእነ አባይ ፀሀዬ ህወሓት ምን ያህል ተገፍቶ እንደነበረ እንረዳለን፡፡) በአናቱም ብአዴን የበላይነቱን በጨበጠበት ወቅት እንደ ስጋት ቆጥሮት ‹ሊፐውዘው› አስቦ የነበረውን መከላከያም፣ ከድርድሩ በኋላ በሁለቱ ኃይሎች ስምምነት ለአምስት ቀናት ኪራይ ሰብሳቢነትን እና ሙሰናን በተመለከተ ብቻ ተገማግሞ እንዲታለፍ ተደርጓል፡፡ ከኃላፊነታቸው ለማንሳት የታሰቡት ጄነራሎች ጉዳይም ‹ያልታሰበ አደጋ ሊያመጣ ይችላል› በሚል ለጊዜው ተዘሏል፡፡ ይሁንና ኤታማዦር ሹሙን ጄነራል ሳሞራ የኑስን በዚሁ ዓመት መጨረሻ በ‹ክብር› ሸኝቶ፣ ጄነራል አበባው ታደሰን የመተካት ዕቅድ መኖሩን ምንጮች ጠቁመዋል (ከዚህ በኋላ በጡረታ የሚሰናበቱ ጄነራሎች ‹መከላከያ ቴክኖሎጂ› /መቴክ/ በሚመራውና ወደፊት በሚያቋቁማቸው ኢንዱስትሪዎች ውስጥ በስራ-አስኪያጅነት ወይም በቦርድ አባልነት እንደሚመደቡ ቃል ተገብቶላቸዋል) ከኃ/ማርያም ጀርባ ያደፈጠ-ስውር እጅ በሁለቱም ቡድን ካሉ ምንጮቼ ‹‹ኃ/ማርያም ስራው ከብዶታል›› የሚል ቅሬታ እንደነበራቸው ሰምቻለሁ፤ ይሁንና መፍትሄ ተደርጎ የተወሰደው በረከት ስምዖንን የጠቅላይ ሚንስትሩ ‹የፖሊሲና ጥናት ምርምር› አማካሪ በሚል ሹመት በጽ/ቤቱ ማስቀመጥን ነው፤ እርሱሁሉንም ነገር ከጀርባ ሆኖ እንዲያከናውን ወስነዋል፡፡ በረከት የተመረጠው ‹ከመለስ ጋር በቅርብ ስርቷል፣ መለስ ያነበበውን አንባቧል፣ የመለስን የዕለት ተዕለት ሥራ በቅርብ ተከታትሏልና መንገድ ይመራል› በሚል እንደሆነ ምንጮቼ ነግረውኛል (በነገራችን ላይ መለስ ሞት ባይቀድመው ኖሮ የወደፊት ዕቅዱ ቤተ-መንግስቱ ውስጥ ጀምሮት የነበረውን ግንባታ አጠናቅቆ፣ ከ2007ቱ ምርጫ በኋላ ስልጣኑን፣ ከአሻንጉሊቶቹ ለአንዱ አስረክቦ፣ መኖሪያውንም ወደ አዲሱ ህንፃ አዛውሮ፣ በለቀቀው ቤት ውስጥ የሚያስገባውን ጠቅላይ ሚንስትር ከጀርባ ሆኖ መዘወር ነበር፡፡ ለዚህም ይመስለኛል ህልፈቱን ተከትሎ ግንባታውም የተቋረጠው፡፡ ሰሞኑን ደግሞ ግንባታው ሊቀጥል እንደሆነ ሰምቻለሁ፡፡ በረከት ስምዖን እንዲገባበት ታስቦ ይሆን? …አባይ ፀሀዬም ከሚቀጥለው ወር ጀምሮ የጠቅላይ ሚንስትሩ ‹አማክሪ› ሆኖ እንደሚሾም ‹ፎርቹን› ጋዜጣ በ‹ጎሲፕ› አምዱ አትቷል፡፡ መቼም ኃ/ማርያም ‹‹ሰርክ ‹እኔም አንደ ዳዊት ጨርቄን ልጣልለት› እያልኩ እዘምርለታለሁ›› ያለን አምላኩ ካልታደገው በቀር፣ ከእነዚህ ጉልበታም ሰዎች በጤና መውጣቱን እንጃ!) ህወሓትና ብአዴን ልዩነታቸው መፈታቱን ለማሳየት፣ በረከት ስምዖን ከአዲሱ ሹመት በኋላ በሃያ ሁለት ዓመታት የስልጣን ዘመኑ አድርጎት የማያውቀውን መንግስትን ወክሎ (በግሉ ሄዶ ሊሆን ይችላል) በትግራይ ክልል በሚገኙ የተለያዩ ከተሞች የስራ ጉብኝት አካሄዷል፡፡ ‹ድምፀ ወያኔ› የተባለው የክልሉ ሬዲዮ ጣቢያም ጉብኝቱን ሳምንት ሙሉ ሳይታክት ደጋግሞ አስተላልፎታል፡፡ ሽራፊ-መረጃ የአቦይ ስብሃት ነጋ ቡድን በኢህአዴግ ውስጥ ተከስቶ ከነበረው ክፍፍል በአሸናፊነት መውጣቱ ከተረጋገጠ በኋላ አዲስ ወሬ እየተሰማ ነው፡፡ ይኸውም ‹ህወሓት የጠቅላይ ሚንስትርነት ቦታውን በመልቀቁ፣ ፕሬዚዳንት ግርማ ወ/ጊዮርጊስ የሚያስረክቡትን ወንበር አቦይ ስብሃት መያዝ አለባቸው› የሚል ነው፤ ምንም እንኳ ሃሳቡ ተፈፃሚነት ባይኖረውም፣ ምንጮቼ አቦይ ራሳቸው በዘወርዋራ መንገድ ያሰራጩት ወሬ ሊሆን ይችላል ብለው ያምናሉ፡፡ አዜብ መስፍንም ቦታውን የመያዝ ፍላጎት ያላት ይመስለኛል፡፡ ብዙ ሲባልለት የቆየው የድህረ-መለስ ኢህአዴግ ከላይ ለማቅረብ በሞከርኩት መንገድ ግራና ቀኝ ሲዋልል፣ የመከፋፈል ተግዳሮትን ሲሻገርና እንደገና እየተመለሰ ሲሰባሰብ እዚህ ደርሷል፡፡ በዚህ ኮሮንኮቻማ ሂደት ውስጥ የጠቅላይ ሚንስትሩ ሚና ‹እዚህ ግባ› የምንለው እንዳይመስለን ሆኗል፡፡ ኃይለማርያም መንግስታዊ ብቻ ሳይሆን የፓርቲው ሊቀ-መንበርነትን የመሰለ ጠንካራ ፖለቲካዊ ስልጣን መያዙ ይህ ሰው የሚባለውን ያህል የዳር ተመልካች ሆኖስ ይቆያልን? ለሚለው ጥያቄ ቀጣይ ጊዜያቶች ብቻ መልስ ይኖራቸዋል፡፡ የጠቀስኳቸው የስርዓቱ ጉምቱ ሰዎች በዚህ መልኩ እየተንቀሳቀሱም ቢሆን፣ ይህን የኃይል መገዳደር እያደረጉ ያሉት በስልጣን ሞኖፖሊ ላይ ተቀምጠው መሆኑን ልብ ይሏል፡፡ እናም ባቀረብኳቸው ሂደቶች እያለፉም ይሁን አይሁን ለስልጣናቸው የሚያሰጋ ጠንካራ የታቃውሞ ስብስብ አለመኖሩን ማመናቸው ይመስለኛል፣ የኃይል ትንቅንቁን ‹ግዜው አይደለም› ብለው ለማራዘም ሳይጠነቀቁ በግላጭ እርስ በእርስ የተፋለሙት፡፡ የሆነው ሆኖ የፓርቲው የታሪክ ድርሳን እንደሚነግረን ‹ይሆናሉ› የተባሉት ተቀልብሰው፣ ባልተጠበቁ ሁነቶች (የኃይል መገለባበጥ ተከስቶ) ፖለቲካው የሚመራበት አጋጣሚ ሊፈጠር የሚችልበት ዕድል ሊኖር እንደሚችልም መዘንጋት አያስፈለግም፡፡

Incomplete Audits Mean More Prison Time For Corruption Detainees

A further continuance until September 30, to complete audit investigations for companies under detained businessmen Mehertab Abreha and Begziabhere Alebel, was granted to the Federal Ethics & Anti Corruption Commission (FEACC) last Friday. Investigations on the two have been ongoing for four months while they remained in custody. .
Meheretab, brother of the ex-TPLF strongman, Seye Abreha, and Begziabhere, a renowned architect, are among a group of over 60 tax officials, businessmen and freight forwarders that were arrested in May 2013. This came following a high level corruption crackdown on the tax sector by the Commission. Melaku Fenta, former director general of the Ethiopian Revenues & Customs Authority (ERCA); Gebrewahed W. Giorgis, his deputy, and businessmen of some fame, including – Simachew Kebede of intercontinental hotels; Ketema Kebede of K.K. Plc and Nega G. Egziabhere of Netsa Trading Plc – were among those detained. Following repeated continuances for investigation, the Commission finally pressed charges against close to 44 of its suspects, including the high profile detainees. Some were allowed to go out on bail. But, for Meheretab and Begziabhere, along with two other detainees – businessman Fitsum G.Medhin and detained ERCA customs official Tekleab Zerabruk – their fates remained undecided. Claiming that audit reports of the suspects’ respective companies were taking time to complete, the Commission asked that they be kept at the Federal Police Commission’s Maekelawi jail. On the other hand, their charged companions were moved to the Kaliti and Kilinto correctional facilities. Three continuances of an average of eight days were granted to the Commission’s investigators before Friday’s hearing. As usual, the four detainees were bussed in to the Federal High Court at 9:00am in the morning. It took until half past eleven before a judge was found to look at the case. Investigators first announced that they had completed audits on Tekleab Zerabruk and had no objections to the defendant being released on bail. The only indication about impending charges came when the investigator stated that charges to be levied against Tekleab were not serious enough to deny him bail rights. Tekeab, who said that he had a gross salary of 7,000 Br, working for the ERCA’s Mille branch, was asked to pay 20,000 Br in bail bond by the judge, who also ordered his release. For Meheretab and Beegziabhere, however, such a conclusion was elusive. The Commission’s investigator maintained that their companies’ audit reports were incomplete and asked for 14 days additional time. The judge, after admonishing the investigator that holding a person for a sustained period of time without charge would later make the government liable for compensation should the person be found innocent, granted an eight-day continuance. This eight day deadline fell on Friday September 27, 2013, which is a Meskel Holiday, hence the case was adjourned until the following Monday. Fetsum Gebremedhin’s case was rescheduled for Monday, September 23, because his file could not be found in time. Two additional detainees were also brought into court in connection to the corruption investigation on Friday. Tadele Berhanu and Woldemichael Halefa, both businessmen, were arrested last week for allegedly importing materials without paying customs fees or taxes, by bribing customs officials. They were also accused of alleged money laundering. Investigators asked for the usual 14 days of investigation to take further testimony of the suspects and gather evidence. The judge granted their request and adjourned the case until October 4

Ethiopia opposition stage anti-government demo September 30/2013

. A leading Ethiopian opposition group gathered Sunday to protest against the country's anti-terrorism legislation, the head of the group said. ???We want the government to abrogate the law and to release all political and prisoners of conscience immediately,??? Negasso Gidada, the leader of the opposition Unity for Democratic Justice (UDJ), told AFP.
Several opposition members and journalists, including dissident blogger Eskinder Nega, have been jailed under the 2009 legislation. The government accused the group of ???glorifying??? convicted criminals and said the threat of terrorism in Ethiopia needed to be taken seriously. ???These people are downplaying the danger that this country has been facing... its not a potential threat, it's already there,??? said government spokesman Redwan Hussein. Negasso said he was briefly arrested ahead of the protests along with the single member of parliament from an opposition party, Girma Seifu, and 60 other people. Redwan said he did ???not know of anybody??? who had been detained. The demonstration is part of a three-month campaign launched by UDJ, which has held protests in several cities across the country. Negasso estimated the crowd at 80,000 people, while Redwan said only a few hundred had gathered. The group, led by five people dressed in prison uniforms, chanted slogans demanding freedom and the release of prisoners, including UDJ member Andualem Arage who is serving a life sentence after he was convicted under the law. Rights groups have accused Ethiopia's anti-terrorism legislation of being vague and used to stifle peaceful dissent. Last year, two Swedish journalists jailed on terror-related offences were released after serving 13 months of their 11-year sentence.

watch ESAT Special on Ginbot 7 Meeting in Washington DC (Part 1)

Editor’s Note: On Sunday September 22, 2013, the Ginbot 7 leadership had a very revealing and open discussion in Washington DC meeting like it has never had before . As you know, the issue of working with Eritrea has been a bone in the throat for G7 as well as for its supporters around the world. Many have argued against using Eritrea as a spring board to wage an armed struggle against TPLF. Opponents claim that Eritrea can not be trusted based on their experience with Isayas Afeworki so far and his public rhetoric as it relates to Ethiopia. They may have a point. But the problem is that they don’t practice the position they defend or argue for. They don’t provide an alternative and actually implement that alternative. For example, they don’t answer to the question of where to wage an armed struggle and show us the way by an example. They don’t. For instance, what don’t they find a place within Ethiopia and wage an armed struggle? What do they go and practice what they preach instead of simply analyzing and arguing from the comfort of their homes in the West. What they do is simply disagree and sometimes with bitterness and even animosity against G7 position towards Eritrea. Instead of making an honest and logical attempt to convince and win our support, those who oppose G7′s position in Eritrea use intimidation, name callings, insults, put downs and inuendos to impose their opinion on G7 and its supporters. But the irony is that these forces claim to believe and fight for democracy in Ethiopia and yet they impose their position on others. G7 has repeatedly expressed the right of any political entity to follow a path it believes in without imposing its policy or belief on any one else except asking their support. G7 has often made clear that it does not oppose other political parties who pursue a political path different than its own. It is interesting whether we know how to win support with a clean logical argument backed by results in the ground instead of an endless ineundos and name callings. Those who opposes G7 are not all in the same wave length. Pro-TPLF mercenaries like Awramba Times editor are going against G7 to accomplish their paid assignments. There is no surprise about them. They are part of the package. There is also a second group that questions and suspects a multi-national political force like G7 for fear of revenge by TPLF victims in the form of genocide or a lesser nationwide violence against the Tigrian population. These group has a legitmate fear. But opposing such a political force as G7 is not a solution to their fear. In fact, a force such as G7, if strengthened, may help stabilize the country by preventing a possible chaos and ethnic violence in Ethiopia when TPLF collapses. And there is a third group. These are political organizations who are competing for power in Ethiopia after TPLF. They believe if they don’t cook the dish, it does not taste good. They want power at any cost and by any means necessary. They are ego-driven and uncompromising. Nothing satisfies them until they are in power to implement their belief. They oppose everything any opponent does. They deliberately or honestly believe that truth is on their side. Doing so is wounding their ego and it is relinquishing the possibility of power in Ethiopia. There is one final group which I consider innocent but suspicious. Our story with Eritrea is full of suspicions and actual heart-breaking experience due to the war waged between Ethiopia and Eritrea for over 40 years now. They don’t trust anything related to Eritrea no matter who said what including God. These group has a legitmate concern but suspicion should not tie our hands and prevent us from doing what needs to be done. Our situation today is desperate. TPLF has done and still doing all it can to destroy our people and country. These suspicioius group should know that there are times in life when you have to do what you got to do to get out of a rock and hard place by swallowing our pride and controlling our suspicion.There is a saying in our country,” ቀን እስኪአልፍልህ የአባትህ ባርያ ይግዛህ” that we should follow. These group has no alternative except to give it a try while holding its suspicions. At this point, all of us have one universal enemy. And we have to focus on it. And that is TPLF. And it is wise to talk about our differences after we free Ethiopia from TPLF by any means necessary. The G7 leadership has directly presented the question in a ‘take it or leave’ it manner to the audience and the Diaspora watching on ESAT. Berhanu and Andi 5 Click the image above to watch the G7 meeting in DC on September 22, 2013 Ato Andargachew Tsige, secretary of G7, has explained in detail about the Eritrean question during the meeting. It may be hard to tell if every body is convinced. With all their suspicions remaining, there is no doubt many may be considering to give G7′s policy on Eritrea a chance, if it has any possibility of working, given the dire and critical circumstances Ethiopia has found itself at this time. There is no sure thing in life as well as in struggle. You take chances and you take risks. Not a blind risk but a pragmatic one based on the circumstances you found yourself boxed in. Not taking that risk, no matter how difficult, is committing a self-inflicted suicide. You put all your options on the table. And you pick the one with the least risk. And then you move on. And if not, the choice is to get stuck in some meaningless and fruitless activity and continue to waste time, money and even lives for nothing and finally give up and be forgotten. G7 seems to have made a decision to take the least risky option, according to Ato Andargachew Tsige, and is pursuing it with resolve. And for those of us with an apposing view, let us do what we believe in without imposing our position on G7 and its policy towards Eritrea. According to Ato Andargachew Tsige, G7 is not imposing its position on any person or political entity. He said they don’t oppose the positions other political organizations are taking when it comes to Eritrea or any other political position. The take home message is that, we in the opposition camp, should all follow our individual political choices in our quest to remove TPLF from power without attacking each other. We all don’t have to come to the same conclusion. Let us just disagree without being disagreeable. There is no need to vehemently be involved in slash and burn campaign against a position we don’t agree on. First, it is not democratic. Second, it is nasty. We will sound like the dictators we claim to hate like Mensgistu and Meles. No one party or person has the monopoly on the truth of what works best to bring TPLF down. The only way to establish that truth is based on the results of a given policy on the ground. And let us all give a chance, with patience, to see what works with our suspicions still intact

Sunday, September 29, 2013

የግንቦት ሰባት ህዝባዊ ኃይል የገቢ ማሰባሰቢያ በተሳካ ሁኔታ ተጠናቀቀ!

ሰበር ዜና፣ የግንቦት ሰባት ህዝባዊ ኃይል የገቢ ማሰባሰቢያ በተሳካ ሁኔታ ተጠናቀቀ! Norway G7 fundrise http://ecadforum.com/Amharic/archives/9868/
ዛሬ ሴፕቴምበር 28 በኦስሎ ኖርዌይ ለግንቦት ሰባት ህዝባዊ ኃይል የታሳካ የገቢ ማሰባሰቢያ ተደረገ። በገቢ ማሰባሰቢያው ላይ በስጦታ እና ጨረታ ብቻ 408 ,633.85 የኖርዌጅያን ክሮነር የተገኘ ሲሆን ። ይህ ገቢ ከምግብ ሺያጭ ፣ ከመግቢያ ትኬት፣ ከቲሸርት ሺያጭ እንዲሁም ከተለያዩ ባህላዊ ቁሳቁሶች ሺያጭ ሳይጭምር መሆኑ ወዳጆችን ሲያስፈነድቅ ጠላቶችንን አንገት አስደፍቷል ። በፕሮግራሙ ላይ አቶ አንዳርጋቸው ጽጌ እና ኮማንደር አሰፋ ማሩ በመገኘት ከሃገር ወዳድ ኢትዮጵያዊያኖች ጋር ምክክር አድርገዋል። ሙሉ ዘገባውን በቅርብ ይዘን እንቀርባለን ። ኢትዮጵያ በክብር ለዘላለም ትኑር ! ከኖርዌይ

ESAT Special Program UDJ Sep 29, 2013 | ESAT Tube

ESAT Special Program UDJ Sep 29, 2013 | ESAT Tube

Freedom For Ethiopia , realize our political prisoners ,Justice ,equality ,TPLF is a corrupted party ,, .......

Manew Ashebare (Who is the Terrorist?!)

TPLF Shall dawn

Today September 29 2013 Addis Ababa serves big demonstration ,as usual Ethiopia people are united and protest TPLF with a great passion.

Today September 29 2013 Addis Ababa serves big demonstration under taken by opposition parties Ethiopian people are united and protest TPLF with a great passion. From the government side there is no one concerned and available  to hear  the people voice but  they used to ask as usual ...

The concept of the demonstration was
1-The government should not consider us like we are terrorist !!!! ,
2-The government should stop to involve in religion  ,
3-we do not want to be killed because of  ethnic ,
4-we are highly protest ethnic politics in our country ,
5-we do not allow the government officials to sell our land for foreigners ,
6-we need freedom of speech and freedom of press ,
7-we need to be released any political prisoners ,
8-we want the government to keep human right ,
9-we do not want our citizens to be killed and injured for noting ,......
are some of the points that people are mentioning in  protesting TPLF/ weyane

Saturday, September 28, 2013

የሞት “ድግስ” ለኢትኦጵ ጋዜጠኛ የስልክ ጥሪ ይደርሰውና .....

መስከረም 4 ቀን 1996ዓ.ም ለኢትኦጵ ጋዜጠኛ የስልክ ጥሪ ይደርሰዋል። “ በነገው እለት ከቀኑ 6ሰአት መስቀል አደባባይ በሚገኘው የትግራይ ልማት ዋና ቢሮ 4ኛፎቅ እንድትገኝ” የሚል ማስጠንቀቂያ አዘል ጥሪ ነበር የደረሰው። ከዛ በፊት ለስድስት ወር የአየር መንገድ የደህንነት ሃላፊ ሃይሌ ጋዜጠኛውን ሲያስጨንቀው፣ የተለያዩ የማግባቢያ ወይም መደለያ ሃሳቦችን ሲያቀርብለት ቆይቷል። መስከረም 2 ቀን ደግሞ በቀበሌ 06/07 መ/ር ቢሮ እንዲገኝ የሚገልፅ
መጥሪያ ቢደርሰውም በአጋጣሚ ጋዜጠኛው ስላልተመቸው አልሄደም። በማግስቱ የቀበሌውን ሊ/መ አቶ ቢሻው አበጋዝን ያገኘውና « ትላንት ፈልጋችሁኝ ነበር፤ ለምን ነበር?» ሲል ይጠይቀዋል፤ ቢሻውም « እኛ አይደለንም የፈለግንህ፤ ከደህንነት ቢሮ የመጡ ሰዎች ናቸው የፈለጉህ፤ ባለመምጣትህ ተናደው ነው የሄዱት፤ ለምን እንደፈለጉህ አልነገሩንም፤» በማለት መለሰ። …ከዛ በኋላ ነው - የመስከረም 4 ጥሪ የደረሰው፤ በማግስቱ በተባለው ቢሮ ተገኘ። ከ30 ደቂቃ ቆይታ በኋላ የማህበሩ ዳይሬክተር « ከሚፈልጉህ የበላይ አካላት ጋር አገናኝሃለሁ» በማለት ለጋዜጠኛው ተናግሮ በሚያሽከረክራት ኒሳን መኪና ተያይዘው ቦሌ በሚገኘው የደህንነት ቢሮ አመሩ።..ከአንድ ግዙፍና አስፈሪ ገፅታ ካለው ሰው ጋር ጋዜጠኛውን አገኛኝቶት ወጥቶ ሄደ። ..« እሺ ኢየሩሳሌም አርአያ..» አለ ንቀት በተሞላበት ሁኔታ፤ አስከተለና፥ « ወ/ስላሴ እባላለሁ፤ ....ከእኛ ባልደረባ ጋር ስትገኛኝ ነበር፤ መንግስት ብዙ አማራጮችን አቅርቦልህ..አንተ ግን አሻፈረኝ ብለሃል። ለመሆኑ የምታወጣቸው መረጃዎች ተፅፈው ነው የሚሰጡህ?...ለምንድነው መረጃ የሚሰጡህን የሕወሐት ሰዎች የማትነግረን?..የምናስራቸው፣ የምንጠይቃቸው መስሎህ ነው?...» ሲል ሹሙ ሲናገር፣ ጋዜጠኛው ግን የቀረቡትን መደራደሪያዎች እንደማይቀበል ተናገረ። ለሁለት ሰአት ተኩል ከደህንነት ሃላፊው ጋር ውዝግብ የተቀላቀለበት ቃላት ተለዋወጡ። በተለይ የደህንነት ሹሙ « ..የትግራይ ተወላጅ ያውም ቤተሰብህ አድዋ ሆነው..እንዴት ፀረ-ሕወሐት ትሆናለህ?..ከጠላቶቻችን አንዱ ከሆነው ኢትኦጵ ጋዜጣ ጋር እንዴት ትሰራለህ?..» እያለ ከመናገሩ በተጨማሪ « እንዳንተ የተለማመጥነውና የታገስነው የለም። ብንገድልህስ?..» ሲል በንቀት ሲጠይቅ፣ ጋዜጠኛውም « ምንም ጥያቄና መልስ አያስፈልገውም፤ አሁኑኑ ሽጉጥህን መዘህ ልታደርገው ትችላለህ። እኔ ብእር እንጂ የያዝኩት - ከጀርባዬ ያሰለፍኩት ሰራዊትና መሳሪያ የለም። ..ደግሞም ለስልጣን ያበቋችሁን 36ሺህ ታጋዮች ላይ ምን እንደፈፀማችሁ ስለማውቅ..» አላስጨረሰውም፤ ..« እሱ አይመለከትህም፤ ከማን ጋር ምን እያወራህ እንዳለህ እወቅ!?..ከዚህ በኋላ እንድታስብበት የ15 ቀን ጊዜ ብቻ ሰጥተንሃል። በነዚህ ቀናት አቋምህን አስተካክለህ፣ የተባልከውን ካልፈፀምክ ግን…እንገድልሃለን!! ማንም አያድንህም!! ጨርሻለሁ።» በማለት አምባረቀበትና አሰናበተው። ..ከአስራ አምስት ቀን በኋላ ረቡዕ መስከረም 20 ቀን 1996ዓ.ም ከምሽቱ 3፡30 ሰአት ገደማ በመኖሪያ ቤቱ አቅራቢያ ወ/ስላሴ ያሰማራቸው ሰባት የፌደራል ፖሊስ አባላት “አቦ ድልድይ” አቅራቢያ ጋዜጠኛውን ጥብቀው በያዙት ዱላ የቻሉትን ያክል ቀጥቅጠውና ከፍተኛ ጉዳት አድርሰው ወደ ድልድዩ ወረወሩት። ሶስት ጥርሱ ተሰበረ፣ ጭንቅላቱ 5 ቦታ ተፈነካከተ፤ ሁለቱ እጆቹ፣ ግራ እግሩ፣ ወገቡ፣..አጠቃላይ አካሉ ተጎዳ። ...እነ ወ/ስላሴ ከድርጊቱ በኋላ ለጋዜጠኛ ሲሳይ አጌና 5 ጊዜ ስልክ ደውለው « የኢየሩሳሌምን ሬሳ ሂድና ከምኒሊክ ሆስፒታል ውሰድ..» ሲሉ ተሳለቁ።…ከጨካኞች፣ ገዳዮችና አምባገነኖች ..የሚጠብቅ ፈጣሪ ከፍተኛ ጉዳት የደረሰባትን የጋዜጠኛውን ነፍስ በኪነ-ጥበቡ ታደጋት። እነሆ ከአስር አመት በኋላ የቀድሞ የደህንነት ሹም ወ/ስላሴ ወ/ሚካኤል እስር ቤት ሲወረወር፥ በእርሱ “ሞት የተደገሰላት” የጋዜጠኛው ነፍስ በህይወት ቆይታ ለማየት በቃች። ሁሉም የዘራውን ሊያጭድ ግድ ነው!! …ይህ ታሪክ የእኔ ነው። (በምስሉ የሚታየው ለስድስት ወር ያልጋ ቁራኛ የዳረገኝ የግድያ ሙከራ ከተፈፀመብኝ በኋላ፣ )

በማሰርና ማደናቀፍ የታጀበው ሰላማዊ ሰልፋችን በታቀደለት ዕለት በድምቀት ይካሄዳል!!!

– በአንድነትና በ33ቱ ፓርቲዎች በጋራ የተሠጠ ጋዜጣዊ መግለጫ አንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ ለሶስት ወራት የሚቆይ ህዝባዊ ንቅናቄ በስትራቴጅው መሰረት በመጀመር፤ በመላው አገሪቱ የሚገኙ አባላቶቹንና ደጋፊዎቹን በማንቀሳቀስ ሕዝቡን ያሳተፈ ትግል በአዲስ አበባና ከአዲስ አበባ ውጭ በሚገኙ ዋና ዋና ከተሞች የተቃውሞ ሰልፎችንና ህዝባዊ ስብሰባዎችን ማከናወኑ የሚታወቅ ነው፡፡ የሚልዮኖች ድምጽ ለነፃነት በሚል መሪ ቃል የተጀመረው ይህ ህዝባዊ ንቅናቄ አራት መሰረታዊ ጥያቄዎችንና ወቅታዊ ጉዳዮችን ያነገበ ሲሆን እንደ ሁልጊዜውም ፓርቲው ሰላማዊነቱን በጠበቀ መልኩ ነገር ግን ሕጋዊ መብቱን ሳያስነካ፤ መከፈል የሚገባውን መስዋዕትነት በመክፈልና በቁርጠኝነት ንቅናቄውን በታቀደለት መሰረት ከአባላቱና አመራሩ ጋር በመሆን ለማከናወን ችሏል፡፡ አገሪቱን በማስተዳደር ላይ የሚገኘው ገዥ ሀይል በሰላማዊ ህዝባዊ ንቅናቄዎች ለሚነሱ ጥያቄዎች አፋጣኝ ምላሽ ከመስጠትና በተነሱ ጉዳዮች ዙሪያ ለመነጋገር
በርን ከመክፈት ይልቅ ዙሪያ ጥምጥም በመሄድ ለጥያቄዎቹ አስተጋቢዎች የተለየ መልክ ለመፍጠር የሚያደርገው ሩጫ እንደተጠበቀ ሆኖ በህገ መንግስቱ በግልጽ የተቀመጡ ሰላማዊ ሰልፍ የማድረግ፣ የመሰብሰብና አቤቱታ የማቅረብ መብትን በአደባባይ እየጨፈለቀና እነዚህ መብቶች ይከበሩ ዘንድ የሚጠይቁ አባላቶቻችንን ከህግ አግባብ ውጪ በገፍ እያሰረም ቢሆን ህዝባችን ጋር ለመድረስና ተቃውሞ ድምፃችንን ከፍ አድርገን ማሰማት ችለናል፡፡ በጎንደርና ደሴ ከተማ በ7/11/2005 የጀመርናቸው የተቀውሞ ሰልፎች በባህርዳር፣ በአርባምንጭ፣ በጅንካ፣ በአዳማ፣ በፍቼ በተሳካ ሁኔታ የተካሄዱ ሲሆን በመቀሌና ባሌ ሮቤ በከፍተኛ ጫናና ህገወትነት ሳካሄዱ ቀርተዋል፡፡ በወላይታ ሶዶና አዲስ አበባ ህዝባዊ ስብሰባዎች ተከናውነዋል፡፡ ከላይ በጠቀስናቸው ከተሚች ሰላማዊ ሰልፎቹን ለማሰናከል ሃላፊዎቹ የየአካባቢዎቹን ሚሊሻዎች፣ የደንነት ሰዎች፣ ታጣቂዎችና ፖሊሶች በመጠቀም አባላቶቻችንን አስረዋል፣ አስፈራርተዋል፣ ደብድበዋል፣ አዋክበዋል፡፡ ከአንድ የመንግስት አካል በማይጠበቅ መልኩም አመራሮቻችንን አግተዋል፣ የተለጠፉ የሰላማዊ ሰልፍ ጥሪ ወረቀቶችን እንዲቀደዱ በማድረግና ህዝቡ በሰልፎቹ እንዳይገኝ በካድሬዎች አማካኝነት የቤት ለቤት ቅስቀሳ ከማካሄዳቸው በተጨማሪ የትራንስፖርት እንቅስቃሴ እንዳይኖር በማድረግ ከየከተሞቹ አቅራቢያ ከሚገኙ ወረዳዎች ዜጎች ድምጻቸውን ለማሰማት እንዳይመጡ እንቅፋት ፈጥረዋል፡፡ በተንቀሳቀስንባቸው አካባቢዎች ሁሉ ገዢው ፓርቲ ከህዝብ የተነጠለ መሆኑንና ህዝቡን እየመራሁ ነው የሚለው ህዝብን በማሸማቀቅ እንደሆነ መገንዘብ ችለናል፡፡ የመጀመሪው ዙር የሶስት ወር ሕዝባዊ ንቅናቄችን ከ33ቱ ፓርቲዎች ጋር በመሆን በአዲስ አበባ እንደሚጠናቀቅ በገለፅነው መሰረትም የተለያዩ እንቅስቃሴዎችንና ዝግጅቶቸን ስናደርግ ቆይተናል፡፡ በሕገ-መንግሥቱ አንቀጽ 3ዐ ተራ ቁጥር (1) መሰረት ዜጎች የመሰብሰብና በጋራ ሠላማዊ ሠልፍ ማድረግ እንደሚችሉ በተደነገገው መሠረት አንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትሕ ፓርቲ (አንድነት) በ24/12/2ዐዐ5 በተፃፈ ደብዳቤ ሕጉ የሚጠይቀውን አሟልቶ የተቃውሞ ሠላማዊ ሠልፍ መስከረም 5 ቀን 2ዐዐ6 ዓ.ም በመስቀል አደባባይ ለማድረግ መወሰናችንን ለአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የሠላማዊ ሠልፍ ማሳወቂያ ክፍል አሳውቀናል፡፡ ሆኖም በ12 ሰዓት ውስጥ መልስ ባለማግኘታችን ስለ ጉዳዩ ለማጣራት ከመስተዳድሩ የከንቲባው ጽ/ቤት ኃላፊ ጋር ተገናኝተን ሠፊ ውይይት ካደረግን በኋላ የጽሕፈት ቤቱ ኃላፊ በወቅቱ በመስቀል አደባባይ ለግንባታ ሥራ ተብሎ አካባቢው በቆርቆሮ የታጠረ ስለሆነ ጊዜ ተገኝቶ ቆርቆሮዎቹ ተነስተው ለጥበቃ አመቺ እስከሚሆን ድረስ የሠላማዊ ሠልፉ ከመስቀል በዓል በኋላ እንዲደረግ ስለጠየቁንና እንዲሁም የትምህርት ቤቶች መክፈቻ ወቅት ከመሆኑም በተጨማሪ በአካባቢውም ከአዲስ ዘመን መለወጫ ጋር በተያያዘ ብዙ ባዛሮች የሚስተናገዱበት ጊዜ በመሆኑ ጊዜው እንዲለወጥ የሚሉ ምክንያቶች በመቅረባቸው በመስቀል አደባባይ ለማድረግ የማንችል መሆኑን ቢነግሩንም በአደባባዩ ግን፡- 1ኛ. ነሐሴ 19 ቀን 2ዐዐ5 ዓ.ም የቀድሞ ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ ሙት ዓመት ምክንያት በማድረግ ሕዝባዊ ስብሰባና ሠላማዊ ሠልፍ የተካሄደበት መሆኑ፤ 2ኛ. ነሐሴ 26 ቀን 2ዐዐ5 ዓ.ም የኢትዮጵያ የኃይማኖቶች ተቋማት ጉባኤ ሠላማዊ ሠልፍ እንዳካሄዱበት እየታወቀ የተሰጡን ምክንያቶች ውሃ የማይቋጥሩና አድሏዊ መሆናቸውን ብናምንም ሆደ ሰፊ በመሆንና እስከመጨረሻው ለመሄድ በማሰብ ሠላማዊ ሠልፉ ወደ መስከረም 19 ቀን 2ዐዐ6 ዓ.ም እንዲተላለፍ አድርገናል፡፡ የአዲስ አበባ ከተማ መስተዳድር የከንቲባው ጽ/ቤት መስከረም 3 ቀን 2ዐዐ6 ዓ.ም ሠላማዊ ሠልፉን መስከረም 19 ቀን ማድረግ እንደምንችል ለዚሁ ተግባር በተዘጋጀው ቅጽ ሲያሳውቀን በቅፁ ላይ መሠረታዊ የሆነውን የሠላማዊ ሠልፉን የመዳረሻ ቦታ ክፍት (ዳሽ) በማድረግ ቀደም ስንል የተስማማንበት ቦታ መስቀል አደባባይን ሳይጠቀስ ቀረ፡፡ ፓርቲያችንም ይህ ተገቢ ያለመሆኑንና የመስተዳድሩን ተዓማኒነት የሚያሳጣው ስለሆነ ሠላማዊ ሠልፉን በመስቀል አደባባይ እንድናደርግ እንዲወሰንልን በተደጋጋሚ ብናሳስብም ተወያይተን መፍትሔ እንሰጣለን በማለት መልሱን በአስር ቀናት ከአዘገዩ በኋላ በቁ.አ.አ/ከጽ/1ዐ/3ዐ.4/12 ሠላማዊ ሠልፉን በጃንሜዳ እንድናደርግ መወሰኑን ገለፁልን፡፡ ሆኖም በዚህ ደበዳቤ መጨረሻ ላይ ‹‹… ከመስቀል አደባባይ ውጭ ሌላ አማራጭ ካላችሁ ማቅረብ እንደሚቻል እናሳስባለን›› ባሉት መሠረት የፓርቲው አመራር በጉዳዩ ላይ ሠፋ ያለ ውይይት ከአደረገ በኋላ ከላይ በጠቀስናቸው ምክንያቶች የተሰጠን መልስ በመስቀል አደባባይ ሠላማዊ ሠልፍ የማድረግ መብታችንን የጣሰ፣ የደፈጠጠ፣ ኢ-ፍትሓዊና አድሎአዊ መሆኑን ሙሉ በሙሉ ብናምንም አሁንም መስተዳድሩ እውነት ልማት አስጨንቆት ነው ወይስ ሰላማዊ ሰልፎችን በወረቀት ብቻ ዕውቅና በመስጠት ሌሎችን የማፈን ተግባር የሚለውን በተጨባጭ ለመፈተሽ የተፈቀደልን ጃንሜዳ በአዋጅ ቁጥር 3/1983 ዓ.ም ለሠላማዊ ሠልፍና የተከለከሉ ሥፍራዎች በሚለው አንቀጽ ሥር ‹‹ማንኛውም ሠላማዊ ሠልፍ ወይም ሕዝባዊ የፖለቲካ ስብሰባ በጦር ኃይሎች፣ በጥበቃና የሕዝብን ሠላምና ደህንነት በሚቆጣጠሩ የመንግሥት የሥራ ክፍሎች አካባቢ 5ዐዐ ሜትር ርቀት ውስጥ ሊደረግ አይችልም›› የሚለውን በመጥቀስ ጃንሜዳን የማንቀበልበትን ምክንያቶች አቅርበናል፡፡ በዚህም መሰረት፡- ሀ) በጃን ሜዳ ዋና መግቢያ በር ፊት ለፊት የመከላከያ ዩኒቨርስቲ በመኖሩ፤ ለ) በጃን ሜዳ ሁለተኛ በር የቀድሞ 3ኛ ሻለቃ ማዕከላዊ እዝ በመኖሩ፤ ሐ) በጃን ሜዳ 3ኛ በር የአራዳና የየካ ክፍለ ከተማ የፌዴራል መምሪያ የሚገኙ ስለሆነ ይህን ሥፍራ ለሠላሚዊ ሠልፍ መፍቀድ አዋጅን የሚጥስ በመሆኑ ትክክል እንዳልሆነ እና እኛም የሕግ ጥሰት ተባባሪ መሆን ስለማንፈቅድ መስከረም 13 ቀን በተፃፈ ደብዳቤ አማራጭ ይሆናሉ ያልናቸውን፡- • ኢትዮ ኩባ አደባባይ ፊት ለፊት • አራት ኪሎ አደባባይን • ስድስት ኪሎ አደባባይ • ቴዎድሮስ አደባባይ • አብነት ሆቴል ፊት ለፊት ያለው አደባባይ • ሳርቤት አካባቢ ያለው ፑሽኪን አደባባይ • ብሔር-ብሔረሰቦች አደባባይ • አዲስ አበባ ስቴድዩም • በቦሌ ድልድይና በኢምፔሪያል ሆቴል መካከል ከቀለበት መንገድ ግራና ቀኝ ያለው ሜዳ መሆናቸውን በመግለጽ ምላሽ በመጠባበቅ የቅስቀሳ ስራችንን በከፍተኛ ጫና ውስጥ ሆነን እያከናወንን እንገኛለን፡፡ በቅስቀሳ ወቅትም ከማክሰኞ መስከረም 15 ቀን 2006 ዓ.ም ጀምሮ በእቅዳችን መሰረት ከ 33ቱ ፓርቲ አመራሮችና አባላት ጋር በመሆን የመኪና ላይ ቅስቀሳ፣ በራሪ ወረቀ፣ ፖስተር መለጠፍ የጀመርን ቢሆንም የከተማው መስተዳድር ህግ በተላለፈ ሁኔታ ነሐሴ 10 ቀን 2006 ዓ.ም የሰላማዊ ሰልፍ ቅስቀሳ የሚከለክል የውስጥ መመሪያ በማውጣት ፓርቲዎች፣ ምርጫ ቦርድና ሚደዲው ሳያውቅ በድብቅ ለአዲስ አበባ ፖሊስና ክፍለ ከተሞች በማሰራጨት አባሎቻችንና አመራሩ ለቅስቀሳ ሲወጡ እንዲታሰሩ አድርጓል፡፡ በዚህ ህገ-ወጥ መመሪያ የተነሳም ማክሰኞ መስከረም 15 ቀን 2006 ዓ.ም ሦስት መኪናና አጠቃላይ 30 ቀስቃሽ አባላት ከቀኑ 5 ሰዓት ጀምሮ ታስረው ከምሽቱ 1 ሰዓት ተለቅቀዋል፤ ዕሮብ መስከረም 16 ቀን 2006 ዓ.ም ሦስት መኪናና 28 ቀስቃሽ አባላት በተመሳሳይ ታስረው ማታ ተለቅቀዋል፤ ሐሙስ መስከረም 17 ቀን 2006 ዓ.ም ሁለት መኪናና 16 ቀስቃሽ አባላት የታሰሩ ሲሆን የፓርቲያችን ሊቀ መንበር ዶ/ር ነጋሶ ጊዳዳ የታሰሩትን ለማስፈታ ወደ ሽሮ ሜዳ ፖሊስ መምሪያ ቢሄዱም የታሰሩ አባላት ካልተለቀቁ አልሄድም በማለት አብረው ታግተው ውለዋል፡፡ መስከረም 18 ቀን 2006 ዓ.ም የፓርቲው መሪ፣ የስራ አስፈፃሚ አባላትና አመራሩ በሁለት መኪና በመሆን አንደኛውን መኪና ዶ/ር ነጋሶ ጊዳዳ እየመሩት፣ ሁለተኛውን መኪና የተከበሩ አቶ ግርማ ሰይፉ እየመሩት ቅስቀሳ ቢጀመርም አጠቃላይ 26 አመራሮች በቁጥጥር ስር ውለው እንዳይቀሰቅሱ ተደርጓል፡፡ ፓርቲያችን በተለያዩ መንገዶች ቅስቀሳውን ማድረግ አጠናክሮ በመቀጠል ሁለት መቶ ሺ በራሪ ወረቀቶች ተሰራጭተዋል፤ አስር ሺ ፖስተሮች ተለጥፈዋል፡፡ ሕዝቡም በነቂስ ወጥቶ ሰላማዊ ሰልፉን በመቀላቀል በሰላማዊ መንገድ የተቃውሞ ድምፁን እንዲያሰማ በአክብሮት ሀገራዊ ጥሪ እናቀርባለን፡፡ በዚህም መሰረት መንግስት በወረቀት ብቻ እውቅና ሰጥቶ በተግባር ቅስቀሳ የከለከለ ቢሆንም የተቃውሞ ሰልፋችን በታቀደለት ዕለት ሠልፉ በምንም አይነት ጫና የማይሰረዝ መሆኑን እያረጋገጥን መነሻውን ከፓርቲያችን ፅ/ቤት በማድረግ የሚካሄድ መሆኑን እየገለጽን፤ አንድነት ለሠላማዊ ትግል የሚከፈሉ መስዋትነቶችንን ከፍሎ የትግላችንን ፍሬ እንደምናረጋግጥ እርግጠኛ ብንሆንም በአሁኑ ወቅት መንግሥት በማከናወን ላይ ያለው ተግባር ከሠላማዊ ትግል ውጭ ያሉ አማራጮችን በቀጥታ እያበረታታና እየደገፈ መሆኑን ማስገንዘብ እንወዳልን፡፡ በመጨረሻም የመንግሥት ተግባር መሠረታዊ የሆነ የዜግነትና የአገራዊ ባለቤትነት ጥያቄን ስለሚያስነሳ፤ አፈናው እንዲቆም በአገርና በሕዝብ ስም እየጠየቅን ይህን ፍርደ ገምድልና ኢ-ፍትሓዊ ውሳኔን ተከትሎ ለሚደርሱ ችግሮች ተጠያቂው መስተዳድሩና መንግሥት መሆኑ እንዲታወቅ አበክረን እንገልፃለን፡፡ ======================================= ዘላለማዊ ክብር ለኢትዮጵያ!!! የአንድነት ፓርቲና የ33ቱ ፓርቲዎች

Friday, September 27, 2013

“አማራ የኦሮሞ ሕዝብ ጠላት አይደለም፤ …ይሄ ፖለቲካ ለካ ላይ ላዩን እንጂ ውስጡ ጥሬ ነው” ጃዋር መሐመድ (ቃለ-ምልልስ) |...

No Human Rights = No Development

No Human Rights = No Development timthumb Oakland Institute and the Housing and Land Rights Network Submit Human Rights Report on Ethiopia to the United Nations OAKLAND CA- In a report submitted to the UN Human Rights Council’s Universal Periodic Review
(UPR) on September 15, 2013, the Oakland Institute and the Housing and Land Rights Network outlined the human rights and international law violations perpetrated by the government of Ethiopia in the name of country’s development strategy. Drawing clear links between recorded testimonies on the ground and breaches of specific international covenants and articles in Ethiopia’s constitution, the joint submission to the UN Human Rights Council also responds to Ethiopia’s draft National Human Rights Action Plan for 2013-2015. “Rather than working to build a development strategy grounded in human rights, the Ethiopian government is attempting to hoodwink its human rights record, leaving unmentioned its villagization program and the Anti-Terrorism Proclamation-both used by the government as significant justifications for forced resettlement, arbitrary detentions, and politically motivated arrests,” said Anuradha Mittal, Executive Director of the Oakland Institute. As previous Oakland Institute reports have chronicled, the Ethiopian government’s efforts to clear land for large-scale foreign investment has entailed widespread violations of human, social, economic, and political rights. Violations of citizen’s rights to self-determination, housing, land for subsistence production, and free political association–enshrined in the Ethiopian constitution, the Rural Land Administration and Land Use Proclamation, and in United Nations international covenants–are carried out in the name of development. The joint UPR submission suggests that the ruling party’s ability to implement country’s unpopular villagization program rests in its monopoly on force and dominance over the allocation of humanitarian assistance. “Authoritarian governance and the methods used in implementing development projects have combined to violate human rights to livelihood and culture for land-based peoples, especially in the peripheral regions,” said Joseph Schechla, Coordinator of the Housing and Land Rights Network. “Involuntary resettlement, a form of forced evictions, accompanies deprivation of the right to food, including the right to feed oneself, particularly for agropastoralists. On the other hand, the ability to control information and stifle dissent has enabled the ruling party to present a positive face to the international community, which has dubbed Ethiopia a nation in “renaissance”, he continued. The joint submission presents undeniable evidence that should compel the international community to advocate for a human rights centered development strategy that would benefit all Ethiopians. Download the joint Oakland Institute/HIC-HLRN submission

ሙስሊም ተማሪዎች አመጽ ጀርባ ሼክ ሙሀመድ አላሙዲን አሉበት ተባለ

የመንግስት የደህንነት መስሪያ ቤት ከወልድያ ሙስሊም ተማሪዎች አመጽ ጀርባ ሼክ ሙሀመድ አላሙዲን አሉበት አለ መስከረም ፲፮(አስራ ስድስት)ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-መንግስት ፣ “ኢህአዴግን የፈተነ ወሳኝ ክስተት” በማለት የገለጸውን የሙስሊሞች እንቅስቃሴ አልሻባብ፣ አልቃይዳ ፣ ግንቦት ሰባት ፣ እና የኤርትራ መንግስት እንደሚደግፉት በተደጋጋሚ በመገናኛ ብዙሀን ቢገልጽም፣ ለኢሳት የደረሰው መረጃ እንደሚያመለክተው ከሆነ ደግሞ የደህንነት ሀይሎች ቱጃሩን ሼክ ሙሀመድ ሁሴን አላሙዲንን ከእንቅስቃሴው ጀርባ እንዳሉበት የሚጠቁም መረጃ ለመንግስት ባለስልጣናት ማቅረቡ ታውቋል። በቅርቡ በወልድያ ከተማ የወልድያ ሙስሊም ተማሪዎች ባነሱት አመጽ መንገድ ዘግተው ወደ ላሊበላ ፤ ሰቆጣ ፣ ደሴ እና አዲስ አበባ የሚደረጉ የትራንስፖርት ጉዞዎች እንዲስተጓጎሉ ማድረጋቸው ይታወሳል፡፡ ከዚሁ ጋር በተያያዘ አመጹን አነሳስታችሁዋል የተባሉ 13 ታዳጊ ወጣቶች በእስር ላይ ይገኛሉ፡፡ የደህነነት ሐይሎች አጣራነው ባሉት መረጃ አመጹን ሼክ አላሙዲን ከጀርባ ሆነው ደግፈውታል። የኢህአዴግ አመራር እና የፌደራል ፖሊስ የጋራ የጸረ ሽብር ግብረ ሐይል በጉዳዩ ዙሪያ በሰፊው ውይይት ካደረጉበት በኃላ ፣ በባለሀብቱ ላይ እርምጃ ለመውሰድ ባይቻልም በወዳጆቻቸው በኩል ምክር አንዲሰጣቸው በአቶ በረከት ስምኦን የሚመራ አንድ ቡድን መዋቀሩን ለማወቅ የደረሰን መረጃ ያመለክታል። ሼክ አላሙዲን ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ከታክስ እና ከግንባታ ጋር በተያያዘ ከመንግስት ጋር ውዝግብ ውስጥ መግባታቸው ይታወቃል። የደህንነት መስሪያ ቤት በባለሀብቱ እንቅስቃሴ ዙሪያ መረጃ እንዳገኘ ቢገልጽም፣ መረጃውን እንዴት እንዳገኘው አልታወቀም። አንዳንድ ወገኖች ግን የሼክ አላሙዲን ከህግ በላይ መሆን ያሳሳበው መንግስት፣ አጋጣሚውን በመጠቀም ባለሀብቱን ለመምታት የፈጠረው ዘዴ ሊሆን ይችላል ይላሉ። በጉዳዩ ዙሪያ ሼክ አላሙዲንን ወይም ወኪሎቻቸውን ለማግኘት ተደጋጋሚ ሙከራ ብናደርግም አልተሳካልንም። ሼህ አሊ አላሙዲን ለኢህአዴግ ከፍተኛ የገንዘብ ድጋፍ እንደሚያደርጉ ይታወቃል። source https://www.facebook.com/justiceallethiopian

ስበር ዜና – አንድነት ፓርቲ ከፍተኛ አመራሮችና አባላት ታሰሩ!

የአንድነት ፓርቲ ሊቀመንበር ዶ/ር ነጋሶ ጊዳዳ ዛሬም ታግተው ወደ አራዳ ፓሊስ ጣቢያ ተወስደዋል፡፡ አብረዋቸው የታሰዩት አመራሮችና አባላት እንደሚከተለው እንዘረዝራለን !በፖለስ የታሰሩ አመራሮችና አባላት በከፊል ዶ/ር ነጋሶ ጊዳዳ – የአንድነት ፓርቲ ሊቀመንበር የተከበሩ ግርማ ሰይፉ – የአንድነት ፓርቲ ሊቀመንበር አቶ ስዩም መንገሻ – የድርጅት ጉዳይ ኃላፊ አቶ ዳንኤል ተፈራ – የህዝብ ግንኙነት ኃላፊ አቶ አስራት ጣሴ – ዋና ጸሃፊ አቶ ተክሌ በቀለ – የፋይናንስ ጉዳይ ኃላፊ አቶ ሽመልስ ሃብቴ – የማህበራዊ ጉዳይ ኃላፊ አቶ ሃብታሙ አያሌው – የህዝብ ግንኙነት ም/ኃላፊ አቶ ብሩ በርመጂ – የብሔራዊ ምክር ቤት አባል አቶ አበበ አካሉ – የብሔራዊ ምክር ቤት አባል አቶ እንግዳ ወ/ፃዲቅ – የብሔራዊ ምክር ቤት አባል አቶ አለባቸው ነጋሽ – አባል አቶ መካንንት ብርሃኑ – አባል አቶ እንዳልካቸው ባዩ – አባል አቶ ብስራት ተሰማ – አባል አቶ ወንደሰን ክንፉ – አባል አቶ ኃይሉ ግዛው – አባል አቶ ደረጀ ጣሰው – አባል አቶ ገዛህኝ – አባል አቶ ባዩ ተስፋዬ – አባል አቶ ወርቁ – አባል

Thursday, September 26, 2013

Abigail Salisbury is an enemy of the state of Ethiopia

by Cristina Holtzer Source: The Pitt News Ethiopia bans access to student’s critical article Abigail Salisbury is an enemy of the state of Ethiopia because of an op-ed column she published online. Salisbury, a student in the Graduate School of Public and International Affairs, spoke about her article to an audience of about 10 in a “Let’s Talk Africa” lecture on Wednesday in 4130
Posvar Hall from 1:30 to 3 p.m. The Ethiopian government blocked her article, titled “Human Rights and the War on Terror in Ethiopia,” one day after she published it online. While in Ethiopia, Salisbury noticed an extreme lack of freedom of speech and press for Ethiopian people and decided to write the piece, which criticizes the Ethiopian government. Salisbury was working as an assistant professor at Mekelle University Law School, a small college outside of Addis Ababa, the capital of Ethiopia, when she published the article. After the university administration discovered her article, Salisbury said the university “basically asked [her] not to work there anymore.” “I was told that, based on what I wrote, that if I had been an Ethiopian person, I would have been put in prison,” Salisbury said. “I don’t think they want me back.” Ironically enough, Salisbury said, she was in the country teaching international human-rights law, a class required for graduation from law school in Ethiopia. Anna-Maria Karnes, a representative of the Africana studies department, also attended the lecture and interjected throughout. Karnes, whose parents live in Ethiopia, has a thorough grasp of the political climate in the country. “Skype was outlawed two years ago in Ethiopia,” Karnes said. “There were people jailed for using Skype.” When Karnes first discovered the Skype law, she worried that she would not be able to get in touch with her parents because that was their primary source of communication. But Skype was illegal only for Ethiopians, not for foreigners. “As a Westerner, you are treated differently,” Salisbury said. “Better.” Ethiopians subscribe to a different race and caste system than many Americans are used to. Salisbury said that when African-Americans traveled to Ethiopia, they were treated the same as whites. Ethiopians believe that everyone else in Africa is black but that they, themselves, are red skinned. Salisbury recounted a story of when someone in the street approached her and asked, “Have you seen any black women today?” Salisbury said she was surprised by the scale of differences between the learning environments in Ethiopia and the U.S. Because of the country’s limited resources, students learn to memorize verbatim what professors say in lecture. Salisbury said she’s seen students reproduce a lecture right down to the “ums” and “likes.” Ethiopian education also differs from Western education because, Salisbury said, there could be “watchers” present at any time, in any classroom. Watchers are government representatives on the lookout for those speaking out against the government. “What would creep me out if I were in that class?” Salisbury said. “I don’t know if I would be raising my hand with opinions.” In addition to an extreme lack of freedom of speech, Salisbury said Ethiopians also struggle with tough racial tensions and “ethnic federalism,” or preferential treatment for one ethnic group that is officially recognized by the government. With Ethiopia located in a contentious part of the world, Salisbury said U.S.-Ethiopia relations are crucial. “Ethiopia is really instrumental in the U.S. agenda and the global war on terror that we’re engaged in,” she said. Salisbury and Karnes opened the presentation with an activity about African knowledge. They divided the audience into small groups and asked them to label a map of Africa with the names of as many countries as they could. Even with several African students and faculty in the audience, no one was able to label the entire map. “You can’t know the whole of Africa,” Director of Africana Studies Macrina Lelei said. “That’s part of why we have African studies here at Pitt … to share those experiences.”

አንድነት ሰላማዊ ሰልፉን ለማካሄድ አራት አደባባዮች በአማራጭነት አቅርቦ እየተነጋገረ ነው

አንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ (አንድነት) መስከረም 19 ቀን 2006 ዓ.ም በመስቀል አደባባይ ጠርቶት የነበረው ሰላማዊ ሰልፍ የከተማው አስተዳደር በአደባባዩ ዙሪያ ኮንስትራክሽን እየተከናወነ ስለሆነ አደባባዩ ማንኛውንም ሰልፍ ስለማያካሂድ ጃንሜዳ በአማራጭነት በማቅረቡ የአንድነት ሰልፍ በመስቀል አደባባይ ማካሄድ አስቸጋሪ ሁኔታ መፈጠሩን ፓርቲው አስታወቀ። የከተማው አስተዳደር የአዋጁን አንቀጾች ጠቅሶ ፓርቲው በመስቀል አደባባይ ሰልፍ ማካሄድ እንደማይችል በመግለፅና አማራጭ አማራጭ እንዲያቀርብ መጠየቁ፤ ከጃንሜዳ እና ከመስቀል አደባባይ ውጪ ሌሎች አራት አደባባዮች በአማራጭነት አቅርቦ
ከአስተዳደሩ እየተነጋገረ መሆኑን የፓርቲው የብሔራዊ ምክር ቤት ዋና ፀሐፊና የሕዝባዊ ንቅናቄ ግብረ-ኃይሉ ፀሐፊ አቶ ትዕግስቱ አወሉ ለሰንደቅ ጋዜጣ ተናግረዋል። ፓርቲው መስቀል አደባባይ የተከለከለበት ሂደት አሳማኝና ሞራላዊ ባይሆንም ፓርቲው እራሱ መስቀል አደባባይን ጨምሮ ሌሎች አራት አደባባዮችን በአማራጭነት ለማየት ከአዲስ አበባ አስተዳደር ጋር ለመነጋገር መገደዱን ገልፀዋል። ፓርቲው በአማራጭነት ያቀረባቸው አደባባዮች የኢትዮ-ኩባ ወዳጅነት አደባባይ፣ ቴዎድሮስ አደባባይ፣ አራት ኪሎ እና ስድስት ኪሎ አደባባዮች መሆናቸውን በመጥቀስ ከተቻለ የአዲስ አበባ ስታዲዬምም እየታየ መሆኑን አመልክተዋል። ቀደም ሲል ሰልፉን ቀበና ከሚገኘው የፓርቲው ጽ/ቤት መነሻ የማድረጉን ነገር በመቀየር ከተመረጡ ክፍለ ከተሞች ከተለያዩ ቦታዎች ወደ አደባባዮች ሕዝቡ እንዲሰባሰብ መወሰኑን ገልፀዋል። ፓርቲው በሰልፉ ይሳተፋል ብሎ የገመተው ግማሽ ሚሊዮን ሕዝብ በላይ ከአደባባዮቹ ስፋት ጋር ባይመጣጠንም ሰልፉ በጎዳናዎቹ ላይ ጭምር የሚከናወን መሆኑን አመልክተዋል። አንድነት ፓርቲ ጃንሜዳ ላይ ሰልፉን የማያካሂደው በሁለት ምክንያት መሆኑን አቶ ትዕግስቱ ገልፀዋል። የመጀመሪያው በሰላማዊ ሰልፍ አዋጅ ቁጥር 3/1983 ዓ.ም አንቀፅ 7 ንዑስ ቁጥር 2 መሠረት ሰላማዊ ሰልፍ መካሄድ ያለበት ከጦር ካምፓች ቢያንስ 500 ሜትር ርቀት ላይ ነው። ነገር ግን ጃንሜዳ በመቶ ሜትር ርቀት ላይ ትልቅ የጦር ካምፕ በመኖሩ በቀጥታ አዋጁን መጣስ ነው የሚሆነው። ሁለተኛው ምክንያት ቦታው ሣር የበቀለበት ረግረጋማ ስፍራ በመሆኑ በአጠቃላይ ጃንሜዳ ሰላማዊ ሰልፍ ለማካሄድ ከሕግም ሆነ ከአመቺነት አንፃር ተመራጭ ባለመሆኑ ነው ብለዋል። “ሰልፉ በምንም አይነት አይቀርም” ያሉት አቶ ትዕግስቱ አንድነት ፓርቲ የሕዝቡን መብት በድርድር እየጠየቀ አይደለም ብለዋል። ስርዓቱ ፍፁም አምባገነናዊ ስርዓት በመሆኑ አንድነት የተገኘውን ቀዳዳ ሁሉ ሰላማዊና ዲፕሎማሲያዊ በሆነ መንገድ እንደሚያስኬድ ገልፀዋል። “አንድነት ሰላማዊ ትግሉን ከዲፕሎማሲያዊ ድርድር ጋር ይዞ ነው የሚሄደው” ያሉት አቶ ትዕግስቱ፤ በሰልፉ ቦታ ላይ ከመንግስት ጋር መደራደሩ ለመንግስት የመንበርከክ ጉዳይ አይደለም ብለዋል። ለጊዜው የሰልፉ ቦታ ባይለይም ኅብረተሰቡ በሰልፉ ላይ እንዲሳተፍ በሦስት ተሽከርካሪዎች የጎዳና ላይ ቅስቀሳ መደረጉን፣ በቤት ለቤት፣ በማኅበራዊ ድረ ገጽ በሌሎች የመቀስቀሻ መንገዶች ቅሰቀሳ እየተካሄደ መሆኑን ተናግረዋል። እንዲሁም ለንግዱ ማኅበረሰብ በልዩ ሁኔታ ጥሪ መደረጉን ገልፀዋል። በተጨማሪም በከተማዋ ውስጥ የሚገኙ መዋቅሮች ስልጠና ተሰጥቷቸው በእንቅስቃሴ ላይ መሆናቸውን ጠቅሰዋል። ሰላማዊ ሰልፉ የ1997ቱ ሰልፍ የሚያስታውስ ሰልፍ እንደሚሆን ተስፋ መኖሩን አመልክተዋል። በሰልፉ ላይ ለመነሻ ያህል አምስት መቶ ሺህና ከዚያ በላይ ሕዝብ የሚሳተፍ ቢሆንም፤ በመንግስት በኩል ፓርቲው የተቃውሞ ሰልፍ በጠራበት ዕለት በተመሳሳይ በየትምህርት ቤቱ የወላጆች ስብሰባ መጥራቱ አግባብ አለመሆኑንም አቶ ትዕግስቱ ተናግረዋል። የወላጆች ውይይት መስከረም 5 ቀን 2006 ዓ.ም ቀደም ሲል አንድነት ሰልፍ በጠራበት ዕለት ተጠርቶ የነበረ ቢሆንም፤ ባልታወቀ ምክንያት ወደ መስከረም 19 ቀን 2006 መቀየሩ ሆን ተብሎ የፓርቲው ሰልፍ ላይ እንቅፋት ለመፍጠር ነው ብለዋል። ሰልፉ የፍትህና የነፃነት ጥሪ መሆኑን ያስገነዘቡት አቶ ትዕግስቱ የፀረ ሽብር ሕጉ እንዲሰረዝ፣ የኑሮ ውድነቱና ስራ አጥነት እንዲቀረፍ፣ የታሰሩ ጋዜጠኞችና የፖለቲካ መሪዎች እንዲፈቱ፣ በልማት ስም የዜጎችን መፈናቀልን የሚቃወምና መብቱን የሚጠይቅ ማንኛውም ኅብረተሰብ እንዲካፈል ጥሪ መቅረቡን አመልክተዋል። የሙስሊሙ ማኅበረሰብ ጥያቄ ከፀረ-ሽብር ሕጉ በተለየ ሁኔታ የሚያያዝ በመሆኑ ሕጉ እንዲሰረዝ ፍላጎት ካላቸው ጎን ይቆማሉ የሚል እምነት እንዳለ ጠቅሰዋል። በሰልፉ ላይ መኢአድ ከአንድነት ፓርቲ ባልተናነሰ ሁኔታ በሰልፉ መሳተፉንና 33ቱ ፓርቲዎች ንቁ ተሳትፎ እያደረጉ መሆኑንም ጠቁመዋል። አንድነት ፓርቲ ከተመሠረተ አራት ዓመት ቢሆነውም የቀድሞው ሊቀመንበር ወይዘሪት ብርቱካን ሚደቅሳ እንዲፈቱ 250 ሰዎች የተካፈሉበት ሰልፍ ማድረጉ አይዘነጋም። ባለፉት ሦስት ወራትም በተለያዩ የሀገሪቱ ከተሞች “የሚሊዮኖች ድምፅ ለነፃነት” በሚል መሪ ቃል ሰልፎችና ሕዝባዊ ውይይት ማድረጉም አይዘነጋም::

እንደ ቆራጥ ንስር ፓይለቶቹ…

ባለፈው ሳምንት በኢትዮጵያውያን ዘንድ ዋና የመነጋገሪያ አርዕስት የነበረው አራት የአየር ሃይል አብራሪዎችና አስልጣኝ መኮንኖች ከዘረኞቹና ከዘራፊዎቹ ጎራ ወጥተው ወደ ነፃነት ታጋዮች ጎራ የመቀላቀላቸው ጉዳይ ነበር። እነዚህ ቆራጥና አገር ወዳድ አብራረዎች የወሰዱት እርምጃ ወገንን የሚያኮራና ከፍተኛ ጀግንነትን የሚጠይቅ ትልቅ ውሳኔ ነው።ይህ ውሳኔ ሰው ባጣች አገር፤ጀግና ባጣች አገር፤ለአገር ለወገን ተቆርቋሪ ባጣች አገር ውስጥ ትልቅ ተስፋ ሰጪ ነው። የኢትዮጵያ ህዝብ በያለበት በተለያየ መንገድ ይህን የጀግና ውሳኔ የወሰኑ ልጆቹን እያደነቀም እያመሰገነም ይገኛል:: የግንቦት ሰባት ንቅናቄም ይህን የጀግና ውስኔ የወሰኑ ወንድሞቹን እንኳን ተወለዳችሁ፤ እንኳንም ተማራችሁ፤ እንኳንም ወደ ነፃነቱ ትግል ተቀላቀላችሁ እያለ ደስታውንና ለጀግኖቹ ያለዉን ከፍተኛ አክብሮት ይገልፃል። ውሳኔያችሁ ከፈርዖን ቤተ-መንግስት ምቾት ይልቅ ከህዝቤ ጋር መሰደደ ይሻለኛል ያለውን የታላቁን ሰው የሙሴን ውሳኔ ይመስላልና የወሰዳችሁትን ትክክለኛ እርምጃ ትውልድ ምን ግዜም አይረሳዉም። የእነዚህ ቆራጥ የኢትዮጵያ ህዝብ ልጆች፣ ሙያና ችሎታ ስጋዊ የሆነ ፍላጎታቸውን ለማርካት ከበቂ በላይ ነው።ከዘረኞቹና ከቃየላውያኑ ቡድኖች ጋር እየተሞዳሞዱ ለመኖርም የሚሳናቸው አልነበሩም።ሆኖም ግን ዘረኞቹ(ህወሃቶች) የሚፈፅሙትን ግፍ ተሸክመው ፤ብኩርናቸውን ሽጠው እና ከሰው ተራ ወርደው ለመኖር ሂሊናችው አልፈቀደላቸውም።ለሚበላና ለሚጠጣ ከንቱ ነገር ብለው ጥቂት ዘረኞችን ተሸክሞ ከመኖር ይልቅ የነፃነቱን መንገድ መርጠዋልና ጀግኖች ብለን ብናወድሳቸው ተገቢ ይሆናል። እንዲህ ዓይነቱን ውሳኔ የሚወስን ሃሞተ ኮስታራ ጀግና እንጂ ሌላ አይደለም። አሁንም ለራሳችሁ ክብር ያላችሁና ተመሳሳይ እርምጃ ለመዉሰድ በዝግጅት ላይ የምትገኙ የአገር መከላከያ አባላት እንዳላችሁ እናውቃለን። ቅምጥሎቹ ጄኔራል ተብየዎች ከድሃ ወገኖቻችሁ ላይ የዘረፉትን
ዘርፈው አገሪቷን ጥለው መሄድ ጀምረዋል። ቀሪዎችም የዘረፉትን የድሃ ንብረት ወደ ውጪ አገር እያሸሹ እንደሆነም ይታወቃል።በአጠቃላይ በእናንተ ምርኩዝነት አገራችንን እያፈራረሷት፤ህዝቧንም እያወረዷት ነው።የህዝቡም መከራና እሮሮ ተወርቶ የሚያልቅ አይደለም።እንዲህ አይነቱን ግፍና በደል እያዩ ከንፈር መምጠጥ እያበቃ ነው።እንግዲህ አሁን እኔ ብቻየን ምን አደርጋለሁ የሚባልበት ግዜ እያለፈ ነው።ጋሻ መከታ እና የኋላ ደጀን የሚሆኗችሁ ብዙ አገር ወዳድ ኢትዮጵያዉያን በየቦታው አሉ።ብትወድቁ የሚያነሷችሁ፤ብትደሙ ደማችሁን የሚያብሱላችሁ፤ብትሰው መስዋእትነታችሁን ለትውልድ የሚዘክሩላችሁ ወገን አለላችሁ።አትፍሩ። ከዘረኞቹ መንደር ወጥታችሁ የነፃነቱን ትግል እንድትቀላቀሉ ወገናዊ ጥሪያችንን እናቀርብላችኋለን። ህውሃት ማለት የዘራፊዎች እና የጨካኝ ነፍሰ ገዳዮች ስብስብ መሆኑን ያለምንም ጥርጥር ማመን አለባችሁ።ህወሃት ስንቱን አርዶ፤ስንቱን ገድሎ፤ስንቱን አጥፍቶ፤የስንቱን ኑሮ በትኖ፤ስንቱን ዘርፎ ባዶ እጁን አስቀርቶ በትረ ስልጣኑን እንደያዘ ምስክር የሚያስፈልገን አይደለም። የህውሃት ዘረኝነትና ዝሪፊያ የቆጨህ እና ለራስህ ክብር ያለህ ኢትዮጵያዊ ሁሉ ተነስተህ ትግሉን ተቀላቀል።እነዚህን ግፈኞች የሚፈፅሙትን በደል እያዩ ዝም ማለት ግፉን ከመደገፍ ተለይቶ የሚታይ አይደለም።እናንተ ለራሳችሁ፤ ለወገናችሁና ለአገራቸችሁ ክብር ያላችሁ ዜጎች ዝም በማለታችሁ ህወሃቶች ዝምታችሁን እንደ በጎ ፈቃድ ቆጥረውት የግፍ ሰይፋቸውን ወደ ሰገባው ሊመልሱ ፈቃደኞች አልሆኑም።በማን አለበኝነታችውም ፀንተው ቆመዋል።እነዚህን ግፈኞች በቃ ለማለት ግዜው ደርሷልና የነፃነቱን ትግል ሳትዘገዩ አሁኑኑ ተቀላቀሉ። እኛም ወደ ነፃነት ትግሉ እንድትቀላቀሉ ጥሪ ስናደርግላችሁ ለአገራችን ክብርና ለወገኖቻችን በሰላም መኖር ስንል ቆርጠን የተነሳን መሆናችንን ልንገልጽላችሁ እንወዳለን።የግንቦት ሰባት ንቅናቄ በምንም ሁኔታ በዘረኞች እጅ ተንቆና ተዋርዶ መኖርን አይቀበልም።እንዲህ ዓይነቱን ውርደት ተቀብሎ ለመኖር ሰው መሆናችን ይከለክለናል።እነዚህን ዘራፊዎች ተሸክመን ከመኖር ከነፃነታችን ጋር አያቶቻችን በተሰውበት ተራራ ላይ ቆመን መሰዋትን እንመርጣለን።አሁን ተነስተናልና የሚያቆመን የለም። እግዚአብሄርም መንገዳችንን ያከናውንልናል። ኑ ሀገርን ለማዳን የነጻነት ትግሉን ጎራ ተቀላቀሉ። ድል ለኢትዮጵያ ህዝብ!!

Wednesday, September 25, 2013

the political movement around arat kilo area done by andnet party members and supporters


አማራወች አሁንም በዘራቸውም ምክንያት እየተፈናቀሉ ነው።voa Amharic አርብ 10/01/2006 ከዘገበው


Public meeting highlights by Ginbot 7 at Washington DC,...

Public meeting highlights by Ginbot 7 at Washington DC,... Ginbot 7 chairman Dr. Birhanu Nega and secretary general Andargachew Tsige

Previous Ethiopian president /Negaso Gidada is injeld because of the party members .

Addis Ababa police announce about the Previous Ethiopian president /Negaso Gidada police announced about the Previous Ethiopian president /Negaso Gidada that he is injeld because of the party members .

Negaso Gidada the president of united for democracy and Justice party ( የአንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ ፕሬዘዳንት ) went to request the branch of Shiromed police found at Gulele Kifle Ketema about the political prisoners to be realised. previous president Negaso Gidada was asking the police to release the prisoners Because the party's members are not commit any crime other than running political propaganda which is already allowed and licensed by the government . What if he is complaining about, the police is not willing to realise those prisoners. However the party is licensed, the police is convinced that there political movement is illegal. After long debate the police is convinced to prison Ethiopian president /Negaso Gidada because he said that he sent the party members for running such political propaganda and realise the members of united for democracy and Justice party( የአንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ ፕሬዘዳንት ) .

Tuesday, September 24, 2013

TPLF Officials are happy for Proclamation on anti terrorism to control and punish any opposition parties movement ...

TPLF Officials are happy for  Proclamation on anti terrorism to control and punish any opposition parties movement  ...

According to the previous Ethiopian pray minister Meless Zenawi , the  Proclamation on anti terrorism is directly word by word copied from three best sources from USA patriot Act of 2001 , UK Terrorism Act 2000, and from council frame work / European Union model Law. when he explain the reason why they decide to copied directly , according to Meless Zenawi Tplf officials afraid  they will be accuse by westerns for non democratic ruling . It is so obvious why he mention such point ...  because he knows why they needs the Proclamation on anti terrorism . As usual tplf plan is clear ,to cover by paper low and to attack the real protesters.

The main actor and roller for terrorism and related criminals are TPLF .May be this Proclamation on anti terrorism is useful or important to punish Tplf officials only. Because currently the only one who are terrorizing in Ethiopian is Tplf and its officials . Also human right watch says lot about Ethiopian Proclamation on anti terrorism " The anti- terror law it self is a huge problem" by Rona Peliga Deputy Africa Director .

Basically,  Proclamation on anti terrorism is not stands for the citizen's of Ethiopian only for TPLF because Tplf  needs this anti terrorism proclamation very much .that  is only to avoid and erase any of Tplf positions from Ethiopia . from the beginning , to protest and to be terrorist are very different .
If Proclamation on anti terrorism believed like as it is essential for Ethiopia , it should be proclaimed only for the well being of the society and country . should not be proclaimed  to keep the well being and Power of  Tplf Political  agenda .

Besides any of Proclamation should be on the top or on the above .. to Judge every of citizens in the country ( weather the person is government official or normal civil person ) . But the current reality is very different .Tplf leaders with there members are above any Law , they are killing any one any time they want  , they are corrupted  ,.... Those Tplf officials who are always above any of Law in the country ,should be accused for there criminal acts  .But unfortunately  because the court is not clean from TPLF politics no one can ask and accuse them for there terrorism and related criminal murder .

To protest and to be terrorist are very different .To mention one simple example ,as Ethiopia is  there personal commodity TPLF officials are selling and offering our land to the market for foreigners , for the sack of their private issue. may be TPLF politician are dreaming in stopping opposition ,But how ?

people need freedom of speech and freedom of press , people need to be released any of political prisoners ( Eskinder Nega , Andualem Arage , Riot alemu , Debteraw  .... )  ,people want the government to keep human right , people do not want there citizens to be killed and injured for the sack of TPLF happiness  and elongation of  power, Ethiopian people need democracy ,  human right violation  should be stopped etc .. people have many  reason in protesting TPLF/ weyane


Ethiopian needs a government which is elected by citizens ,TPLF is a group which is not represent the hole part of all Ethiopia . TPLF has no right even to design any rule and regulation in our land . more over TPLF policy are connected with ethnic politics . In Ethiopia any one can see the reality that Ethiopians refuse to give recognition or value  for ethnic politics .
No no can stopped the people from protesting Unless they got freedom ,if asking freedom is concisered like terrorism , may be 90 million Ethiopian People will be terrorist by TPLF Officials .
by Metasebia Tadesse

15 የሚሆኑ የአንድነት ፓርቲ አባለት ዛሬ ህገወጥ እስር ተፈፀመባቸው የተቀሩት ስኬታማ ቅስቀሳ በማድረግ ላይ ናቸው

አንድነት ፓርቲ በመጪው እሁድ መስከረም 19 ከ33ቱ ፓርቲዎች ጋር ለሚያደርገው ሰላማዊ ሰልፍ የመኪና ላይ ቅስቀሳ ሲያደርጉ የነበሩ 15 አባላቱ ህገወጥ እስር ተፈፀመባቸው፡፡ አባላቱ ከስድስት ኪሎ ወደ አራት ኪሎ በሚወስደው ጎዳና በመኪና ላይ እየቀሰቀሱ ባለበት ወቅት ሚኒሊክ ት/ቤት ፊትለፊት የፖሊስና
የደህንነት ኃይሎች የሚተላለፈውን መኪና መንገድ በመዝጋት ቅስቀሳውን አደናቅፈዋል፡፡ በስፍራው የነበሩ በርካታ ሰዎች “ቀስቃሾቹ ህጋዊ ወረቀት ይዘዋል፤ልቀቋቸው” በማለት ተቃውሞ አሰምተዋል ከአንድነት ፓርቲ ጎን እንደሚቆሙም ተናግረዋል፡፡ ፖሊስ 15 የሚሆኑትን የቅስቀሳ ቡድን አባላት ወደ ሁለተኛ ፖሊስ ጣቢያ ወስደዋቸዋል፡፡ የአንድነት ፓርቲ ከፍተኛ አመራሮች አባላቱ ወደ ታሰሩበት 2ኛ ፖሊስ ጣቢያ በመሄድ ረ/ኢ መንግስቱ ለማ የተባሉትን የፖሊስ ጣቢያው ኃላፊ የታሰሩት አባላት እንዲለቀቁ ጠይቀዋል፡፡ ኃላፊውም “ህጋዊ ሰልፍ እንደምታደርጉ እናውቃለን ይቀስቅሱ የሚል መመሪያ አልደረሰንም ብለዋል፡፡ አመራሮቹ የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽነርንና የከተማዋን መስተዳድር ሃላፊዎች ለማነጋገር ተንቀሳቅሰዋል፡፡ በተለያየ አቅጣጫ የተሰማሩት ሌሎቹ የአንድነት ፓርቲ ቅስቀሳ ቡድን አባላት ስኬታማ የመኪና ላይ ቅስቀሳ በማደረግ ላይ ናቸው፡ source http://freedom4ethiopian.wordpress.com/2013/09/24/6761/ posted by Aseged Tamen e

Azeb Mesfin arrest imminent

EthiopianReview.com | September 24th, 2013 Azeb MesfinAzeb Mesfin, the widow of Ethiopia’s deceased dictator, is facing multiple charges of corruption and her arrest is imminent unless she leaves the country, according to Ethiopian

Review sources in Addis Ababa. Political and business associates of Azeb Mesfin are dropping like flies. The biggest one to fall was Gebrewahid WoldeGiorgis, a senior official, who was charged with stealilng over one hundred million birr. Others are leaving the country with their families. Since May 2013, over 50 high profile TPLF officials and businessmen have been arrested on charges of corruption. All of them are associates and partners of Azeb. Azeb, aka the Mother of Corruption, is currently being protected by Abay Woldu, chairman of the ruling Tigray People Liberation Front (TPLF), and Bereket Simon, former propaganda chief, but both Abay and Berket are being marginalized, and Abay is fighting to maintain his diminishing authority over TPLF.

ጉድ በል ጎንደር!!!! ፕሬዝደንት ግርማ ወ/ግዮርጊስ በወር 400,000 ብር የሚከፈልበት የመኖሪያ ቤት ውል ተፈራረሙ

ጉድ በል ጎንደር!!!! ፕሬዝደንት ግርማ ወ/ግዮርጊስ በወር 400,000 ብር የሚከፈልበት የመኖሪያ ቤት ውል እንደተፈራረሙሰማን ። በሀይሌ ገ/ስላሴ ጎዳና ከአክሱም ሆቴል ጀርባ የሚገኝ የመዋኛ ገንዳ ጨምሮ ባለ ሁለት ፎቅ ህንፃ የሆነ ነው:: ህንፃው ለፕሬዘዳንቱ ከመተላለፉ በፊት ዳን ቴክኖክራፍት በተባለ ድርጅት 1.6 ሚሊዮን ብር የሚያወጣ ሊፍት እየተገጠመለት ነው፡: ሀገሪቱ በድህነት በርሀብ በችግር ህዝቡም በኑሮ ውድነት መላወሻ አጥቶ እየተንገላታ እነሱ ይህን ያህል ብር በየወሩ ለቤት ኪራይ?መሪዎቻች ለምን የደሀ ሀገር መሪዎች እንደሆኑ ይረሳሉ :: እስቲ ስለእውነት እንነጋገር ስንት ዜጎች ጎዳና ላይ? ስንት ጠዋሪ ያጡ አረጋውያን? ስንት ወላጅ አልባ ህፃናት? ስንቱ በህመም የአልጋ ቁራኛ? ሆኖ በሚኖሩባት ሀገር ይታያችሁ በወር 400.000 አራት መቶ ሺ ብር፤፤በወር 400,000 በአመት 4.8 ሚሊየን ብር በ10 አመት "የሚኖሩ ከሆነ"480 ሚሊየን ብር ማለት ነዉ።ስንት ስራአጥ ወጣቶችን ሂወት ይቀይራ
ል ? ስንት የህክምና ተቋም ይሰራል? በ እኔ እምነት የኢትዮጵያን ህዝብ ከመናቅና ምን ያመጣል ከሚል ስሜት የመጣ ነው::አረ እባካችሁ ለተቸገሩት እንዘንላቸው፡፡ ጸረ ሙስና ኮሚሽን ስራው ምንድን ነው የፕሬዘደንቱ የገንዘብ ምንጭ ምንድ ነው :: ለህዝብ ሊገለጽ ይገባል:: ዘሪቸስት.ኮም (www.therichest.com) በ2013 ባወጣው የሀብታም ፕሬዝደንቶች ስም ዝርዝር ውስጥ የኛ ፕሬዝደንት ግርማ ወ/ጊዮርጊስ በ 1.5 ሚሊዮን ዶላር ከአለም ሶስተኛ ፕሬዝደንት እንደሆኑ አስነብብዋላ:: በቀን አንዴ እንኳን ጠግቦ ለመብላት ያልታደለውን ህዝብ ከግምት ውስጥ ያላስገባ የተጋነነ ወጪ ፡፡ከአንድ ሀገር መሪ (ርእሰብሄር) ትልቅ ሰው ያማይጠበቅ አሳፋሪ ተግባር ነው፡: ንጉስ ክፍሌ:: ጉድ በል ጎንደር!!!! ፕሬዝደንት ግርማ ወ/ግዮርጊስ በወር 400,000 ብር የሚከፈልበት የመኖሪያ ቤት ውል እንደተፈራረሙ ሰማን። በሀይሌ ገ/ስላሴ ጎዳና ከአክሱም ሆቴል ጀርባ የሚገኝ የመዋኛ ገንዳ ጨምሮ ባለ ሁለት ፎቅ ህንፃ የሆነ ነው:: ህንፃው ለፕሬዘዳንቱ ከመተላለፉ በፊት ዳን ቴክኖክራፍት በተባለ ድርጅት 1.6 ሚሊዮን ብር የሚያወጣ ሊፍት እየተገጠመለት ነው፡: ሀገሪቱ በድህነት በርሀብ በችግር ህዝቡም በኑሮ ውድነት መላወሻ አጥቶ እየተንገላታ እነሱ ይህን ያህል ብር በየወሩ ለቤት ኪራይ?መሪዎቻች ለምን የደሀ ሀገር መሪዎች እንደሆኑ ይረሳሉ :: እስቲ ስለእውነት እንነጋገር ስንት ዜጎች ጎዳና ላይ? ስንት ጠዋሪ ያጡ አረጋውያን? ስንት ወላጅ አልባ ህፃናት? ስንቱ በህመም የአልጋ ቁራኛ? ሆኖ በሚኖሩባት ሀገር ይታያችሁ በወር 400.000 አራት መቶ ሺ ብር፤፤በወር 400,000 በአመት 4.8 ሚሊየን ብር በ10 አመት "የሚኖሩ ከሆነ"480 ሚሊየን ብር ማለት ነዉ።ስንት ስራአጥ ወጣቶችን ሂወት ይቀይራል ? ስንት የህክምና ተቋም ይሰራል? በ እኔ እምነት የኢትዮጵያን ህዝብ ከመናቅና ምን ያመጣል ከሚል ስሜት የመጣ ነው::አረ እባካችሁ ለተቸገሩት እንዘንላቸው፡፡ ጸረ ሙስና ኮሚሽን ስራው ምንድን ነው የፕሬዘደንቱ የገንዘብ ምንጭ ምንድ ነው :: ለህዝብ ሊገለጽ ይገባል:: ዘሪቸስት.ኮም (www.therichest.com) በ2013 ባወጣው የሀብታም ፕሬዝደንቶች ስም ዝርዝር ውስጥ የኛ ፕሬዝደንት ግርማ ወ/ጊዮርጊስ በ 1.5 ሚሊዮን ዶላር ከአለም ሶስተኛ ፕሬዝደንት እንደሆኑ አስነብብዋላ:: በቀን አንዴ እንኳን ጠግቦ ለመብላት ያልታደለውን ህዝብ ከግምት ውስጥ ያላስገባ የተጋነነ ወጪ ፡፡ከአንድ ሀገር መሪ (ርእሰብሄር) ትልቅ ሰው ያማይጠበቅ አሳፋሪ ተግባር ነው፡: ንጉስ ክፍሌ::

Displacement follows clashes on Kenya-Ethiopia border

MOYALE, 6 September 2013 (IRIN) - Thousands of families remain displaced from the northern Kenya district of Moyale, close to the Ethiopian border, following the latest spate of clan
violence, which has left at least two dozen dead since it broke out on 30 August. Aid agencies say they have been unable to conduct a comprehensive assessment of humanitarian needs, essential for providing emergency assistance to populations in some of the district's more volatile areas. Two days of inter-clan fighting among the Gabra, Burji and Borana communities saw houses torched, gunfire exchanged and business come to a standstill in the areas of Somare and Teti. The violence has since subsided, but tension remains high in the area. Education officials say all 32 primary and secondary schools in Moyale remained closed on 2 September, as all both teachers and students remained displaced, too afraid of renewed violence to return home. The violence is believed to be part of a series of revenge attacks that began when the Borana and Gabra clashed on 15 July, leaving one dead and three wounded. Displaced "More than 38,000 people from 6,381 households have been forced to leave their homes," said the Kenya Red Cross Society's (KRCS) Moyale coordinator, Stephen Bonaya, who noted that most of the displaced had crossed into Ethiopia, while others were staying with relatives in Moyale and the counties of Marsabit and Wajir. He said scores of children, women and men were still separated from their families, while others were missing. "A team is helping families trace lost members and reunite them. At the moment, 60 families have been united," he added. According to Bonaya, displaced families are in urgent need of food assistance, shelter, drugs, water, cooking utensils, clothing and mosquito nets, among other things. Moyale's traders say the suspension of operations by transporters has led to a spike in food prices in the area. "My lorry has been parked for a whole week now. I am afraid it could either be burnt or hijacked, and yet I am supposed to service a loan," said Golicha, a truck owner. Ismail Adan, a livestock trader and a transporter, said the prices of hiring and ferrying livestock by lorries doubled as a result of the clashes. "It's not possible to make any profit from livestock trade. Animals at the market are too few and very expensive," he said. Seeking a solution Historically, the regions' communities - which straddle Kenya and Ethiopia - have fought over resources such as pasture and water for their livestock, butresearch by Tufts University and KRCS shows that the violence has recently become more deadly and communities and their leaders now seek to achieve control over these resources through the political system. "The government is now in charge. Militia gangs from the warring communities have been flushed out [by the police and the army]," Marsabit County commissioner Isaiah Nakoru told IRIN. "Some have fled and crossed the border. We have arrested eight Ethiopians, two Kenya[ns]. The state is serious; nobody will escape punishment... Politicians responsible will not be spared." He added that preliminary investigations had established that "foreign militia" armed with mortars and bombs had fuelled the fighting. People affected by the conflict say the intermittent violence will continue unless the government addresses the root causes, involving the warring communities and their leaders. "This is a political problem. Neither Kenya's entire military nor police can contain or end this problem. Arrest the politicians, involve all communities in the political process and share resources fairly," said one Moyale resident, who preferred anonymity. Former national assembly speaker Francis Ole Kaparo said a peaceful solution to the conflict needed to be found. "These communities must stop this bloody way of resolving disputes and share them [resources] or lose all anticipated benefits," he told IRIN

Police Block Blue Party Rally Near Office


The Blue Party are highly protesting the Ethiopian government to stop interfering in religious affairs , to realize the political prisoners and to stop ethnic politics in the country .they are also demanding citizen justice and freedom .But Police blocked thousands of Blue Party demonstrators from rallying to the City’s biggest square, Meskel Square. They were blocked after they walked 100 meters from their Head office in Ginfele,near 4Kilo. The leaders of Blue Party have ordered demonstrators to return back to the Party’s Head Office and to peacefully continue the demo there. The demonstrators are voicing slogans like ” We Need Freedom, Police belongs to the people, we are one, Free Eskinder Nega, Free Reeyot Alemu and others”, sitting near their Head Office.

Monday, September 23, 2013

ወላጆች ንበረቶቻቸውን ከዘራፊዎች ለማስጣል በሪያድ ከኢትዮጵያ ዲፕሎማቶች ጋር እያደረጉ ያለው ትንቅንቅ ዛሬ ወደ ግጭት አመራ

በወላጆች እና በሳውዲ አረቢያ የኢትዮጵያ በዲፕሎማቶች መሃከል ዛሬ ሴፕቴምበር 22 2013 ምሽት ተፈጥሮ የነበረው ግጭት ለግዜው ጋብ ቢልም መንግስት በጉዳዩ ጣልቃ ገብቶ የተማሪዎቹ ወላጆች በተደጋጋሚ ላቀረቡት ጥያቄ አስቸኳይ መላምት ካለፈላለገ ጉዳዩ የከፋ ሊሆን እንደሚችል የወላጆች ኮሚቴ አባላት ይገልጻሉ! በተለይ ዛሬ ሴፕቴምበር 22/2013 ምሽት በሪያድ አለማቀፍ የኮሚኒቲ ት/ቤት ተማሪ ወላጆች ኮሚቴ የሳውዲ መንግስት በወጭ፡ሃገር ዘጎች ላይ ያወጣውን ህግ ተከትሎ በኤንባሲው የተመረጠው የት/ቤቱ ህገወጥ፡የቦርድ አስተዳደር «የመኖሪያ ፈቃድ አልተሞላም ፡ ፓስፖርት አልታደሰም ፡ ቦንድ አልገዛችሁም ፡ ወላጆቻችሁ የድምጻችን ይሰማ ደጋፊዎች ናቸው ……ወዘተ » በጣም አስዛኝ እና ግብረገብነት በጎደለው ሰንካል ምክንያት ከ 1ሺህ የሚበልጡ ተማሪዎችን ከትምህርት ገበታቸው ማፈናቀሉ ይታወሳል። በመሆኑም የአያሌ ኢትዮጵያውያን ህጻናት በሰው ሃገር ከትምህርት ገበታቸው መፈናቀል የአብዛኛውን ወላጆች በልጆቻቸው ላይ ያላቸው ተስፋ እንዲጨልም አድርጓ። ይህንንም የተረዳው 11 አባላት ያሉት የት/ቤቱ የወላጆች ኮሚቴ ከ1 ሺህ የሚበልጥ የድጋፍ ፊርማ በማሰባሰብ ኤምባሲው በራሱ ስልጣን መርጦ ህገወጥ በሆነ መንገድ ያስቀመጠው የት/ቤቱ ቦርድ አዲስ የትምህርት ዘምን መጀመርን አስመክቶ ያወጣውን የአዲስ እና ነባር ተማሪዎች መመዝገቢያ ማመዘኛዎች ትክክለኝነት በመጠራጠር ኮሚቴው የሳውዲ ት/ሚኒስቴር መ/ቤት ድረስ በመሄድ ለማጣራት ባደረገው ሙከራ በኢትዮጵያ ኤምባሲ ዲፕሎማቶች በእጅ አዙር እንዳይ መዘገቡ ታግደው ከነበሩ 1ሺህ ኢትዮጵያውያን ህጻናት ውስጥ 8 መቶው የሳውዲ ት/ሚ ያወጣውን ህግ የሚያሞሉ መሆናቸውን በማረጋገጥ፡ ወደ ትምህርት ገበታቸው እንዲመለሱ ኮሚቴው ማስቻሉን ተከትሎ ወላጆች በተጠቀሰው ቦርድ እና ከቦርዱ ጀርባ ሆነው በሪያድ እለም አቀፍ የኢትዮጵያ ኮሚኒት ት/ቤትን የመማር ማስተማር ሂደት እያመሰቃቀሉ ባሉ ወገኖች ዙሪያ ለመነጋገር ሴፕቴምበር 22 2013 የወላጅ ኮሚቴው በሪያድ የኢትዮጵያ ኮሚኒቲ አዳራሽ ስብሰባ ጠርቶ እንደ ነበር የወላጆች ኮሚቴ ተወካይ ይገልጻሉ ። ተወካዩም በማያያዝ ቀደም ብለው ስብሰባ ያደርጉባቸው የነበሩ ቦታዎች ወላጆች በግል በሚከራዮቸው አካባቢያቸው በሚገኙ የመዝናኛ ቦታዎች መሆኑንን ጠቀሰው በሪያድ የኢትዮጵያ ዲያስፖራ ሃላፊ የሆኑት አቶ ተመስገን ኡመር ይህ አዳራሽ እያለ ለምን ለድህነታችሁ አስተማማኝ፡ያልሆነ ቦታ ትሰበሰባላችሁ ከኤምባሲው እና ከኮሚኒቲው ርቃችሁ በድብቅ ስብሰባ ለምን ታደርጋላችሁ በሚል ቅን አስተሳሰብ ለወላጆ ኮሚቴው በሰጡት ሞራል እና ምክር ኮሚቴው ለእሁድ ቀን ሴፕቴምበር 22 2013 ከምሽቱ 7 ስዓት ጀምሮ ወላጆች በኢትዮጵያ ኮሚኒቲ አዳራሽ፡ እንዲገኙ የስብሰባ ጥሪ በደብዳቤ እንደበተኑ ያወጋሉ። እስከ ተጠቀሰው ቀን ድረስ ምንም አይነት ተቃውሞ ከኤንባሲው እንዳልነበረ የሚናገሩት የወላጅ ኮሚቴው ተወካይ በስበሰባው እለት ወላጆችን ለማስተናገድ ኮሚኒተው አካባቢ ወንበሮችን ስናስተካክል ውለን ለተለዩ ጉዳዩች ከግቢ ወጥተን ስንመለስ የግቢው በር ያለወትሮው በቁልፍ ተቆልፎ ጠበቀን። ጉዳዩን ለማጣራት ዘበኛውን በመስኮት ስንጠይቅ በአምባሳደር መሃመድ ሃሰን በተደገፈ ፌርማ በተጻፈ የደብዳቤ ተዕዛዝ መዘጋቱን ቢገልጽም በወቅቱ ጥሪ የተደረገላቸው ወላጆች ቁጥር እየጨመረ መምጣት አካቢው ተሽከርካሪ መተላለፊያ በመሆኑ ወላጆች ለአደጋ እንዳይዳረጉ ጠቅሰን በገዛ ቤታችን በር እንዲከፈትልን ብንማፀንም ዘበኛው ጉዳዩ ከአቅሙ በላይ ስለነበር ፈቃደኛ አልነበረም ብለዋል ። የኮሚኒቲው ሊቀመንበር አቶ ሙስጠፋ ሁሴን መጥተው በቁጣ የሚጉርመረመውን ወላጅ ለማረጋጋት ሙከራ በማድረግ የኮሚኒቲውን በር እንደሚከፍቱ እና ህዝቡ እንደሚገባ ቃል ገብተው ዲፕሎማቱን አነጋግሬ መጣሁ በለው ህዝቡን በር ላይ አቁመው በዛው መቀረታቸው አስነዋሪ እና አንድ የኮሚኒቲ ተወካይ ከሆነ አካል የሚጠበቅ አለመሆኑን ገልጸዋል። ከሰአታት ቆይታ በሃላ አልፎ አልፎ አምባሳደር መሃመድ ሃሰንን ወክለው እንደሚሰሩ የሚነገርላቸው ዲፕሎማት አቶ ዘላለም እና ቀደም ሲል በአዳራሹ እንደ ዜጋ መገልገል « መሰብሰብ » መብታችን መሆኑንን ምክራቸውን ሲልግሱ የነብሩ የዲያስፖራው ሃላፊ አቶ ተመስገን ኡመር በወቅቱ ህዝቡን ለማነጋገር መጥተው እንደ ነበር ቢታወቅም የህዝቡ ስሜት ጥሩ አለምሆኑ መገድ ላይ እያሉ መርጃ ስለደረሳቸው እና በአንዳንድ ተእግስታቸው በተሞጠጠ ወላጆች በገዛ ቤታችን እንዴት እንከለከላለን በሚል ቁጣ እና ንዴት ሊፈጸምባቸው የሚችለውን እርምጃ በመስጋት በት/ቤቱ የጓሮ በር ድምጻቸውን አጥፈተው በመግባት ህዝቡ ከአካባቢው እስኪበትን እዛው ባሉበት ድምጻቸውን አጥፈተው ለመቆየት መገደዳቸውን የአይን ምስክሮች ገልጸዋል። በመጨረሻ የወላጆች ኮሚቴው ወደፊት ተመሳሳይ የሆነ ስብሰባ እንደሚጠራ ጠቅሷ፡ህዝቡ እልህ ውስጥ፡ሳይገባ በሰከነ መንፈስ እና ህጋዊ እና ሰላማዊ በሆነ መንገድ አይን ባልገለጹ ሃገር ተረካቢ ታዳጊ ህጻናት ልጆቹ ላይ የተሰነዘረውን ጥቃት እና ንብረቱ የሆነውን በሪያድ አለም አቀፍ የኢትዮጵያ ኮሚኒት ት/ቤት ከዘራፊዎች ለማዳን እያደረገ ያለውን ትግል አጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት በመገስጽ የኢትዮጵያ መንግስት ለጉዳዩ ትኩረት ስጥቶ አስቸኳይ የሆነ መፍትሄ እስካላበጀለት ድረስ በዲፕሎማቱ እና በተማሪ ወላጆች መሃከል የተፈጠረው ግጭት ወደ ከፋ ደረጃ እንደሚሸጋገር አበክረው አሳስበዋል።

A Journalist kidnapped, Threatened, and Beaten by Intelligence and Security Agents in Ethiopia

A Journalist kidnapped, Threatened, and Beaten by Intelligence and Security Agents in

Ethiopia .The Ethiopian journalist Bisrat Woldemichael was kidnapped, threatened, humiliated, and beaten by the Ethiopian intelligence and security agents on 28 August, 2013. He has reported this incident today to journalists. Bisrat reported that the dreadful incident took place at Gotera, a place in the capital Addis Ababa as he was walking home from work. He said he was victimized for exercising his right to free expression in conjunction with the related right to press freedom. Bisrat Woldemichael works for a magazine, Ebony, as Editor in Chief, and writes political articles on different Ethiopian private press outlets. He also blogs at www.addismedia.wordpress.com and www.ethiopiahot.wordpress.com. The journalist is known for his outspoken articles focused on the poor governance and pervasive human right violation, which are turning the oldest East African nation, Ethiopia, into a hall. Violence against journalists is a common practice in Ethiopia, a country generally regarded as one of the most dangerous places to be a journalist. According to Amnesty International, during the past three years only, over 100 prominent journalists were brutally prosecuted on fabricated charges, and too many others were also subjected to harassment, intimidation, and other violence. “It was 3:30 AM in the evening, and I was returning home from my workplace. 4 people came to me and said: ‘we need to ask you some questions. Two of them were dressed in black and their faces were almost covered with their caps”, Bisrat said, while narrating his ordeal to journalists. “I first didn’t understand what was going on. I realized that I was in danger just when one of them put a knife on my stomach”, he noted. “When I saw the knife, I asked them: ‘Who are you? What do you need? But none of them gave me an answer, instead they warned me just to keep walking forward,” he explained. “I didn’t do anything but followed them, because I was surrounded, and the guy also clearly told me he would stab me with the knife if I tried to challenge them. In addition, one of them had a gun”, Bisrat said. From there Bisrat was taken to a place far away from the main road. The place he was taken to was quite dark and out of public sight. “As soon as we reached there they told me they were disappointed at my articles I had recently written, particularly at the one which dealt about the wealth of the late Prime Minister Meles Zenawi ”, Bisrat said. “They said: ‘Who are you to count the wealth of Meles Zenawi? Who are you to write about his family’s wealth? You have passed the red line!’ ” he explained. The journalist said that the kidnappers violently interrogated him at length, for almost one hour, and threatened him to stop writing. “They said: ‘here we are giving you a last warning. If you write any more for any media (or if you keep blogging), the consequence will be worse for you. If you need your life, stop wiring. Remember! It is a last warning’ ”, Bisrat explained. The journalist said that this was not the end of the drama but the beginning. “They also insulted and humiliated me, and finally began to beat me. Right after the incident, Bisrat was able to go to a nearby police station, to report the case. But, according to him, having heard the case, the police officers simply gave him an appointment for the coming mooring and let him go. Bisrat said that it took him several days to get the case registered. “They are Watching Me” Bisrat said since the day he experienced the violence he has been under surveillance. “Few days ago, I saw them following me behind”, he explained adding “I know they are watching me very closely.” But, in the face of such grave threats, Bisrat, a journalist who is committed to freedom of speech, has continued doing his job with courage. He continues writing about the political crisis, poor governance, and human right violation worsening in Ethiopia. “I don’t have a choice. I am a journalist. There is nothing to do except writing what I see, hear, and feel.” Bisrat explained. He again and again made clear that no threats and tortures would make him stop writing The paper Tigers Article 19 of the Universal Declaration of Human Rights, guarantees the right to freedom of expression saying that: “Everyone has the right to freedom of opinion and expression; this right includes freedom to hold opinions without interference and to seek, receive and impart information and ideas through any media regardless of frontiers. Likewise, the International Covenant on Civil and Political Rights (ICCPR), which Ethiopia ratified in 1993, and the African Charter on Human and Peoples’ Rights guarantee the right in a very clear way. They even impose formal legal obligations on state parties to insure this fundamental right is protected. But, sadly, even in the presence of all these legal documents, Enjoyment of press freedom and freedom of expression still continue to be a far cry for Ethiopian journalists and bloggers as they experience violence while doing their job. They are harassed, threatened, humiliated, and arbitrary jailed. Tags: Ethiopia, Ethiopian People’s Revolutionary Democratic Front (EPRDF), Freedom of expression, Human Right Violation, Journalists, Press Freedom By Betre Yacob Source: http://thedailyjournalist.com/theinvestigative/a-journalist-kidnapped-threatened-and-beaten-by-intelligence-and-security-agents-in-ethiopia/
African dictators’ crocodile tear for justice Sunday, September 22, 2013 By Belayneh Abate The gluttonous and corrupt African tyrants are raising their voice again against the international criminal court (ICC). They are preaching us that ICC is an unjust institution which hunts only Africans. I do not think Africans would have any problem if this claim came
from people other than African Rulers who murder innocent peoples every minute using guns, prisons, torture chambers, starvation and disease as weapons. The urgent priority for these shameful despots is the unequal treatment of heinous criminals; not delivering justice for victims of the criminals. Is not this another indicator for the immoral nature of the African despots? Unlike these wicked dictators, I hope Africans would set the priority the other way around. Ya! Africans should demand justice for the victims before they talk about unequal treatment of mass murderers. Humanity exists wherever humans live. Therefore, perpetuators of crimes against humanity and genocide shall face justice (even after death) anywhere on this earth. The African dictators’ claim that ICC should set dreadful African murderers free since it is not chasing criminals from other parts of the world is a non-sense argument. The African oppressors (many of them mass murderers) are barking that the unjust ICC should stop looking for them when they massacre innocent African citizens in one or another way. What a shame! Which direction their three fingers direct when their index finger points towards the ICC? Do not these African tyrants kill citizens even when they are not happy with the color of their victims’ eyes? How many people are being killed in Africa every day by these despots’ armed forces? How many innocent people are dying in infested prisons? How many are experiencing physical, mental and psychological tortures in Africa as we speak? Is it not enamoring to observe when African rulers who slaughter their own citizens like livestock speak about justice? ICC may have its own limitations. However, ICC is not looking for Nelson Mandela or John Mahama. ICC is looking for criminals who appointed themselves as rulers and committed crimes against humanity and genocide. Otherwise, who should be responsible for the bloodshed in Liberia, Rwanda, Sera Leone, Ethiopia, Libya, Kenya, Sudan and other unfortunate countries? Who shall be held accountable for the illegal imprisonments, tortures, disappearances, ethnic conflicts, mass murders being committed in most of African countries as we speak? African dictators! Please listen if you have functioning ears and a processing brain. The major concern for your victims and perhaps for any humane- African citizen is your dictatorial rule, your boundless greed, your endless mass murder, crime against humanity and genocide; not ICC’s partiality. I do not think any concerned African citizen will care if Satan, let alone ICC, brings you to justice. An African adage goes “it does not matter where you crush the crop; just bring the flour.” What is needed is justice for your victims! You should face justice anywhere on earth or in the sky for the endless monstrous crimes you repeatedly committed against innocent Africans to prevent further flourishing of your clones on Africa soil. The writer can be reached at abatebelai@yahoo.com posted by Daniel tesfaye

የአባይና የደብረፅዮን ጠብ በጣም በመክረሩ የተነሳ ሽጉጥ መማዘዛቸው ተሰምቷል{የአባይ ቡድን በሁለት ተከፈለ !!!

http://www.zehabesha.com/amharic/archives/7629

Abay-woldu-and-Debretsion ህወሓት በአባይ ወልዱና ደብረፅዮን ቡድኖች በሁለት መከፈሉ ይታወቃል። ባለፈው የህወሓት የማእከላዊ ኮሚቴ ስብሰባ የአባይና የደብረፅዮን ጠብ በጣም በመክረሩ የተነሳ ሽጉጥ መማዘዛቸው ተሰምቷል። ሃይለማርያም ደሳለኝና በረከት ስምዖን ለማስታረቅ የሞከሩ ሲሆን ዉጤቱ አልታወቅም። ይህ በንዲህ እንዳለ የአባይ ቡድንም ሰሞኑ በሁለት ተከፍሏል፤ የአባይ ወልዱና የበየነ መክሩ። ከህወሓት ስብሰባ በኋላ የስልጣን ሽግሽግ ለማድረግ የተሞከረ ቢሆንም በየነ መክሩና ኪሮስ ቢተው ከስልጣናቸው ለመውረድ (ሓላፊነት ለመቀየር) ፍቃደኛ ባለመሆናቸው ከአባይ ወልዱ ጋር ከፍተኛ አምባጓሮ ተፈጥሯል። ኪሮስ ቢተው የግብርና ቢሮ ሓላፊና የኢንተርፕራይዞች የቦርድ ሰብሳቢ ነበር። አባይ ወደ ሌላ ቢሮ ሊቀይሮው አስቦ ፍቃደኛ ሳይሆን ቀርቷል። የኢንተርፕራይዞች (ብዙ በጀት የሚመደብበት) ስልጣን ግን ቀምቶ ለአለም ገብረዋህድ ሰጥቶታል። ግብርና ቢሮም ለወደ አዳል ታስቦ ነበር። ግን ጠብ ስለተነሳ አልተሳካም። በየነ መክሩም የንግድና ኢንዱስትሪ (የከተማ ልማት ጨምሮ) ስልጣን በእጁ ሲሆን አባይ ቢሮው ለሌላ ሊሰጠው ፈልጎ ፍቃደኛ ባለመሆኑ ግን እስካሁን ውዝግብ ላይ ናቸው። በየነ መክሩ ወደ ሀገሩ (እስራኤል) የመሄድ ሓሳብ ይዟል። የአባይ ቡድን በሁለት መከፈሉ (አባይና በየነ የሚመሩት) ማሳያ በትግራይ ክልል የዉሃ ሃብት ቢሮ አመራር አባላት የሁለቱ ቡድኖች ደጋፊዎች ተጣልተው እንደተደባደቡና አከባቢው እስካሁን በፌደራል ፖሊስ እየተጠበቀ መሆኑ ተረጋግጧል። ስርዓት ሲበሰብስ እንዲህ ነው። ለማንኛውም ቸር ያሰማን። It is so!!! Abraha Desta

ሌ/ጀነራል ገዛኢ አበራ ቤተሰቦቻቸውን ሰብሰበው ስዊድን ገቡ

ሌ/ጀነራል ገዛኢ አበራ ቤተሰቦቻቸውን ሰብሰበው ስዊድን ገቡ (ዘ-ሐበሻ) የጦር ሃይሎች የሎጂስቲክስ ዋና ሐላፊ የነበሩት ሌ/ጀነራል ገዛኢ አበራ ቤተሰቦቻቸውን ሰብስበው ስዊድን መግባታቸውን አብርሃ ደስታ ከመቀሌ ባስተላለፈው መረጃ አመለከተ። አብርሃም ገዛኢ ከሃገር የወጡት በጡረታ ለተገለሉ በኋላ ነው በማላት ”የህወሓት ሃላፊዎችማ የያዙትን ይዘው ከሀገር እየወጡ ነው። የተቸገሩ ታችኞቹ ካድሬዎች ናቸው። እንደ አለቆቻቸው ወደ ዉጭ በመኮብለል የግል ደህንነታቸው መጠበቅ አይችሉም።” ሲል ትችቱን አስፍሯል። ጄነራል ገዛኢ አበራ በሱዳን አቢ ግዛት ሰፍሮ የነበረውን የኢትዮጵያ ሰላም አስከባሪ ሃይል የመሩ ናቸው። ከአንድ ዓመት በፊት የግንቦት 7 የኢትዮጵያ የጥናት ቡድን ባሰራጨው ምስጢራዊ መረጃ ወያኔ የአገዛዝ እድሜውን ለማራዘም የትግራይ ተወላጆች የሆኑትን የጦር አለቆች ከፍተኛ የሆነ ሃብት እንዲያካብቱና ዘረፋ እንዲፈጽሙ ሁኔታዎችን ማመቻቸት ለተለያዩት የጦር መኮንኖች ሟቹ ጠ/ሚ/ር በ1989 ለአ/አበባ አስተዳደርና ለመከላከያ ሚ/ር መ/ቤት ለ25 የወያኔ የጦር መኮንኖች፣ ለእያንዳንዳቸው በሽልማት በአዲስ አበባ ውስጥ 500 ካሬ ሜትር 1ኛ ደረጃ መሬት እንዲሰጣቸው ትእዛዝ በሰጡት መሰረት ይህን መሬት የተቀበሉት ሌ/ጄነራል ገዛኢ አበራ በወር 170 ሺህ ብር የሚከራይ ቤት ቦሌ አካባቢ ሠርተው እንደሚያከራዩ ተጋልጦ ነበር። ግንቦት 7 በአንድ ዓመት በፊት እንዳጋለጠው፦ የወያኔ የጦር መኮንኖች የአዲስ አበባን ከተማ በመዝረፍ ያከማቹት ሃብት ተራ/ቁ ማእረግ ስም ቦታው የሚገኝበት ወርሃዊ ኪራይ በብር የዘውግ መግለጫ 1 ሌ/ጄ ጻድቃን ገ/ትንሳኤ ቦሌ 25,000 ከ4 ዓመት በፊት ትግሬ 2 ጄኔ ሳሞራ የኑስ ቦሌ 28,000 ትግሬ 3 ሌ/ጄ ታደሰ ወረደ ቦሌ 38,000 ትግሬ 4 ሌ/ጄ ገዛኢ Aበራ ቦሌ 170.000 ትግሬ 5 ሌ/ጄ ብርሃነ ነጋሽ ቦሌ 38,000 ትግሬ 6 ሌ/ጄ ሳእረ መኮንን ቦሌ 35,000 ትግሬ 7 ሌ/ጄ አበባው ታደሰ ቦሌ 1,2 ሚሊየን መሬቱን የሽጠ አገው 8 ሜ/ጄ አበበ ተ/ሃይማኖት ቦሌ 2.5 ሚሊዮን መሬቱን የሽጠ ትግሬ 9 ሜ/ጄ አብርሃ ው/ገብርኤል ቦሌ 34,000 ትግሬ 10 ሜ/ጄ ዮሃንስ ገ/መስቀል ቦሌ 28,000 ትግሬ 11 ሜ/ጄ አባ ዱላ ገመዳ ቦሌ 45,000 ትግሬ/ኦርሞ 12 ሜ/ጄ አለሙ አየለ ቦሌ መሬቱን በ1.7 ሚሊዮን የሸጠ አገው 13 ሜ/ጄ ስዮም ሃጎስ ቦሌ 28,000 ትግሬ 14 ሜ/ጄ ሃየሎም አርAያ ቦሌ ? ትግሬ 15 ሜ/ጄ ገ/እግዚአብሄር መብራቱ ቦሌ 40,000 ትግሬ 16 ሜ/ጄ ባጫ ደበሌ ቦሌ 20,000 ኦሮሞ 17 ብ/ጄ ታደሰ ጋውና ቦሌ መሬቱን 1.2 ሚሊዮን ብር የሽጠ ትግሬ 18 ብ/ጄ ተክላይ አሽብር ቦሌ 60,000 ትግሬ 19 ብ/ጄ ፍስሃ ኪዳነ ቦሌ 30,000 ትግሬ 20 ብ/ጄ ፓትሪስ ቦሌ 34,000 ትግሬ 21 ብ/ጄ መስፍን አማረ ቦሌ 23,000 ትግሬ 22 ብ/ጄ ምግበ ሃይለ ቦሌ 20,000 ትግሬ 23 ብ/ጄ ሃለፎም ቸንቶ ቦሌ 22,000 ትግሬ 24 ኮ/ል ታደስ ንጉሴ ቦሌ 48,000 ትግሬ 25 ኮ/ል ጸሃየ መንጁስ ቦሌ መሬቱን 1.2 ሚሊዮን የሽጠ ትግሬ ከእነዚህ የጦር አለቆች ውስጥ ባሁኑ ሰዓት በተራ ቁጥር 1, 8, እና 17 ከስርአቱ ውጭ ሲሆኑ፣ በተራ ቁጥር 14 እና 24 ያሉት ደግሞ በህይወት የሌሉ ናቸው። ከላይ ከተጠቀሰው በተጨማሪ ወያኔ ለጦር አለቆቹ የሚሰጠው ጥቅማ ጥቅም የሚከተለውን ይመስላል። እነዚህ የጦር አለቆች በነጻ መሬት ወስደው ቤት በዘረፋ ከሰሩ በህዋላም በከተማው ውስጥ በመንግስት እጅ ከሚገኙ ምርጥ ቪላዎች መሃል ተመርጦ በተሰጣቸው ቤቶች ውስጥ በነጻ መኖር ቀጥለዋል። የውሃ የመብራት የስልክ ወጭዎችን ሙሉ በሙሉ የወያኔ መንግስት ይከፍላል። እነዚህ ሞልቃቃና ቅምጥል የጦር አለቆች በሚኖሩበት ቪላ ውስጥ ብርዱን
አልቻልንም በማለት ቤታችውን ሙሉ በሙሉ በውድ ምንጣፍ ማሽፈናቸው አልበቃ ብሉዋቸው ከፍተኛ የኤሌትሪክ ሃይል ፍጆታ የሚያስፈልጋችው የኤሌትሪክ የቤት ማሞቂያ መሳሪያዎች በየክፍሉ አስገጥመዋል። ምንጣፍ ለሚጠርገው የኤሌትሪክ መጥረጊያ ሆነ ለኤሌትሪክ ማሞቂያዎቹ የሚወጣው ክፍተኛ ወጪ፣ እንዲሁም እንዳሻቸው ለሚያፈሱት ውሃ በነጻ ተገልጋዮች እንዲሆኑ ተደርገዋል። በእዚህ ላይ ነጻ የሆነውን የሞባይልና የቤት ስልክ አገልገሎት ስንጨምርው በነጻ የሚያገኙት አገልግሎት በሽዎች የሚቆጠር ብር ይደርሳል። የጦር አለቆቹ ራሳቸውና ቤተሰቦቻቸው፣ ከእዚህም አልፎ አባትና እናቶቻቸው ሳይቀሩ እሰከ ውጭ ሃገር ድረስ በመሄድ የሚሰጥ ነጻ ህክምና ያገኛሉ። ሁሉም የጦር አለቆች ተጨማሪ የመኖሪያና የንግድ ቤቶችን በመቀሌ በባህር ዳር፣ አንዳንዶቹም በአ/አበባ ከተማ፣ በድጋሚ መሬት እንዲወስዱና እንዲገነቡ ተደርገዋል። ከእዚህ በተጨማሪ በአዲስ አበባ ከተማ በዱከም በናዝሬትና በሌሎች ቦታዎች ለንግድና ለመኖሪያ ቤት የሚሆኑ ቦታዎች በመውሰድ ይህን መሬት በቀላሉ ለማያገኙ ሌላ የሃገሪቱ ዜጎች በከፍተኛ ዋጋ በመቸብቸብ ያካበቱት ሃብት ገደብ የሌለው ሆንዋል። ታደስ ወረደ፣ ወዲ እምቤቲ፣ ፍስሃ ኪዳነ፣ ገዛኢ አበራ የተባሉት የጦር አለቆች በዚህ ድርጊት በዋንኛነት ከሚጠቀሱት መሃል ናችው። ይህ አልብቃ ብሎ እነዚህ የጦር አለቆች በመከላከያ ሚኒስትር በተያዘ ከፍተኛ የመስተንገዶ በጀት በመጠቀም የሚኖሩትን የቅንጦት ኑሮ ለተመለከተ ሃገራችን በምን አይነት የቀን ጅቦች እንደተወረረች ለማየት የሚያስችል ይሆናል። በ1992 ዓ/ም መከላከያ ሚኒስቴረ ለመስተንግዶ ብቻ የመደበው በጀት 280,000,000 (280 ሚሊዮን) ብር ነበር። በእዚሁ በ1992 ዓ/ም የሶማሊያ ክልል አመታዊ በጀት በተመሳሳይ 280 ሚሊዮን ብር እንደነበር ስናስታውስ፣ ይህ ለጦር አለቆቹ የተመደበው በጀት ምን ያህል ግዙፍ እንደሆነ የኢትዮጵያ ህዝብ መረዳት ይችላል የሚል እምነት አለን። በእዚህ የመስተንግዶ በጀት በመጠቀም የጦር አለቆቹ በየቀኑ ብፌ እያዘጋጁ ራሳቸውን ሲቀልቡ ከእዚህም አልፈው እንደጥንቶቹ መሳፍንት ግብር እንዲያበሉ፣ ውድ የሆኑ የውስኪ አይነቶች እንደ ውሃ እያፈሰሱ የሚኖሩበትን ሁኔታ አመቻችቶላቸዋል። በእዚህ የመስተንግዶ በጀት አማካይነት የወያኔ የጦር አለቆች ከትንሹ ሹካና ማንኪያ ጀምሮ የጥራት ደረጃቸውን የጠበቁ ሶፋዎች የምግብ ጠረጴዛዎች አልጋዎችና ሌሎችም በአውሮፓና በአሜሪካ የሚኖሩ ታዋቂ ሃብታም ዘፋኞችና የፊልም ተዋንያኖች የሚገልገሉባቸውን የቤት ቁሳቁሶች መግዛት ችለዋል። የጦር አለቆቹ እነዚህን የቤት ቁስቁሶች በየአመቱ የመቀየር መብት ስለተሰጣችው በእዚህ መብት ስም የሚያባክኑት የህዝብ ሃብት እጅግ በርካታ ነው። እያንዳንዱ የወያኔ የጦር አለቃ ከሁለት በላይ ውድና ዘመናዊ መኪናዎች ተሰጥቶታል። እነዚህ መኪናዎች በየአመቱ በአዲስ ሞዴል መኪናዎች ይተካሉ። የወያኔ ጄኔራል አንድ መኪና ለራሱ ሌላ መኪና ለሚስቱና ለልጆቹ በመውሰድ፣ እነዚህን መኪናዎች በግላቸው ያለምንም ወጪ እንዳሻቸው ከመገልገል አልፎ የኮንትሮባንድ እቃዎች ማመላለሻ አድርገው ይገለገሉባቸዋል። የኮንትሮባንድ እቃዎችን ከድሬደዋ፣ ሃረር፣ ጅጅጋ አርቲሸክና ሞያሌ በማመላለሱ ስራ ተሰማርተው ከሚገኙት መሃል ጎልተው የሚታወቁት ሌ/ጄ ታደስ ወረደ፣ ሌ/ጄ ሳረ መኮንን፣ ሌ/ጄ አበባው ታደሰ፣ ሜ/ጄ ሙሉጌታ በርሀ፣ ሜ/ጄ አለሙ አየለና ሌሎችም በርካታዎች ናቸው። በሌላ መንገድም የተሰጣቸውን መኪና፣ ከመንግስት ያለምንም ገደብ ከሚወስዱት ነጻ ነዳጅ ጋር እያከራዩ የሚጠቀሙ ጄነራሎች ብዙ ናቸው። በዚህ ተግባር ከተሰማሩት በርካታዎች መሃል ሌ/ጄ ገዛኢ አበራ ብ/ጄ ሃለፎም ቸንቶ፣ ብ/ጄ ተክላይ አሽብርን መጥቀስ ይቻላል። የመከላከያ ሚኒስቴር በ1993 አ/ም ብቻ በአንድ ግዜ ለመለስ የጦር አለቆች መገልገያ የሚሆኑ 300 ኮብራ ቶዮታ ላንድ ክሩዘር አስገብተዋል። ኢትዮጵያን በመሰለ ደሃ ሃገር ውስጥ በአንድ ሚኒስቴር መስሪያ ቤት በአንድ ግዜ ብቻ ይህንን ያህል የውጭ ምንዛሪ ሲባክን አይቶ የማይደነግጥ ሃገር ወዳድ ዜጋ ይኖራል የሚል እምነት የለንም። ከእዚህ በተጨማሪ በመከላከያ ስር ያሉ ወታደራዊ መደቦችና ክበቦች የወያኔ የጦር አለቆች የግል ንብረቶችና መገልገያዎች እንዲሆኑ ተደርገዋል። የጎልፍ ክበብ፣ መኮንኖች ክበብ፣ ደብረዘይት የአየር ሃይል ክበብና በየክልሉ የሚገኙ ትላልቅ ክበቦችን ጨምሮ እነዚህ የጦር መኮንኖች እንዳሻችው ያለምንም ወጪ የሚሰክሩባቸውና የሚዝናኑባቸው ናቸው። ወታደራዊ መደብሮቹ እቃዎች ከቀረጥ ነጻ እንዲያስግቡ የተፈቀደላቸው በመሆናቸው ማንኛውም የውስጥ እቃዎቻቸውና ድርጅታቸው በልዩ በጀት የተሙዋሉላቸው በመሆናቸው ከፍተኛ ገቢ ያላቸው አትራፊዎች ናቸው። ይህ ትርፍ፣ በየጦር ሰፈሩ የሚሸጠው ሳር፣ ዛፍ፣ አትክልት፣ ውዳቂ ብረታ ብረትና አላቂ እቃዎች፣ የሚረቡ የወተት ከብቶችና የሚደልቡ የስጋ በሬዎች በሙሉ የውያኔ የጦር አለቆች ተጨማሪ የግል ገቢዎች ምንጮች ናቸው። http://www.zehabesha.com/amharic/wp-content/uploads/2013/09/General-Gezae.jpg http://www.zehabesha.com/amharic/?p=7622

አወይ ሶሪያ….የኢትዮጵያ ጠላት!

September 23, 2013 (በሰሎሞን ተሰማ ጂ.) የሶሪያ ጉዳይ ከዕለት ወደ ዕለት እየከፋ መጥቷል፡፡ በስልጣን ላይ ያለው ጎሳ “የአላዊት ጎሳ” ይባላል፡፡ አላዊቶችና በደዊኖች በሽፍትነትና በባህር ላይ ውንብድና ስማቸው የገነኑ ናቸው፡፡ በደዊኖች፣ ሶሪያን ለዘመናት ያህል ሲፈልጧትና ሲቆርጧት ኖረዋል፡፡ እንደነሱ ዘረኛ፣ እንደበደዊኖች ጠባብ፣ አክራሪና ቁመኛ ታይቶም-ተሰምቶም አይታወቅም፡፡ አላዊቶችም ቢሆኑ “አልሸሹም ዞር አሉ” ናቸው፡፡ እነዚህ ወገኖች፣ የሶሪያን ሀገረ-መንግሥት (State apparatus) ከተቆጣጠሩበት ዘመን ጀምሮ ለኢትዮጵያ በጎ ተመኝተውላት አያውቁም፡፡ ይባስ ብሎ ደግሞ፣ ከ1950ዎቹ መጀመሪያ ወዲህ እጅግ በከፋ መልኩ የኢትዮጵያን ጥቅምና ሉዓላዊነት በሚፈታተን መልኩ በግትርነት ቆመው ነበር፡፡ በጣም በተጋነነና በመረረ ኹናቴ መንቀሳቀስ የጀመሩት ግን ከ1953ዓ/ም ወዲህ ነው፡፡ በዚህ ዓመትም በጂዳ-ሳዑዲት ዓረቢያ የተቋቋመውን “የኤርትራ ነፃ-አውጪ ድርጅት” (ወይም በተለምዶ አጠራሩ ጀ.ብ.ሐ) እየተባለ የሚታወቀው፣ በአሳውርታ የሚኖሩት የቤንአሚር ጎሳ ተወላጆች ቡድን ለመደገፍ በደዊኖች ተሯሯጡ፡፡ ከእነርሱም ቀጥሎ ወደስልጣን የመጡት አላዊቶች ተመሳሳይ ተግባር ፈፀሙ፡፡ ያለምክንያት አልነበረም፤ በአሳውርታ የሚወለዱት ቤንአሚሮች “የበደዊንና የአላዊት ደም አላቸው” ከሚል ጎሰኛ ቀመር ተነስተው ነው፡፡ Syria officially the Syrian Arab Republic ስለሆነም፣ በ1955ዓ/ም በይፋ ለጀ.ብ.ሐ አገናኝ ቢሮ በደማስቆ ከተማ ተከፈተለት፡፡ ከዚያም ጊዜ ጀምሮ፣ በርካታ ፀረ-ኢትዮጵያ እንቅስቃሴዎችን መደገፍ ጀመሩ፡፡ በ1960 እና 1961ዓ.ም ብቻ እንኳን፣ “ነፃነትን-መደገፍ” በሚል ስም፣ እ.አ.አ እስከ 1970 ድረስ በበደዊን ጎሳዎች የሚመራው የሶሪያ መንግሥት በርካታ የአጋሚዶ/የውንብድና ተልዕኮዎችን ከአፍ-እስከ-ገደፉ ደግፏል፡፡ (ይሄንን በተመለከተ፣ በ1933ዓ/ም በደቀሽሐይ-ሐማሴን የተወለደውና በጀብሐ ውስጥ የ5ተኛው ወታደራዊ ክፍል/ምድብ ዋና መሪ የነበረው፣ ወልዳይ ካህሳይ ብዙ-ብዙ ነገር ያወሳናል፡፡ ወደኋላ ላይ እንመለስበታለን፡፡) በዚህ የመቀራረብና የመተሳሰብ ዘመን በሆነው በ21ኛው ክፍለ ዘመን፣ በደዊኖችና አላዊቶች ከአንድ መንግሥት የሚጠበቀውን ዓለም አቀፍ ኃላፊነት ዘንግተው፣ ዓለም አቀፍ ውንብድና ውስጥ ሙጭጭ አሉ፡፡ በዘመናዊ አስተዳደር፣ ሃይማኖትና ጎሳ እምብዛም ቦታ እንደሌላቸው ያልተገነዘቡት በደዊኖችና አላዊቶች፣ በዘር፣ በጎሳና በሃይማኖት ጥላ ስር የተሰባሰቡትን ወንበዴዎች ሁሉ በወታደራዊ ስልጠናና በትጥቅ ሲረዱ ኖረዋል፡፡ በዚህም አቋማቸው የተነሳ በመካከለኛው ምስራቅ ውስጥ የተነሱትን ማናቸውንም ግጭቶች ቤንዚን በማርከፍከፍ ሲጋግሙት ኖረዋል፡፡ ወይም በሀገራችን አባባል ጭድ ሲነሰንሱበት ኖረዋል፡፡ ሊባኖስ ቀንደኛዋ ተጎጂ ናት፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትሯ ሐሪሪ ሳይቀሩ የተገደሉት በሶሪያ ጎሰኞች መሰሪ ደባ ነው፡፡ (በአሜሪካዊያኑና በበርካታ የዓረቡ ዓለም ሰዎች የተጠላውና የተወገዘው-“ጫማ ሳይቀር የተወረወረበት”-ትንሹ ጆርጅ ቡሽ እንኳ፣ “የዳቢሎስ ዛቢያ (Evil Axes)” ብሎ እስኪጠራት ድረስ፣ የበደዊኖቹና የአላዊቶቹ ሶሪያ፣ እጅግ አገደኛ ምሳር ናት፡፡) ከአላዊቶች ጎሳ/ወገን የሆነው የሶሪያው ፕሬዝዳንት፣ በሺር አላሳድ ይባላል፡፡ ከደማስቆ ዩኒቨርሲቲ በዓይን ሕክምና (Ophthalmology) ዶክተር ነው፡፡ እ.አ.አ ከ2000ዓ/ም እስካሁን ድረስ በስልጣን ላይ ተፈናጧል፡፡ ከእርሱ በፊትም አባትየው ሀፊዝ አላሳድ (እ.አ.አ ከ1971-2000) ሶሪያን አንቀጥቅጦ ገዝቷታል፡፡ የጦር ጀነራልና ከ1946 (እ.አ.አ ጀምሮ የባዐዝ ፓርቲ አባልና መሪም ነበር፡፡) አላዊቶችም የበደዊኖቹ በሽታ አለባቸው፡፡ እነርሱም ከላይ እንደገለጽነው-ዘረኝነት፣ ጠባብነትና አክራሪነት ናቸው፡፡ ከ1957ዓ.ም ጀምሮ በኮሚኒዝም ስብከትና አስተምህሮት ናላቸው የዞሩትን ተማሪዎችና ወጣቶች ለመደገፍ የሩሲያ፣ የቼኮዝሎቫኪያና የቻይና መንግሥታት ያልተገደበ ጥረት አድረገዋል፡፡ ለዚህም ማሳያው ደግሞ፣ በመጋቢት 4/1961ዓ.ም ሁለት የሩሲያ፣ ሦስት የቼኮዝሎቫኪያና ሁለት የቻይና ዜጎች ኢትዮጵያን በ24 ሰዓታት ውስጥ ለቀው እንዲወጡ ተደርገዋል፡፡ ሁሉም፣ ኮሚኒዝምን በየትምህርት ቤቱና በየኮሌጆቹ ለማስረጽ በመሞከራቸውና ወጣቶችን ለዓመጽ በመቀስቀሳቸው ነበር፡፡ ይህ ሴራቸው የተደረሰባቸው ሦስቱ አገሮች ጀብደኛውን የሶሪያ ጎሰኛ መንግሥት እንደፈለጉት ተጠቅመውበታል፡፡ እነዚህ ጊዜ የሠጣቸው ኃያላን መንግሥታት፣ የራሳቸውን ተጽዕኖ ኢትዮጵያ ላይ ለመጣልና በሀገራችን ጉዳይ ጣልቃ ለመግባት ያልፈነቀሉት ነገር አልነበረም፡፡ ያ ስር የማይሰድላቸው ቢመስላቸው፣ የሶሪያን ጣልቃ ገብነት ተማፀኑ፡፡ አርቀው የማያዩትም የሶሪያ መሪዎች ዘው ብለው ገቡበት፡፡ ምክንያታቸው ግልጽ ነው፤ የሶሪያ ጣልቃ ገብነት ለሌሎች ኃያል ኮሚኒስቶች መሣሪያና ስልጠና መሸጋገ ድልድይ በመሆን ነው፡፡ በሌላ በኩል ደግሞ፣ “ነጋዴ ራሱ ስለተቀማ ሳይሆን፣ ሌላው ነጋዴ ስለዳነ ይቆጫል፤” በሚለው የአገራችን ምሳሌ አማካይነት ሊተረጎምም ይችላል፡፡ የሶሪያ መንግሥት በሀገሩ ውስጥ ያለውን ሁከት፣ ትረምስና ብጥብጥ፣ ከዚያም አልፎ ከእስራኤል ጋር ከነበረው የተደጋገመ የተጠቂነት ሽንፈት የዜጎቹን አስተሳሰብ ለማስቀየስ፣ ሌሎች የእስራኤል መንግሥት ወዳጆች ናቸው ያላቸውን አገሮች በመተናኮል ሊወጣ ሞክሯል፡፡ ይህ አባዜ፣ “ወድቆ የቆመው እንደመጎተት” ዓይነት ነው፡፡ ከላይ እንደገለጽነው፣ የሶሪያ መንግሥት በኢትዮጵያ የውስጥ ጉዳይ ጣልቃ መግባት ከጀመረና ኢትዮጵያን መተናኮልም ከጀመረ ቆይቷል፡፡ በ1958ዓ.ም ከኢትዮጵያ ተጠልፎ ወደካርቱም የተወሰደውን የኢትዮጵያ አይሮፕላን የጠለፈው ወጣቱ ከበደ ደበላ፣ መጀመሪያ ጥገኝነት ያገኘው ሶሪያ ደማስቆ ነበር፡፡ የፈረንጆቹ 1969 ዓ.ም ደግሞ የሶሪያ የጠላትነት ሽፍንፍን ቅልጥጥ ብሎ የወጣበት ዓመት ሆነ፡፡ በዚሁ ዓመት ከተሞከሩት የኢትዮጵያን አየር መንገድ የማጥቃት አምስት ሙከራዎች ውስጥ አራቱ የሶሪያ መንግሥት ቀጥተኛ ድጋፍ ነበራቸው፡፡ በዕለተ ማክሰኞ መጋቢት 2/1961ዓ.ም ፈራንክፈርት አይሮፕላን ማረፊያ በቆመበት በሁለት ፈንጂዎች የተቀጣጠለውን ቦይንግ 707 አይሮፕላን በስልጠናና በትጥቅ የደገፈችው ሶሪያ ነበረች፡፡ በዚሁ ዓመት፣ በሚያዝያ 2/1961ዓ/ም በካይሮ ከተማ አቅራቢያ (105 ኪ.ሜ በስተደቡብ) ከወደቀው የኢትዮጵያ አየር መንገድ ጋግላስ ሲ-47 አይሮፕላን አደጋ ጀርባም ያለችው መሰሪ ሶሪያ ነበረች፡፡ በሰኔ 11/1961ዓ.ም ከምሽቱ 1፡15 ላይ ካራቺ አይሮፕላን ማረፊያ እንደቆመ ነበር በእጅ መትረየስ ከ50 ሜትር ርቀት ላይ አደጋውን የያሉት፡፡ እነዚህ ሦስት ሽፍቶች ከሶሪያ ተነስተው ካርቱም ላይ ሴራቸውን ካቀነባበሩ በኋላ፣ ወደ ቤይሩት በረሩ፡፡ ከዚያም ፓኪስታን ሁለተኛዋ ከተማ ካራቺ ደረሱ፤ አደጋውንም ጣሉ፡፡ ስማቸውም-መሐመድ ኢድሪስ፣ ፍስሐዬ አብርሃምና ዓሊ አብደላ የሚባሉ ናቸው፡፡ ሦስቱም ስልጠናቸውንና ትጥቃቸውን ከሶሪያ መንግሥት ያገኙ የጀብሐ አባሎች ነበሩ፡፡ ከእነዚህም የሶሪያ ቅጥረኞች ቀጥሎ፣ በዕለተ ሰኞ ነሐሴ 5/1961ዓ.ም ከአስመራ ተነስቶ በባሕር ዳር በኩል ወደአዲስ አበባ ይጓዝ የነበረውን ንብረትነቱ የኢትዮጵያ አየር መንገድ፣ የበረራ ቁጥር-231፣ DC-3 አይሮፕላን ባህር ዳር ከተማ ላይ ተሳፍረው ሲጠለፉትና ወደካርቱም ሲወስዱት ያሉት ነገር ቢኖር፣ “እኛ በማኦሴቱንግ ፍልስፍና የምናምን ኮሚኒስቶች ነን፡፡ አይሮፕላኑንም አስገድደን ወደካርቱም ያመጣነው ወደኮሚኒስት ቻይና ለመሄድ ላቀድነው ጉዞ ልንጠቀምበት ነው፤” ነበር ያሉት፡፡ እነዚህም የሲቪል አቬሽን ወንበዴዎች፣ በቀጥታ ከሶሪያ ጋር ግንኙነት ባይኖራቸው በርዕዮተ-ዓለማቸው የግራ ክንፍ አቀንቃኞች ነበሩ፡፡ የዚህኛው ጠለፋ አድራጊዎች ደግሞ፣ ሰባት የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ሲሆኑ፣ በአንዳንድ የባዕዳንን ሴራ ባልተረዱ ወገኖች በበጎ የሚነሱም ናቸው፡፡ ለምሳሌ በ1960 እና 1961ዱ የተማሪዎች ዓመጽ ዋነኛ አስበጥባጭና ተከሳሽ የነበሩት ዋለልኝ መኮንንና ማርታ ይገኙበታል፡፡ ከኋላቸው የነበሩት አገሮች ሩሲያና ቼኮዝሎቫኪያ ናቸው፡፡ በመስከረም 3/1962ዓ/ም ከድሬዳዋ ወደጂቡቲ ሲበር የነበረውን የኢትዮጵያ አየር መንገድ DC-6B አይሮፕላን መንገድ አስቀይረው ወደ የመን-ኤደን የወሰዱት የጀብሐ ሰዎች ተቀማጭነታቸው ሶሪያ-ደማሽቆ ነበር፡፡ ይህ አይሮፕላን 39 መንገደኞችና አምስት የአውሮፕላኑን ሠራተኞች ይዞ የነበረ ሲሆን፣ ሁሉም በደህና ሁኔታ በመስከረም 5/1962ዓ.ም ከቀትር በኋላ ወደአዲስ አበባ ተመልዋል፡፡ አይሮፕላኑን ሳልይዝ ወደኢትዮጵያ አልመለስም ያሉት ካፒቴን ቀፀላ ኃይሌና ጠለፋውን ያከሸፈው ም/የአስር አለቃ ካሳዬ ታደሰ ኤደን ቀርተዋል፡፡ (በነገራችን ላይ፣ ካሳዬ ታደሰ የሻለቃ ማዕረግ አግኝተው በጡረታ ከሠራዊቱ ከተገለሉ በኋላ፣ ኑሯቸውን በሎስ አንጀለስ አድርገዋል፡፡) አደጋው በደረሰበት በመስከረም 3/1962ዓ/ም አመሻሹ ላይ መቀመጫውን ሶሪያ-ደማስቆ ያደረገው የኤርትራ ነጻ-አውጪ ድርጅት (ጀብሐ) ኃላፊቱን ወሰደ፡፡ ጠለፋውን ያደረኩት “እኔ ነኝ” አለ፡፡ ከነዚህ “የቻይና ኮሚኒስት ነኝ!” “የአልባኒያ ኮሚኒስትን የሚከተል ከኔ በላይ ላሳር!” “የሩሲያን ኮሚኒዝም ጡት እየመገመገ ያደገ ማን እንደኔ!” ወይም ደግሞ “በመኮሚኒስትነት እኔ የቼኩ ምልምል አሽከር ጋር የሚፎካከር ማነው?” የሚሉት ወገኖች ሁሉ አንድ ናቸው፡፡ ሁሉም የግለሰብን መብት ለመደፍጠጥና የመንጋ (“ተራማጅ ነን ባዮችን”) መዋቅር እንደሸረሪት ድር ለማቆሸሽ የሚተጉ ናቸው፡፡ በጋማል አብደል ናስር ኮትኳችነት የተጀመረውና የዓረቡን ዓለም በኮሚኒዝም ርዕዮት-ዓለም ለማስተሳሰር የጣረው ባአዝ (BAAZ Party) የሶሪያ አውራ ፓርቲ ሆኖ ነበር፡፡ በገለልተኛ ሀገሮች ስራችነቷ ፀንታ ለመቆም የምትፍጨረጨረውን ኢትዮጵያን ኮሚኒስቶቹ አገሮች በጥላቻ ነበር የሚመለከቷት፡፡ ለዚህ ብያኔያን ጥሩ ማሳያ የሚሆነን የጀብሐ 5ተኛ ወታደራዊ ምድብ/ክንፍ አላፊ የነበረውና ይህንን ቃለ-ምልልስ ሲያደርግ የ29ዓመት ወጣት የነበረው ወልዳይ ካሕሳይ ነው፡፡ እስከ 12ተኛ ክፍል ድረስ በአስመራ ኮምቦኒ ትምህርት ቤት ተምሯል፡፡ ከዚያም በትውልድ መንደሩ በደቀሽሐይ-ሐማሴን ለሁለት ዓመታት ያህል አስተምሯል፡፡ በጥቅምት 25/1960ዓ.ም ካርቱም ለሚገኘው የኢትዮጵያ ኤምባሲ እጁን ሰጠ፡፡ ይህም ቃለ-ምልልስ የተደረገለት ካርቱም ሳለ ነበር፡፡ ወልዳይ ስለድርጅቱ እንዲህ አለ፤ “የጀብሐ መሪዎች እኔን የ5ተኛው ወታደራዊ ክፍል አላፊ ያደረጉኝ ወደው አይደለም፡፡ ‘በድርጅቱ ውስጥ አንድም ክርስቲያን ወታደራዊ መሪ የለም!’ ለሚለው የደጋው ኤርትራዊ ቅሬታ ማስተንፈሻ ሲሉ ነው እንጂ፤ በእውነተኛነት አስበውት አይደለም፡፡ እኔ ከምመራው ወታደራዊ ክፍል ውጪ ያሉት አራቱም ክፍሎች አንድም ክርስያቲያን ተዋጊ እንኳን የላቸውም፡፡ ለዚህ ደግሞ በቂ ምክንያት አለው፤ ድርጅቱ የሚሠራው ለአንዳንድ የዓረብ አገሮች ነው፡፡ ተዋጊዎቹም ሆኑ አመራሮቻቸው ስልጠና የሚያገኙት ወደሶሪያ እየሄዱ ነው፡፡ ለሽፍትነት ስልጠና ወደሶሪያ ከሄዱት 300 (ሦስት መቶ) ሰልጣኞች መካከል፣ አንድም ክርስቲያን አልነበረባቸውም፡፡ አምስት አረቢኛ ተናጋሪዎች ብንኖር እንኳን፣ ስማችንን እንድንለውጥ ተደርገናል፤” እያለ ያብራራል፡፡ ወልዳይ ለጀብሐ ርዳታ ስለሚያደርጉትም አገሮች ተጠይቆ ሲያብራራ እንዲህ ብሎ ነበር፤ “ሶሪያና ኢራቅ ወታደሮችን በማሰልጠን በኩል ሲረዱ፣ ሶሪያ በተለይ የጦር መሳሪያም በገፍ ታቀብለናለች፡፡ እንደሚታወቀው፣ ጀብሐት እ.አ.አ በ1961 ጂዳ-ሳዑዲ የተመሠረተ በመሆኑ፣ የሳዑዲ መንግሥትና ሕዝብ በገንዘብ በኩል ይረዳል፡፡ ከጎረቤት አገሮችም መካከል ግብጽ፣ ሱዳን፣ ሶማሊያና ጅቡቲ ሽፍቶቹ በዓረብ አገሮች በሚዘዋወሩበት ጊዜ የሚያገለግላቸውን ፓስፖርት በመስጠትና በልዩ ልዩ መንገዶችም ይረዳሉ፡፡ በተለይም ግብፅ የመሳሪያ እርዳታዋን ነፍጋን አታውቅም፤”በማለት ገልፆ ነበር፡፡ “ቻይናም የወታደሮች ልብስ ሰጥታ፣ ልብሱ ግን ለበረሃው ሊያገለግል ሳይችል ቀርቷል፡፡ በቅርቡ ለከፍተኛ የወታደራዊ ስልጠና ስኮላርሺፕ ሰጥታ-20 ሰዎች ተመርጠው ወደቻይና ለመሄድ ወደሶሪያ እያመሩ መሆናቸውንም” አመልክቶ ነበር፡፡ ወልዳይ እንዲህም ሲል አከለ፣ “በአሁኑ ሰዓት በኤርትራ ውስጥ 65% ክርስቲያኖችና 35% ደግሞ ሙስሊሞች ይገኛሉ፡፡ እስከ 4ተኛ ክፍል ድረስብቻ የነበረውም ትምህርት እስከ ዩኒቨርሲቲ ድረስ አድጓል፡፡ ታዲያ እኔ ለምን ብዬ ይሄንን እውነታ ከካዱ ሰዎች ጋር እሰለፋለሁ?” ሲል ተደምጧል(አዲስ ዘመን፣ ጥቅምት 1/1960ዓ/ም፣ ገጽ-1፣5 ይመልከቱ)፡፡ ማጠቃለያ፤ ከሰሞኑ፣ የበሺር አላሳድ መንግስት ላይ የወታደራዊ ጥቃት ለመክፈት አሜሪካንና ፈረንሳይ ቆርጠው ተነስተዋል፡፡ የባዝ ፓርቲና የአላሳድ ወዳጆች ሩሲያና ቻይናም እየተከላከሉለት ናቸው፡፡ የፀፅታ ምክር ቤትም በአንድ ዓመት ጊዜ ውስጥ ከሳዳም ሁሴን የተቀበላቸውን የኬሚካል የጦር መሳሪያዎች የአላሳድ መንግስት እንዲያስወግድ ቀን ተቆርጦለታል፡፡ የምዕራባዊያኑ አካሄድ፤ ወድቆ የቆመውን እንደመጎተት ያለ ነው፡፡ ሳዳምንም እንዲሁ ነበር ያደረጉት፡፡ ከ80ኪ.ሜ በላይ የሚወነጨፉትን አልሳሙድ ሚሳይሎቹን እንዲያስወግድ ነገሩትና አስወገደ፡፡ ከዚያም፣ ወረሩት፡፡ ይህ ሶሪያም ላይ እንደሚደገም ቅንጣት ታክል ጥርጠሬ የለኝም፡፡ የኢትዮጵያና የኢትዮጵያውያን ታሪካዊ ጠላቶች አሳር መከራቸውን ሲበሉ በማየቴ ምንያህል እደለኛነት እንደሚሰማኝ ልሸሽገው አልዳዳም፡፡ ኢትዮጵያና ሰላም ወዳድ ኢትዮጵያውያን በነፃነታቸው ለዘላለም ትኑሩ! ጠላቶቻቸውም ኹሉ በሰፈሩት ቁና ይሠፈሩ!….. Source/WWW.ECARDF.com